• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንዴት ሀገር (ህዝብ) ይጥፋ?

December 21, 2012 05:18 am by Editor Leave a Comment

 እንዴትሀገር (ህዝብ) ይጥፋ?

ያለመተማመን ስለዘራን ዘር

እንሰበስባለን የማያልቅ ‘መከር’።

‘’መግዛት’’ እውቀት ሆኖ፣ ገንዘብና ሀይል

አቋራጭ ጎዳናው ‘መቦልተክ’ ሆኗል።

ሃይማኖት ተንቃ ስትሆን መቀለጃ

የእግዚአበሄርም ቃል ሆነ ምነገጃ።

ሳይሰሩ ያገኙት ሀብት፣ ክብር – ዝና

ያስከብር ጀመረ መናቁ ቀረና።

ፈረሀ – እግዚአብሄር ከልባችን ወ’ቶ

ህገ – አውሬ ይገዛናል ሰው-ከሰው አባልቶ።

ለመሾም – መሸለም፣ መክዳት – መከዳዳት

ምግባራችን ሆኗል ዋናው ሀይማኖት።

እያለን የሌለን ስለሆን ተመፅዋች

መጠሪያችን ሆነ እናንተ ለማኞች።

እውነት ተገንዞ ስለተቀበረ

ውሸት ገዥ ሆነና ሰው ለ’ሱው አደረ።

ፍቅርና ሰላም ፈላጊ ስለአጡ

ተባረው ሄደዋል በአገር እንዳይመጡ።

በሌሎች ደም – እምባ፣ ንዋይ ማካበት

ስልጣኔ ሆነ ዘመናዊነት።

መተሳሰብ – ማዘን፣ ቅንነት – ጨዋነት

ሲወራም አንሰማም በተረትነት።

ወገን – ሀገር ማለት ወንጀል አድርገነው

ዘመናት አሳለፍን ቃሉን ከሰማነው።

ቁምነገር ተጠልቶ ስለተሰደደ

‘’ወቶ-ፎቶ’’ ወሬ እጅግ ተወደደ።

ምቀኝነታችን ቦታውን ያዘና

እንነጉደዋለን በጥፋት ጎዳና።

በክፋት በተንኮል ቀኑን አጨልመን

እርስ በርስ ተላለቅን አልተያይ ብለን።

መብቱን አሳልፎ ዜጋው ሰለሰጠ

በእጅ ያለውን ትቶ ማዶ ቀላወጠ።

እራሱን በራሱ ሰው ሰለአስናቀ

ባ’ገሩ እየኖረ ሀገሩን ናፈቀ።

ለስልጣን ነው እንጅ ‘’ለነብር ጅራት’’

ጊዜም የለን እኛ ድህነት ለማጥፋት።

ፍትህ – እኩልነት፣ ’ዲሞክራሲ’ እያሉ

መቀለድ ተለምዷል በህዝብ እየማሉ።

የጋራ መሆኗ ሀገርም ቀረባት

የበይ ተመልካች ፆም አዳሪ ሞላት።

ጥቂቶች በስልጣን በድሎት እንዲያድሩ

ስደተኛ ሆነ ሰው በገንዛ ሀገሩ።

እጅግ ስለከፋ የ’ኛ ሰው ጥላቻው

ይታመሳል ሀገር በሆነው ባልሆነው።

መግዛት ያቃተው ለመገዛት ሲሮጥ

ትውልድ ሁሉ አለፈ ያለነፃነት።

ጥፋት በጥፋት ላይ እያየን ሲስፋፋ

ቆም ብሎ የሚያስብ ‘’በቃ!’’ የሚል ጠፋ።

ህሊና ሰለአጣን ለምንሰራው ሥራ

ወገን ይነግዳል በወገን መከራ።

ፍርሀታችን በልጦ፣ ከሞት ፍርሀት

በቁም እንሞታለን በማይቀረው ሞት።

ሞት እንደሆን ላይቀር በዚህ ቢሉት በዚያ

እንዴት ሀገር (ህዝብ) ይጥፋ? የሌለው መተኪያ።

——–//———

ፊልጶስ / e-mail: philiposmw@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule