• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአሜሪካ የ፳፮ ሕፃናትና መምህራን ግድያና ግንዛቤዬ

December 20, 2012 04:38 am by Editor Leave a Comment

የምኖረው አሜሪካ ነው። አርብ ዕለት በከነቲከት ስቴት፣ ኒውታውን በምትባል ከተማ፤ ሳንዲ ሁክ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ፤ ፳ የስድስትና የሰባት ዓመት የአንደኛ ክፍል ተማሪ ሕፃናትና ስድስት መምህርቶቻቸው በትምህርት ቤታቸው ተገደሉ። የተገደሉት የእናቱን መሣሪያዎች አንግቶ፤ መጀመሪያ እናቱን ከተኛችበት ገድሎ፣ የትምህርት ቤቱን መጠበቂያ ጥሶ በገባ የሃያ ዓመት ጎረምሣ ደጋግሞ በረፈረፈባቸው ጥይቶች ነበር። አሜሪካ ከላይ እስከ ታች በዚህ ኢሰብዓዊ ተግባር ተርገበገበች። ከዩጋንዳ ለሐዘኑ መልዕክትና ማስታወሻ ተላከ። ከቦዝንያ፣ ከአውስትራሊያ፣ በጠቅላላው ከዓለም ዙሪያ የሀዘን መግለጫዎች ጎረፉ። የአሜሪካ ፕሬዚዳንት በቦታው በመገኘት የስነ ሥርዓቱ ተካፋይ ሆነው፤ የሀገሪቱን አጠቃላይ የሀዘን ትብብር ለሙታን ወላጆችና ለከተማው ነዋሪዎች አቀረቡ። እኔም የዚሁ ሀገር ነዋሪ ሆኜ ጉዳዩን በቅርብ ስከታተል፤ ሀዘኑ አጥንቴ ገባ። የሁለት ልጆች አባትም በመሆኔ፤ ውስጤ ተርገበገበ። ሁለተኛዋ ልጄ በሟቾቹ ተመሣሣይ ዕድሜ ያለች በመሆኗ፤ ሀዘኑን አቀረበብኝ። በሀዘኔ መካከል አዕምሮዬ አጥረ ሰፊ ነውና የሀገሬን ድቅድቅ የፖለቲካ ጨለማ ጥሶ መንከራተት ያዘ።

ጎንደር ከተማ መላኩ ተፈራ የጨፈጨፋቸው ለሰላማዊ ሠልፍ የወጡ ወጣቶች፤ ከፊቴ ተደቀኑ። በዓለም የሠራተኞች ቀን መከበሪያ (ሜይ ደይ) ምሽት፤ ፲ ፱ ፻ ፷ ፱ ዓመተ ምህረት አዲስ አበባ ውስጥ፤ በመንግሥቱ ኃይለ ማርያም ትዕዛዝ ሶስት ሽህ ወጣቶች ሲታረዱ ነበርኩና ልቤ ተንሰፈሰፈ። ወያኔ የሕዝቡን ድምፅ ለመቀማት፤ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ፤ በግንቦት ፲ ፭ ቀን ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ ዓመተ ምህረት ማግሥት የገደላቸዉ ፻ ፺ ፪ ወጣቶች አዕምሮን አጣበቡት። አሁን ካጋጠመኝ ሀዘን ጋር ሳመዛዝነው፤ ሁለት የሚዛን ሠፈሮች ጎልተው ወጡ። በኢትዮጵያ፤ በሥልጣን ላይ የሚወጡ፤ ሥልጣናቸውን ለመጠበቅ፤ ያርዳሉ፣ ያስራሉ፣ ያሳድዳሉ፤ እንዳሻቸው ያደርጋሉ። በዚህ ሀገር ደግሞ፤ የሀገሪቱ መሪዎች፤ ሰው ሲሞት፤ የሟቾችን ዕልፈት በመጠቀም፤ ተቀባይነታቸውን ለማሳደግ፤ በቀብራቸው ስነ ሥርዓት በአካል በመገኘት አብረው የሕዝቡን ሀዘን ይካፈላሉ።

ይኼ እንዴት ነው? የኢትዮጵያዊ ሕይወት በሚዛኑ ሲቀመጥ ሚዛኑ ስለሚቀል ነው? ለምን? መላኩ ተፈራ፣ መለሰ ዜናዊ፣ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም የግል ሕይወታቸውን ለማሣመር፤ ለሥልጣን ባላቸው ጥማት፤ “እኔ ብቻ ነኝ ትክክለኛው።” “ለሀገሪቱ እኔ አውቃለሁ።” “የምነግራችሁን ስሙ፤ የማዛችሁን ፊፅሙ።” እያሉ በሽዎች የሚቆጠሩ ሕፃናትን፣ ወጣቶችን፣ በመካከለኛ ዕድሜ ያሉትንና አዛውንትን ማረዳቸው ምን ይባላል? ይህ ከፖለቲካ አመለካከት በላይ ነው። ሌሎችን ገዳዮች ቀርቶ፤ እኔም ሰብዕናዬ ጥያቄ ውስጥ ገብቷል።

ኢትዮጵያዊ ከመሆኔ በላይ፤ ሰው ነኝ። ሰው በመሆኔም፤ ይህ አሜሪካ ውስጥ፤ በትንሽ ከተማ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የተደረገው አረመኔያዊ ተግባር፤ ዓይኔን በእንባ ልቤን በስስት ሞላው። ይኼ እንዳይደገም እፈልጋለሁ። ከሞላ ጎደል አሜሪካዊያን በሙሉ ይኼ እንዳይደገም ይፈልጋሉ። ከሞላ ጎደል በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች፤ ይኼ እንዳይደገም ይፈልጋሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ የደርግና የወያኔ ዘመን እንዳይደገም እፈልጋለሁ። ወያኔ ግን አሁንም አለ። ግድያውን፣ ማሠሩን፣ ማሳደዱን እየገፋበት ነው። ሰብዕናችንን የምናከብር ሁሉ፤ በቃ ልንል ይገባል። ወያኔ መወገድ አለበት።

ለሥልጣን ጥማት የተደረጉት ጦርነቶች ለምጥ፤ ሀገራችንን አጥለቅልቋታል። ለምጡ እያገረሸ፤ ተጨማሪ በደሎች ተጨማሪ ጦርነችን እያስከተሉ፤ የተከተሉት ጦርነቶች አዳዲስ ጠባሳዎችን እየፈጠሩ፤ ማለቂያ የሌለው እሽክርክሪት ውስጥ ገብተን እየዳከርን ነው። ለትናንቱ ግፍ፤ ዛሬና ነገ በዱቤ ተይዘው፤ አንገታቸውን ሰብረው እዳ ከፋይ ሆነዋል። እስከመቼ?

ወያኔ የትግራይን ሕዝብ ከኋላው ለማሠለፍ፤ ትግራይን የተለየችና ነፃ መዉጣት ያለባት አድርጎ አቀረበ። ለዚህም ይረዳው ዘንድ “እኛ” እና “ሌሎች” የሚል ፈጠረ። እናም “ወርቃሞቹን ትግሬዎች” ለማሰባሰብ፤ ጠላት አዘጋጀ። “አማራ ገዢ በመሆኑ፤ ትግሬዎች ተበደልን” አለ። ስለዚህ “ጠላታችን አማራ ነው” አለ። በገዥዎችና ተገዥዎች መካከል ያለውን በደል ተመርኩዞ የሚነሳውን ትክክለኛ ሕዝባዊ አመፅ፤ ወያኔ ባነገተው አቆማዳ ጠቅልሎ፤ ደደቢት ውስጥ ቀበረው። ይኼ ያልበገራቸው ጥሩ ኢትዮጵያዊያን አሉ። ትግሬ በመሆናቸው ወያኔን ከመደገፍ ይልቅ፤ ኢትዮጵያዊነታቸው ያየለባቸውና የወያኔን ምንነት ከማንም የበለጠ ያወቁ አሉ። አብዛኞቹ ትግሬዎች ግን፤ በአንድ ምክንያት ወይንም በሌላ፤ የወያኔ ሥርዓት ጠበቃ ሆነዋል። በምንም መንገድ ቢሆን ግን፤ ትግሬዎችን ጠቅልሎ ከወያኔ ጉያ መክተት፤ ፀረ አንድነት ነው። በአንፃሩ ልንገነዘበው የሚገባው፤ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ሲዳማ፣ ወይንም ሶማሌ ሆነው፤ ከወያኔ ለሚወረወርላቸው ትራፊ፤ የሀገራቸውን ሕልውና “ገደል ይግባ” ብለው የተሠለፉ ሆድ አደር ወያኔዎች መኖራቸውን ነው።

አንድ ነገር እንደገና በደንብ ግልፅ መሆን አለበት። በኛ ሀገርም ሆነ በሌሎች ሀገሮች፤ በጨቋኝና በተጨቋኞች መካከል ባለው ሀቅ፤ ተፃራሪ የሆኑ አቋሞችን በያዙ ክፍሎች መካከል ትግሎች ተደርገዋል፤ ይደረጋሉም። የመጨረሻው መለከት ሲነፋ፤ ወደ ፊት የሚመለከተው ወገን፤ ወደ ኋላ የሚመለከተውን ወገን አቸንፎ ይወጣል። ለትክክለኛ ፍትኅ፣ ለእውነት፣ ለእኩልነትና ለአንድነት የቆመ ወገን ያቸንፋል። ይህ በያንዳንዱ ዉጊያ የተመዘገበ አይደለም፤ በማጠቃለያው ጦርነት እንጂ። በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ያለው ትግል፤ ወደ ፊት በሚመለከተው የአንድነት ክፍሉና ወደ ኋላ በሚመለከተው ሀገር በታኙ መካከል ነው። ለሥልጣናቸው ሲሉ ሀገሪቱን ለመበታተን የሚያቀነቅኑት ይቸነፋሉ። የወደ ፊቱ የአንድነት ነው።

ታህሣሥ ፲ ቀን ፳ ፻ ፭ ዓመተ ምህረት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule