• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስለ “አንቀጽ 39” ማንን እናመስግን?

December 10, 2012 08:05 am by Editor 3 Comments

በዋዜማ ዝግጅቶች ሲታጀብ ከርሞ፣ ቅዳሜ የተከበረውን “የብሄር ብሄረሰቦች” ቀንን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎችን በማሳተፍ “አንቀጽ 39 ለዘላለም ይኑር” ብሎናል። እኛም ለዚህ ውለታ ማንን ማመስገን እንዳለብን ለመጠየቅ ተገደድን። ለመልካሙና “የህዝቦች አብሮ የመኖር አለኝታ” ስለሚባለው አንቀጽ 39!

የሶማሌ ብሄር አባል ናቸው። አቶ አብዱላሂ አብዱራሂም ይባላሉ። ዘጠነኛውን “የብሄር ብሄረሰቦች” ቀን አስመልክቶ አስተያየት እንዲሰጡ ተጋብዘው በቴሌቪዥን ብቅ አሉ “… አቅማችሁ ካደገ በኋላ፣ ልጆቻችሁን አስተምራችሁ አቅም ስታዳብሩ ለአንቀጽ 39 ትደርሱበታላችሁ…” እንዳሉዋቸው አቶ መለስን ጠቅሰው ተናገሩ። ትዝታቸው መሆኑ ነው።

ወዲያው አቶ መለስ በወቅቱ እንገነጠላለን ያሉትን የሶማሌ ህዝቦች ሰብስበው ሲናገሩ ታዩ።እንዲህ አሉ “አስራ ዘጠኝ ዓመት የታገልኩበት አላማ እንዳይቀለበስ እፈልጋለሁ። አይቀለበስም ብዬ ቃል ስገባ እናንተን ለመደለል አይደለም። ምክንያቱም ስለመብቱ ምን አልባትም ከናንተ በላይ አስባለሁ። ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም። ከልቤ ስለማምንበት ነው” ሌላ አስተያየት ሰጪ ተከተለ። ተከተለች። “አንቀጽ 39 ለዘላለም ይኑር” ተባለ።

“የኢትዮጵያዊነት ፋይዳው በጣም ጥልቅና መሰረታዊ ነው። 80 ሚሊዮን ህዝቦች አንድ ላይ ስናጨበጭብ እንደመጣለን።ተመጋጋቢ ኢኮኖሚ አለን። ለአገራችን ደህንነትም ሃይል ነው” ይህን ምርጥ አባባልም በተመሳሳይ ፕሮግራም የተደመጠው ከቀድሞው ጠ/ሚ አቶ መለስ አንደበት ነው። በዚህ አያበቃም።

“ተበጣጥሰን የምናገኘው ቴክኖሎጂ ተሰባስበን የተሻለ አይደለም። መሰባሰቡ ጠንካራ ነገር አለው። መሰባሰባችን /አንድነታችን/ የመንደር ንፋስ የሚጠራርገውና የሚበጣጥሰው አይደለም።ስሜት አይደለም። ኢትዮጵያዊነት ጠንካራ የሚሆነው ምክንያት ስላለው ነው” አንጀት የሚያርስ አባባል። ወርቅ ንግግር። ከዚያስ?

“ነጻ ኦሮሚያ” የሚሉ ሰልፈኞች ታዩ። መለስ መጡ። አዲስ አበባ እንደገቡ ሰሞን ነው። እንዲህ አሉ “እኛ ጦርነትን በቴሌቪዥን አናውቅም። እኛ ጦርነትን በወሬ አናውቅም። እኛ ጦርነትን በተቃጠሉ ቤቶች፣ በተጨፈጨፈ ህዝብ ነው የምናውቀው። ከእንግዲህ አንዋጋም። በቅቶናል። ሰልችቶናል። ከእንግዲህ አንዋጋም” በማለት የተናገሩትን አሞጋሾችን እየቀላቀለ ኢቲቪ ትውስታ አቃመሰን።

አቶ መለስ አማራ ናቸው፣ አቶ መለስ ሃረሪ ናቸው፤ አቶ መለስ ወላይታ ናቸው። አቶ መለስ ሶማሌ ናቸው። ወዘተ የሚሉ ሰዎች መለስን ባረኩ። የሶማሌ ክልል አስተያየት ሰጪ የአቶ መለስን ፎቶ ጸሃይ ሲመታው አይተው “ፎቶም ቢሆን መለስ እኮ ነው ጥላ አድርጉለት አልኩ” ሲሉ አሁንም ኢቲቪ አስደመጠ። የሃረሪው አስተያየት ሰጪ ከጭቆናው ብዛት ከምድረ ገጽ ሳይጠፉ አቶ መለስ እንደደረሱላቸው መሰከሩ። አቶ ኩማም ኦነግን እየረገሙ አንቀጽ 39 ዋጁ። ታላቅ ገጸ በረከት እንደሆነ ደጋግመው መሰከሩ። ይብቃን!!

“የብሄር ብሄረሰቦች” ቀን ሲከበር የመጻፍ፣ የመናገር፣ የመደራጀት፣ የመቃወም፣ ህዝብ በፈቀደው መንገድ እንዲደራጅ፣ ይህ ካልሆነ እስከመገንጠል መብት አለው የሚል የተጨመቀ ዓላማ እንዳለው በተደጋጋሚ ሰምተናል። ይህንን እየሰማን አማራው መፈናቀሉ ይነገረናል። ለዓመታት ከኖሩበት እየተሰደዱ ልመና ላይ መሆናቸውን ከበዓሉ ጋር የቀጥታ ስርጭት ሆኗል። ህጻናት ለችግር ተጋልጠዋል። አባት ከጎጆው ወጥቶ የቀን ሰራተኛ ለመሆን ተገዷል። ቤተሰብ ተበትኗል። የታሰሩ አሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው “እገሌን ደገፍክ” በሚል የፖለቲካ ቂም እንደሆነ ሰለባዎቹ ሲናገሩ እየሰማን ነው። ለዚህ ታላቅ ብስራት ኢቲቪ ጆሮ የለውም። “ብሄር ብሄረሰቦች” እኩልነትን የተጎናጸፉበትን ክብረ በአል በቀጥታ በማሰራጨት ስራ ተጠምዷል።

ብዙ ሺህ አስረኞች “ኦነግ ናችሁ” ተብለው በአመለካከታቸው ሳቢያ እየተሰቃዩ ነው። ቅንጅን በገንዘብ ደግፋችኋል የተባሉ ከስራና ከንግድ እንዲወጡ እየተደረገ ነው። በቀረጥና በእዳ ስም የተዘረሩና የቁም ሞት የሞቱ አሉ። ጠኔ የሚቆላቸው የበይ ተመልካቾች ችግር ከጓዳ አልፎ አደባባይ ውሏል። ሃሳብን በነጻ መግለጽ የሚቻል መስሏቸውና መብቱ የተፈጥሮም በመሆኑ የተናገሩ፣ የጻፉ፣ የተቹ፣ “አሸባሪ” ተብለው ተከርችመዋል። ስለ መብት መከበርና ስለ እምነት ነጻነት የሚጠይቁ በጋሪ የሚገፋ የክስ ፋይል ተከፍቶባቸው እስር ቤት እየተሰቃዩ ነው። እነዚህ ሁሉ ሰዎች በኢህአዴግ በራሱ ቋንቋ ብሔር የላቸውም? የህዝብ አካል አይደሉም? ይህ መሰረታዊ ችግር እያለ ከበሮ ይደለቃል። ለስርዓቱ የቀለም ማስዋቢያ እንዲሆን ከየብሄረሰብ የተውጣጡ አጊጠው ሲጨፍሩ ይስተዋላል። በብሄርም ደረጃ ወርደን እንነጋገር ከተባለ በተለይ አማራ ክልል ለወገኖቹ መሟገት ሲገባው ባህር ዳር ላይ አስረሽ ምቺው መጨፈሩ ያሳፍራል። ወገኑንና የሚምልለትን ህዝብ የማይሰበስብ ድርጅት!

መራገምና ማውገዝ ሰልችቶናል። የውግዘት መንገድ ለማንም እንደማይበጅ እናውቃለን። ውግዘት ለቀጣዩ ትውልድ መርዝ የመጋት ያህል መራር ውርስ ነው። ግን ምን እናድርግ? የምናመሰግነው አጣን። ማንን እናመስግን? እንዲሁ በቅዠትና በሚያደነቁር ፕሮፓጋንዳ ኖረን እንለፍ?

“ዝናውም፣ ክብሩም፣ ሃብቱም፣ ሁሉም ያልፋል። ጊዜም ከጥላችን ይልቅ ይበራል። ደጎች ላገራቸው፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለተተኪው ትውልድ መልካም ነገር አስቀምጠው ሲያልፉ በበጎ ሲታወሱ ይኖራሉ። የክፉ ታሪክና ልምድ ማጣቀሻ ከመሆን ለአገርና ለወገን መልካም ስራ ሰርቶ ማለፍ ያኮራል” ከአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ድረገጽ ላይ የተወሰደ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    December 13, 2012 07:05 am at 7:05 am

    ” ስለ አንቀፅ ፴፱ የምናመሰግነው ስለ ቀለሙ ብቻ ነው”
    *ሁሉም እና እያንዳንዱ ሆድ አደር የፈረሙትን የቀድሞ ፕሬዘዳንት ጨምሮ ሁሉም የፖለቲካ አቀንቃኞች የብሔር ቱልቱላ ነፊዎች አንቀፅ ፴፱ አንብቦ ቂጡን እየመታ ሲጨፍር ሲያስጨፍር ላንቃው እስኪታይ ሲቀሳፍቱ ነበር። አሁንም ያፋሽካሉ ያምታታሉ መች ያስተምራሉ? ሁሉም ዜጎች እንዳያነብቡ፣ እንዳይጠያየቁ፣እንዳይነጋገሩ፣እንዳይወያዩ፣እንዳይረዳዱ በክልልና በራሳቸው ቋንቋ ተብትበው አሰሯቸው አጭበርብረው እኛ ስለ አንተ ታሪክ እናውቅልሃለን አንተ ብቻ “ዝም ብለህ ሸክሽክ!” ብለው ሕዝቡን ጭራ አድርገውት የግል ሀብት አከማቹ! ሥልጣን አገኙ! ቤተሰባቸውን ባለሀብት, ባለዕውቀት አደረጉ! አንዲት ትግራይ ብቻ …ትግርኛ፣ አማርኛ፣ ጣሊያንኛ፣አረቢኛ፣ኦሮሚኛ፣ፈረንሳይኛ፣ቻይንኛ መናገር ሙሉ መብት አላት ሌላው በፌዴራሉ መሥሪያ ቤት የመቀጠር ባለሥልጣን የመሆን ዕድሉ ተከለለ። ዛሬ ቻይና ሕንድ አረብ ባለልጅ ሆነ ቀጥሎም የፌዴራሉ ከንቲባ የቻይና ልጅ እንጂ ጉራጌ,ደቡቡ, ኦሮሞ ወይም አማራ አይሆንም! ዛሬ በተግባር የታየው ከአማራው ክልል ተነጥቆ መሬት ተሠጠኝ የሚለው ኦሮሞ ሕንድ፣፣አረብ፣ቻይናና ቱርክ መሬቱን ወስዶለታል። አማራው ፷ ሺህ ወጣት የሚይዝ ቂጡን የሚያለፋበት አፉን ከፍቶ የሚውልበት ስታዲየም ተሠርቶለታል፣በቀን በቀን ዘፈን ያወጣል ይሸጣል ሱሪውን ዝቅ አድርጎ ይንሳፈፋል። ጉራጌ ከንግድ ዓለም በጠረባ ተመቶ በዝረራ ወድቋል። ወይ አለህ እያለ ያኗኑራል?። ደቡቡ አካባቢውን ጥሎ ደኑን አቃጥሎ ቀዬውን አስረክቦ በቁም እሥር ባዕድ ሲበላ አይኑ ይቁለጨለጫል።ያለቅሳል!!

    “ኢፈርት’በኢንዱስትሪ ዘርፍ ከአፍሪካ አንደኛ ሲሆን የተመሠረተበት ገንዘብ ሳይታወቅ ዓመታዊ ገቢው ሳይታይ ሳይጠና ለሥርዓቱ ማስቀጠያ ያገባውን ድጎማ እንደመንግስት የገቢ ቀረጥ ጉራ ይቸረቸርበታል?? የወያኔ ወታደር የራሱ አስተዳደር ኢኮኖሚና የራሱን መንግስት መሥርቷል። ትግራይ በመተሳሰብ እና በመፈቃቀድ ላይ በተመሠረተ የህግ መንግስቱ አብሮ መኖር ከወሎ እና ከጎንደር መሬት ይወስዳል። ባድሜን ፹ ሺህ የመሃል ሀገሩን የድሃ ልጅ ሆን ብሎ አስፈጅቶበት በነፃ መሬቱን አስረከበ። የአሰብን ወደብ ስንጠይቅ አሸባሪዎች የደርግ ቡችሎች ትምክተኞች ስንባል እነሱ በፈለጉ ጊዜ የፈለጉትን መሬት ለጎረቤት ሀገር በመስጠት የእህል ምርት ወደ መሀል ሀገር እንዳይገባ አፍነው ግረቤት ሀገር በርካሽ ያሸጣል፣የመሀል ሀገር መብራት በፈረቃ ሲያበራ ኬንያ,ሱማልያ, ጅቡቲ,ሱዳን ሌሊቱን የጎጆ እንዱስትሪውን ሥራ አጧጡፈውታል፤ አሰፈላጊ ሆኖ ሲገኝ የሰሊጥ ምርት ወስደው ሽንኩርት ይልኩልናል።አቤት ሀገር አቤት ሕገ-መንግስት አልቀረብንም።ማፈሪያ ሁሉ በለው!
    ለመሆኑ ይህ ሥርዓት የማን እና ለማን ነው? ህገመንግስቱ የፈታው ችግር አለ? ወይስ አሠረ? የእኛ ምሁር ዶ/ር፣ ፐሮፌሰር፣ ኢንጂነር፣ ይህንን በቲቪ እና በራዲዮ ተለጥፎ ወሬ ቢተው ምን አለበት? በዚህ ድሃ,የዋህ,ታጋሽ,ጨዋ ሕዝብ ባትሳለቁበት ባታላግጡበት ምን አለ??ሕገ መንግስቱ የአንተ አደለም! አይሆንም! ይህ ሕገ- መንግስት ከመፃፉና ከመፅደቁ በፊት ሀገሪቱ ላይ ሰው እንደነበር እውቅና አይሰጥም አንብብ ዓይንህን ግለጥ በለው!! ከሀገረ ካናዳ

    Reply
  2. Hager says

    December 24, 2012 08:38 pm at 8:38 pm

    There is no means to end this suffering, nothing but war . So if we love our country, if we care for coming generation, we should fight fiercely this brutalism. Now if we say we should fight, some so called” Peace Lover” try to deceive us as War is evil.. By the way “All human knows War is evil but TPLF has not given us no choice. So war ,in our situation, is the lesser evil, otherwise we let our people to enslave by these Racist. I am happy when I see some people start recognize this…it is bitter but it is truth. So let us focus on supporting the fight against TPLF in all forms such as Economically, Psychologically, and so on
    ..Let us reclaim our birthright.

    Reply
  3. ababi says

    January 28, 2013 11:33 pm at 11:33 pm

    This is a secret divide and rule agenda of woyane.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule