• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድነት ስየን ሊሰርዝ ወይም ሊያስጠነቅቅ ይችላል

December 14, 2012 12:06 pm by Editor 1 Comment

በነባር አመራሮች ሲንከባለል የኖረው “የቅንጅት ወራሽ” አንድነት ፓርቲ ኃላፊነቱንና አመራሩን ለተተኪ ሳያስረክብ መቆየቱ በአብዛኛው ትችት ሲያሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተለይም አቶ ስየ አብርሃ ፓርቲውን በተቀላቀሉ ማግስት በከፍተኛ ኃላፊነት መሰየማቸው አልተወደደለትም ነበር፡፡ በአንድነት ፓርቲ ውስጥም እስከመከፋፈል የዘለቀ ልዩነት መፍጠሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡

አሁን የረገበ የሚመስለው የፓርቲው የውስጥ ልዩነት፤ በወቅቱ “ዝም አንልም፤ መርህ ይከበር” የሚሉት ኃይሎች የወሰዷቸውን ጽንፈኛ አቋሞች ብዙዎች የሚደግፉት ባይሆኑም ያነሱትን ጥያቄ አግባብነት ግን ይቀበላሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊመንበር የነበሩት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም “እኛ የማማከር አገልግሎት መስጠት አለብን፤ አመራሩን መያዝ ያለበት አዲሱ ትውልድ ነው” በማለት ራሳቸውን በቅሬታ ከፓርቲው ማግለላቸው ይታወሳል፡፡

በአሁኑ ሰዓት አሜሪካ የሚገኙት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳም ከፓርቲው ጋር ያላቸው ግንኙነት በይፋ በሚታወቅ ደረጃ ላይ አይገኝም፡፡ እርሳቸውን ተከትለው ወደ አሜሪካ የመጡት አቶ ስየም በተየያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በፓርቲው ስም ንግግር ሲያደርጉና የራሳቸው እምነት ሲያንጸባርቁ የሚታዩትን ያህል ወ/ት ብርቱካን ከአንድነት ጋር በተቆራኘ ጉዳይ መድረክ ላይ አለመታየታቸው ከፓርቲው ጋር ያላቸውን ግኑኘነት ግልጽ እንዳልሆነ አመላካች ነው፡፡ ወ/ት ብርቱካን ወደ አሜሪካ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በአጠቃላይ ከትግሉ ጎራ እንዳልራቁ ቢናገሩም ሲመሩ የነበሩትን ፓርቲ በተመለከተ ዝምታን መምረጣቸው የዳያስፖራውን የፖለቲካ ትግል ይመራሉ ብሎ ተስፋ በጣለባቸው ደጋፊያቸው ዘንድ ይፋ ያልወጣ ግን በብዛት ያነጋገረ ጉዳይ ነው፡፡

እነዚህ ሁሉ በፓርቲው ላይ ዙሪያ በሚነሱበት ወቅት ፓርቲው ራሱን ለሹምሽር ማዘጋጀቱ በሚደረገው ሹምሽርም አቶ ስየን ጨምሮ ከም/ቤት የሚባረሩ እንዳሉ ዘወትር ረቡዕ ከአዲስአበባ የሚታተመው ሰንደቅ ጋዜጣ አዲስ ወሬ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡

ወ/ት ብርቱካን ሊ/መንበር ሆነው መመረጣቸውን በግልጽ የተቃወሙትና ለበርካታ ጊዜያት ራሳቸውን ከፓርቲው አግልለው ቆይተው የተመለሱትና ከፓርቲው “በክብር ተሰናብተው” የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው እንደገና ወደ አመራር እንደሚመጡ ሰንደቅ በዘገባው ፍንጭ ሰጥቷል፡፡

በፓርቲው እውቅና ለአንድ ዓመት ለትምህርት ወደ አሜሪካ የሄዱት አቶ ስየ ትምህርታቸውን ባለፈው ግንቦት አካባቢ ቢያጠናቅቁም እስካሁን ወደ አገር ቤት አልተመለሱም፡፡ ሆኖም በቅርቡ የመድረክ አመራሮች በአሜሪካ ባካሄዱት ስብሰባዎች ላይ አቶ ስየ በአጋርነት ሲሳተፉ ቢቆዩም በአንድነት ፓርቲ ም/ቤት ስብሰባ ላይ በተደጋጋሚ አለመገኘታቸው በርካታዎችን ከማሳሰብ አልፎ ቅሬታንም እንደፈጠረ ሰንደቅ ዘግቧል፡፡ በመሆኑም ሁኔታው ሕገ-ደንብ የመጣስ ሆኖ በመገኘቱ ከም/ቤት አባልነት እንደሚያሰርዝ ሰንደቅ የቅርብ ምንጮቹን ጠቅሶ አስታውቋል፡፡ ሆኖም የመጨረሻው ውሳኔ እሁድ የሚታወቅ ሲሆን ይህም ሰብሳቢው በሚያቀርቡት ሪፖርት ላይ የሚንተራስ እንደሆነ ጨምሮ ዘግቧል፡፡

ሁኔታው የሕገ-ደንብ ሳይሆን በፓርቲው ውስጥ ገና ከጅምሩ ያልተቋጨ የሥልጣን ሽኩቻና ያለመተማመን ነጸብራቅ ነው የሚሉ ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው አስተያየት ሰጪዎች የእሁዱ ውሳኔ በፓርቲው ላይ መጠነኛና ጊዜያዊ መልክን የመቀየር ለውጥን እንጂ ተፈላጊውን ተሃድሶ እንደማያመጣ ይናገራሉ፡፡ በተለይ በቅርቡ ሊ/መንበሩ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ “የግል እምነቴ ነው” በማለት ለውይይት መነሻ ባቀረቡት ጽሁፍ ተሃድሶ የማድረግን አስፈላጊነት በማጉላትና እስካሁንም ይህ አለመደረጉ ተፈላጊውን ለውጥ በአገራችን ላይ ሊያመጣ እንዳላስቻለ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ሆኖም ተሃድሶው እንዴትና ከየት እንደሚጀመር አልተናገሩም፡፡ በካቢኔ ሹምሽርነት የተጠራው የእሁዱ ስብሰባም የዚህ ተሃድሶ መጀመሪያ ይሁን እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር የለም፡፡

በቅርቡ ቀድሞ የቅንጅት እንዲሁም የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊ በሆኑ የተቋቋመው ሰማያዊ ፓርቲ ወደፊት ምን ያህል እንደሚዘልቅና የት ድረስ እንደሚራመድ ባይታወቅም እያካሄደ ያለው ያልተለመደ የፖለቲካ አሠራር የብዙዎችን ትኩረት እየሳበ የመጣ ሆኗል፡፡ የቀድሞ የፖለቲካ አመራሮችን “በአማካሪነት” በማቀፍ በተለይ ፓርቲው በወጣት አመራሮች የተቋቋመና እየተመራ ያለ መሆኑ በአገር ውስጥ ያሉት ነባር ፓርቲዎች ያላስመዘገቡትን ውጤትና ያላመጡትን ተሃድሶ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ እየተገበረና እየሄደ ያለው መንገድ በሌሎች ዘንድ የተሃድሶን አስፈላጊነት እንዲያስቡ ያስገደደ ነው የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡

(ሐብታሙ ሂካ ያምቦ፤ Habtamu Hiikaa Yaamboo; habtamu@goolgule.com)

የሰንደቅ ሙሉ ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. dershaye says

    December 15, 2012 08:30 am at 8:30 am

    you are doing nice keep up!!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule