• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድነት ስየን ሊሰርዝ ወይም ሊያስጠነቅቅ ይችላል

December 14, 2012 12:06 pm by Editor 1 Comment

በነባር አመራሮች ሲንከባለል የኖረው “የቅንጅት ወራሽ” አንድነት ፓርቲ ኃላፊነቱንና አመራሩን ለተተኪ ሳያስረክብ መቆየቱ በአብዛኛው ትችት ሲያሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተለይም አቶ ስየ አብርሃ ፓርቲውን በተቀላቀሉ ማግስት በከፍተኛ ኃላፊነት መሰየማቸው አልተወደደለትም ነበር፡፡ በአንድነት ፓርቲ ውስጥም እስከመከፋፈል የዘለቀ ልዩነት መፍጠሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡

አሁን የረገበ የሚመስለው የፓርቲው የውስጥ ልዩነት፤ በወቅቱ “ዝም አንልም፤ መርህ ይከበር” የሚሉት ኃይሎች የወሰዷቸውን ጽንፈኛ አቋሞች ብዙዎች የሚደግፉት ባይሆኑም ያነሱትን ጥያቄ አግባብነት ግን ይቀበላሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊመንበር የነበሩት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም “እኛ የማማከር አገልግሎት መስጠት አለብን፤ አመራሩን መያዝ ያለበት አዲሱ ትውልድ ነው” በማለት ራሳቸውን በቅሬታ ከፓርቲው ማግለላቸው ይታወሳል፡፡

በአሁኑ ሰዓት አሜሪካ የሚገኙት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳም ከፓርቲው ጋር ያላቸው ግንኙነት በይፋ በሚታወቅ ደረጃ ላይ አይገኝም፡፡ እርሳቸውን ተከትለው ወደ አሜሪካ የመጡት አቶ ስየም በተየያዩ የአሜሪካ ግዛቶች በፓርቲው ስም ንግግር ሲያደርጉና የራሳቸው እምነት ሲያንጸባርቁ የሚታዩትን ያህል ወ/ት ብርቱካን ከአንድነት ጋር በተቆራኘ ጉዳይ መድረክ ላይ አለመታየታቸው ከፓርቲው ጋር ያላቸውን ግኑኘነት ግልጽ እንዳልሆነ አመላካች ነው፡፡ ወ/ት ብርቱካን ወደ አሜሪካ ከመጡበት ጊዜ ጀምሮ በአጠቃላይ ከትግሉ ጎራ እንዳልራቁ ቢናገሩም ሲመሩ የነበሩትን ፓርቲ በተመለከተ ዝምታን መምረጣቸው የዳያስፖራውን የፖለቲካ ትግል ይመራሉ ብሎ ተስፋ በጣለባቸው ደጋፊያቸው ዘንድ ይፋ ያልወጣ ግን በብዛት ያነጋገረ ጉዳይ ነው፡፡

እነዚህ ሁሉ በፓርቲው ላይ ዙሪያ በሚነሱበት ወቅት ፓርቲው ራሱን ለሹምሽር ማዘጋጀቱ በሚደረገው ሹምሽርም አቶ ስየን ጨምሮ ከም/ቤት የሚባረሩ እንዳሉ ዘወትር ረቡዕ ከአዲስአበባ የሚታተመው ሰንደቅ ጋዜጣ አዲስ ወሬ ይዞ ብቅ ብሏል፡፡

ወ/ት ብርቱካን ሊ/መንበር ሆነው መመረጣቸውን በግልጽ የተቃወሙትና ለበርካታ ጊዜያት ራሳቸውን ከፓርቲው አግልለው ቆይተው የተመለሱትና ከፓርቲው “በክብር ተሰናብተው” የነበሩት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው እንደገና ወደ አመራር እንደሚመጡ ሰንደቅ በዘገባው ፍንጭ ሰጥቷል፡፡

በፓርቲው እውቅና ለአንድ ዓመት ለትምህርት ወደ አሜሪካ የሄዱት አቶ ስየ ትምህርታቸውን ባለፈው ግንቦት አካባቢ ቢያጠናቅቁም እስካሁን ወደ አገር ቤት አልተመለሱም፡፡ ሆኖም በቅርቡ የመድረክ አመራሮች በአሜሪካ ባካሄዱት ስብሰባዎች ላይ አቶ ስየ በአጋርነት ሲሳተፉ ቢቆዩም በአንድነት ፓርቲ ም/ቤት ስብሰባ ላይ በተደጋጋሚ አለመገኘታቸው በርካታዎችን ከማሳሰብ አልፎ ቅሬታንም እንደፈጠረ ሰንደቅ ዘግቧል፡፡ በመሆኑም ሁኔታው ሕገ-ደንብ የመጣስ ሆኖ በመገኘቱ ከም/ቤት አባልነት እንደሚያሰርዝ ሰንደቅ የቅርብ ምንጮቹን ጠቅሶ አስታውቋል፡፡ ሆኖም የመጨረሻው ውሳኔ እሁድ የሚታወቅ ሲሆን ይህም ሰብሳቢው በሚያቀርቡት ሪፖርት ላይ የሚንተራስ እንደሆነ ጨምሮ ዘግቧል፡፡

ሁኔታው የሕገ-ደንብ ሳይሆን በፓርቲው ውስጥ ገና ከጅምሩ ያልተቋጨ የሥልጣን ሽኩቻና ያለመተማመን ነጸብራቅ ነው የሚሉ ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው አስተያየት ሰጪዎች የእሁዱ ውሳኔ በፓርቲው ላይ መጠነኛና ጊዜያዊ መልክን የመቀየር ለውጥን እንጂ ተፈላጊውን ተሃድሶ እንደማያመጣ ይናገራሉ፡፡ በተለይ በቅርቡ ሊ/መንበሩ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ “የግል እምነቴ ነው” በማለት ለውይይት መነሻ ባቀረቡት ጽሁፍ ተሃድሶ የማድረግን አስፈላጊነት በማጉላትና እስካሁንም ይህ አለመደረጉ ተፈላጊውን ለውጥ በአገራችን ላይ ሊያመጣ እንዳላስቻለ መናገራቸው ይታወሳል፡፡ ሆኖም ተሃድሶው እንዴትና ከየት እንደሚጀመር አልተናገሩም፡፡ በካቢኔ ሹምሽርነት የተጠራው የእሁዱ ስብሰባም የዚህ ተሃድሶ መጀመሪያ ይሁን እስካሁን በግልጽ የታወቀ ነገር የለም፡፡

በቅርቡ ቀድሞ የቅንጅት እንዲሁም የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊ በሆኑ የተቋቋመው ሰማያዊ ፓርቲ ወደፊት ምን ያህል እንደሚዘልቅና የት ድረስ እንደሚራመድ ባይታወቅም እያካሄደ ያለው ያልተለመደ የፖለቲካ አሠራር የብዙዎችን ትኩረት እየሳበ የመጣ ሆኗል፡፡ የቀድሞ የፖለቲካ አመራሮችን “በአማካሪነት” በማቀፍ በተለይ ፓርቲው በወጣት አመራሮች የተቋቋመና እየተመራ ያለ መሆኑ በአገር ውስጥ ያሉት ነባር ፓርቲዎች ያላስመዘገቡትን ውጤትና ያላመጡትን ተሃድሶ ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ እየተገበረና እየሄደ ያለው መንገድ በሌሎች ዘንድ የተሃድሶን አስፈላጊነት እንዲያስቡ ያስገደደ ነው የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡

(ሐብታሙ ሂካ ያምቦ፤ Habtamu Hiikaa Yaamboo; habtamu@goolgule.com)

የሰንደቅ ሙሉ ዘገባ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. dershaye says

    December 15, 2012 08:30 am at 8:30 am

    you are doing nice keep up!!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule