• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወርቁ ካዶላ የሚያጌጥበት ሌላ!

December 11, 2012 12:26 pm by Editor 1 Comment

ከሁለት ወር በፊት “የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!! ወርቃችን እንዴት አላሙዲ እጅ ገባ?” በሚል ርዕስ ላቀረብነው ጽሁፍ የድረገጻችን የዘወትር ተሳታፊ አሥራደው ከፈረንሣይ “የአላሙዲ ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አዶላ ኑሮ በጭንቅ!” በሚል ርዕስ የመጀመሪያውን ክፍል ጽሁፋቸውን አስነብበውን ነበር፡፡ በዚህ የክፍል ሁለት ጽሁፋቸው ደግሞ ባለፈው ያነሱትን ጉዳይ በመዳሰስ እንደሚከተለው አቅርበውታል፡፡

ወርቁ ካዶላ የሚያጌጥበት ሌላ!

በመጀመሪያው ክፍል መጣጥፌ፤ ቡችላው ማነው? ለምንስ ቡችላ ተባለ? በሚል ጥያቄ ነበር የተለየኋችሁ :: የወርቁ ቡችላ በምስሉ የሚያዩትን ይመስላል፤ ቡችላ የተባለበት ምክንያት ተለቅ ያለ የወርቅ ፍንካች በመሆኑ ነው::

እናም:

አዶላ ወርቅ ነው፤ አዶላ ማርና ወተት ነው፤ አዶላ የዱር አራዊትና አዕዋፍ በአንድላይ ሆነው የሚዘምሩበት፤ ዛፎች እጅ ለእጅ ተያይዘው በንፋስ አጃቢነት ጎንበስ ቀና እያሉ የሚሰግዱበት፤ ሰማይና ምድር መሳሳማቸውን ሳያበቁ በማለዳ፤ ጉሬዛዎች በዛፎች ላይ ሆነው ከወዲያ ወዲህ እየተንጠላጠሉ፤ በወፎች ዝማሬ ታጅበው፤ ከደኑ መሃል በሚፈልቀው ውብ የዕጣን ሽታ እየታጠኑ፤ ለፈጣሪያቸው ምስጋናውን በሽብሸባ የሚያቀርቡበት፤ ምድራዊ ገነት ነው::

አዶላ እንደሚወራው ምድራዊ ገሃነም አይደለም፤ ይልቁንም የገብስ ቆሎውን እያዘገነ፤ የገተሜ ጠጁን በብርሌ እያንቆረቆረ፤ በቆራሰማ የታጠነ ወተቱን እያስጎነጨ፤ እጅ የሚያስቆረጥም ክትፎውን በቆጮ ጠቅሎ እያጎረሰ፤ በአትክልትና ፍራፍሬው ሆድን እያንሸራሸረ፤ ለዛ ያላቸው ገጠመኞቹን በጆሮ እያንቆረቆረ የሚያስተናግድ ደግ ሕዝብና ምድር እንጂ!

አዶላ ፍቅር ነው፤ አንዱ ቢያጣ ከሌላው ተካፍሎ የሚበላበት፤ ሰው ለሰው የሚኖርበት፤ ሰው ሰው የሚሸት የሰው ልጆች ጠረን !

ደሞም አዶላ ተስፋ ነው፤ ዛሬ ቢያጡ ነገ ለማግኘት ተስፋ ሳይቆርጡ፤ የሕይወት ዑደቱ እንዳይቋረጥ፤ ዛሬን በነገ ተክቶ የወደፊቱን ሕይወት ለመኖር፤ የሚያልሙበት የተስፋ ምድር ::
አዶላ መሬቱ ዳቦ ነው ይገመጣል፤ ውሃው ጠበል ነው ይፈውሳል፤ አየሩ መንፈስ ነው፤ ሁሉንም በፍቅር ሰንሰለት የማስተሳሰር ሃይል ያለው!

አቦ የትም ተወለድ፤ ወርቅ ከእናት አገርህ ኢትዮጵያ ማሕጸን በምጥ የሚወለድበትን፤ የአዶላን ምድር ሳታይ ግን አትሙት!!

ሼክ አላሙዲ የአዶላን የተፈጥሮ ውበት ለማድነቅና ለመጠበቅ አልመጣም፤ በተቃራኒው ይህን ውብ የሆነ የተፈጥሮ ሃብት ለማውደም፤ ነዋሪዎቹን ከይዞታቸው በማፈናቀል ወርቅ ለማግበስበስና በመርዛማ ኬሚካሎች የአካባቢውን ውሃ ለመበከል እንጂ::

  • ለመሆኑ ከአላሙዲ በስተጀርባ ያለውና የኢትዮጵያን ሕዝብ ሃብት እየዘረፈ የሚያዘርፈው ረጅሙ እጅ የማነው?
  • የኢትዮጵያ ተማሪዎች «መሬት ለአራሹ» የሚል መፈክራቸውን አንግበው የፊውዳሉን ሥርዓት ሲታገሉ አላሙዲ የት ነበር ?
  • በ17 አመታት የወታደር አስተዳደር ዘመን፤ ተማሪው፤ ገበሬውና ሠራተኛው በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ሰፊ ሕዝብ በጥይት ሲቆላ አላሙዲ የት ነበር ?
  • በዘመነ ወያኔ አላሙዲ እንዴት ? በማን ? ለምን ? ተጎትቶ ወይም ሰተት ብሎ ሊገባ ቻለ ?
  • የአዶላን የወርቅ ማዕድን ሁለት እግሮቹን አንፈራጦ እንዲይዝ በሩን ወለል አድርገው የከፈቱለት እነማን ናቸው ? ለምን ?
  • አላሙዲ የጉጂ፤ የደራሳና ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍል መተው ኑሯቸውን በአዶላ የወርቅ ፍለጋና በእርሻ ሥራ የተሰማሩ ወገኖቻችንን የማፈናቀል መብት ማን ሰጠው ?

ሕዝብ ለነዚህ ጥያቄዎች በአስቸኳይ መልስ ይፈልጋል፤ መልስ ሊሰጠውም የግድ ይላል !

«ጥቂት ቆሎ ይዘህ ከአሻሮ ተጠጋ » እንዲሉ፤

  • አላሙዲ ዘፋኝ ሳይሆን ዘፋኞችን አጅቦ መድረክ ላይ ወጥቶ ሲኩነሰነስ፤ ምሥጢሩ ያልገባው ሕዝባችን አጨበጨበ፤ እሱ ግን ከመጋረጃው በስተጀርባ ሆኖ ሥራውን መሥራት ጀመረ ::
  • አላሙዲ እስፖርተኛ ሳይሆን እስፖርተኞችን አጅቦ አብዶ (ፊንታ) በመሥራት ብዙ የከተማ መሬቶችና የሕዝብ ንብረት የነበሩ የማምረቻ መሥሪያ ቤቶችን ወደ ግል ንብረትነት ማዘዋወር ፕራቫታይዜሽን (privatization) በሚል ሸፍጥ: ዘርፎ በማዘረፊያ ስውር ጫረታ፤ ከንግድ ባንክ በወሰደው ብድር በሾኬ ጠልፎ በእጁ አስገባ፤ ብድሩም እስካሁን አልተከፈለም ::
  • በቅርቡ ገበሬዎችን እያፈናቀለ መሬት አልባ በማድረግ ለም መሬት በርካሽ ሸመተ፤
  • ከበፊቱ የሸፍጥ ስውር ጨረታ ተርፈው የነበሩ የሕዝብ የማምረቻ ድርጅቶችና፤ የእርሻ ማህበራት ድርጅቶችን፤ ሳንቲም ከኪሱ ሳያወጣ አሁንም ከንግድ ባንክ በተሰጠ ብድር አግበሰበሰ…ወዘተ

ላለው ይጨመርለታል ለሌለው ያቺው የሌለችው ትወሰድበታለች የምትለው አዲሷ የወያኔ ፈሊጥ ይሏችኋል ይቺ ናት !

የአላሙዲ እጅ ከአገርቤትም አልፎ እስከ አሜሪካን ድረስ በመሻገር፤ በአሜሪካን አገር በየዓመቱ የሚደረገውን የኢትዮጵያውያን የእስፖርት ውድድር ሳይቀር፤ ከአዶላ በሚዝቀው ወርቅ ዶላር መንዝሮ ጥቂት ሆድ አደሮችን በመግዛት ያደረገውን ጣልቃ ገብነት ያስታውሷል ::

አላሙዲ ከአዶላ በሚዘርፈው የወርቅ ሽያጭ፤ ለሆድ አደሮች ዶላር በመበተን፤ የአገር ወዳድ ዜጎችን የማሰብ ነፃነት ለማፈንና፤ የብዕሮቻችንን ልሳን ለመዝጋት፤ እንደማይተኛ ብናውቅም፤ የቆምንበት የማዕዘን ድንጋይ ሃቅ በመሆኑ ከዕምነታችን ንቅንቅ አያደርገንም::

ሕሊናችንን እያስራብን፤ ሆዳችንን ለመሙላት ስንል ብቻ፤ አገር የምንሸጥና በወገኖቻችን ዕንባ ገላችንን የምንታጠብ ከርሳሞች አይደለንም ::

አላሙዲ በብዙ ቶን ከሚዝቀው የአዶላ ወርቅ መሃል፤ በማንኪያ ቆንጥሮ፤ ጥቂት ዘፋኞችን፤ እስፖርተኞችንና ጋዜጠኞችን (ያውም ሊሞቱ ከተቃረቡ በኋላ) ፤ስሙን በዜና ማሰራጫዎች ለማስጠራት ሲል፤ አሳከምኩ ቢለን: ባይገርመን አይደንቀንም :: ፈረንጆች «L’arbre qui cache la foret»  (አንዱ ዛፍ ደኑን ሙሉ ሸፈነው) እንዲሉ፤   ስውር ዘረፋውን ለመሸፈን የተጠቀመበት የተቀደደ የሱቲ ጨርቅ ነው ::

ለመሆኑ ሼክ አላሙዲ፤

  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ጤንነት አስጨንቆት፤ የትኛውን ሆስፒታልና ጤና ጣቢያ አሠራ?
  • የኢትዮጵያ ሕዝብ ልጆች አለመማር አስቆጭቶት የትኛውን ት/ ቤት፤ የትኛውን ኮሌጅ፤ የትኛውን ዩኒቨርስቲ አሠርቶ የድሃ ልጆች እንዲማሩ አደረገ?
  • እራሱና ሌሎች ድንበር ዘለል ከበርቴዎች ላፈናቀሏቸው ብዙ ወገኖቻችን የትኛውን የመጠለያ ጣሚያ አሠርቶ እንዲጠለሉ አደረገ?
  • የአንድ አገር ትልቁ ሃብቷ ሕዝቧ መሆኑ እየታወቀ ወያኔ ሕፃናትን በጉዲፈቻ እያሳበበ ሲሸጥ፤ በመቆጨት አይሆንም ብሎ የትኛውን የሕፃናት መጠጊያ አሠራ?
  • ወያኔ አደገኛ ቦዘኔ፤ እያለ ለሚሰድባቸው ወጣት የጎዳና ተዳዳሪ ወገኖቻችን የቱን መጠለያ ሠርቶ እንዲጠለሉ አደረገ ?
  • ወያኔ ቤታቸውን እያፈረሰ ቀን ለሃሩር፤ ማታ ለብርድ፤ የዳረጋቸውን አዛውንት እናቶች፤ አባቶችና ሕፃናት መች ዞር ብሎ አያቸው ?

ይልቁንም ሕዝባችን ከአላሙዲ የተረፈው፤

  • ለም የእርሻ መሬቶችን እየነጠቀ ገበሬዎችን ማፈናቀል
  • የደን ምንጠራ፤ የአራዊትና የአእዋፍ ውድመት
  • በመርዛማ ኬሚካል የአካባቢውን ውሃ መበከል
  • የተዛባ የአየር ጠባይ ማስከተልና
  • የወርቅ ዘረፋ ሲሆኑ:

ከዛሬ 5 እና 3 ዓመት በፊት የ1 ኪ.ግ. ወርቅ ዋጋ 14,000 እሮ ሲሆን ዛሬ የወርቅ ዋጋ በአስር  እጥፍ ጨምሮ 1 ኪ.ግ. ወርቅ በ 140,000 እሮ ይሸጣል:: እንግዲህ አላሙዲ ከአዶላ የወርቅ ማዕድን በብዙ ቶን የሚቆጠር ወርቅ ስለሚዝቅ የዘረፋውን መጠን አስቡት!

ይህን ያህል መጠነ ሰፊ ዘረፋ ሲያካሂድ ለአካባቢው ሕዝብ:

  • የትኛውን ሆስፒታልና ጤና ጣቢያ አሠራ?
  • የትኛውን ት/ ቤት፤ ኮሊጅ፤ ዩኒቨርስቲ አሠርቶ የአካባቢው ልጆች እንዲማሩ አደረገ?
  • እራሱ ላፈናቀላቸው ብዙ ወገኖቻችን የትኛውን የመጠለያ ጣሚያ ሠርቶ እንዲጠጉ አደረገ ?
  • የትኛውን የንጹህ ውሃ መጠጥ መስመር ዘረጋ ?
  • የትኞቹን ለአካባቢው መጣኝ የሆኑ መንገዶችን ሠራ ? …ወዘተ.

ተጠያቂነት የሌለበት የአዶላ ወርቅ የሚዘረፈውስ እስከመቼ ነው ?

አላሙዲ በወርቅ ሲያጌጥ፤ ለገዛ ወርቁ ባዳ የሆነው ጉጂ በመዳብ ያጌጣል! የማይደረገው ሁሉ የሚደረግበት ዘመነ ግርቢጥ !

ማስታወሻነቷ
ለክብረመንግሥት፤ ለኦዶ ሻኪሶ፤ ለቴፒ፤ ለመጋዶ፤ ለቦሬ፤ ለሃዲማ፤ ለኡላኡሎ፤ ለለገደንቢና በአካባቢው በኢትዮጵያዊነታቸው ኮርተው ለሚኖሩ ሕብረ ብሄር ወገኖቼ በሙሉ::

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ! ኢትዮጵያ በተባበሩ ልጆቿ ክንድ ክብሯ ይመለሳል!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    December 13, 2012 01:40 am at 1:40 am

    Keep it up looters and killers will face justice sooner of later.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule