በሃገራችን በሁለት የከተማ አስተዳደሮች እና በአስር ክልሎች ተከፋፍላ ትተዳደራለች። ከአስሩ ክልሎች ውስጥ ከኦሮሚያ ክልል በቀር ዘጠኙ ክልሎች ከሞላ ጎደል አንፃራዊ ሰላም ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ሆኖም እነዚህ ዘጠኝ ክልሎችም አለፍ አለፍ ብሎ የፀጥታ መደፍረስ፣ ዘውግ ተኮር ግጭት፣ የባለስልጣናትን ሞት የጨመረ ፖለቲካዊ ምስቅልቅል ውስጥ ገብተው ያውቃሉ፤ ወደፊትም እንዲህ ያለ ነገር ሊገጥማቸው ይችላል። ክልሎቹ የገጠማቸውን ፈተና ጠቅልሎ ማጥፋት አይቻልምና በአጭር ጊዜ ውስጥ ችግሩ እንዲቃለል ግን አደርገዋል። ይህ የሆነው በዋናነት በክልሎቹ አመራሮች ኢትዮጵያን የማዳን ቁርጠኝነት ነው። እነዚህ ክልሎች ኢትዮጵያን ለማዳን የሚሰሩት የዘውጋቸው ሰው “ስልጣን በቃኝ” እስከሚል ዙፋን ላይ ተቀምጦ ስለኖረ ወይም የህዝባቸው ጥያቄም ሙሉ በሙሉ ስለተመለሰ አለያም በክልላቸው ሁሉ ሙሉ ሁሉ ዝግጁ … [Read more...] about ሺቅዳ ሺመልስ፤ “ኦሮሞ ኦሮሞን አይገድልም” የሚለው አባባል “ዲና ነፍጠኛን” ግደል ማለት ነው!
Archives for August 2020
“የጥላቻው ምንጭ … ፖለቲከኞች፣ ብሔረተኞች፣ የጥላቻ ሰለባዎችና ጽንፈኞች የሚተፉት መርዝ ነው” ኦባንግ
“በኦሮሚያ ክልል በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት ከሰውነት፣ አብሮነትና ኢትዮጵያዊነት ይልቅ በሃሰተኛ ትርክትና በማንነት ጥላቻ ላይ ለበርካታ ዓመታት ሲሰራ የነበረ ስራ ውጤት ነው፤ ሊወገዝ የሚገባው የከፋ ድርጊት ነው ሲሉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ ኦባንግ ሜቶ ተናገሩ። በኢትዮጵያዊነትና ሰብዓዊነት ላይ የሚሰሩ ድርጅችን በማቋቋም የሚንቀሳቀሱት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አቶ አባንግ ሜቶ ከሰሞኑ በዝዋይና ሻሸመኔ ተዘዋውረው ጉዳት የደረሰባቸውን ግለሰቦች አነጋግረዋል። ከጉብኝታቸው መልስ ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታም ሰኔ 22 ሌሊት ጀምሮ በተፈጠረው ጥፋት የተጎዱ የ17 ግለሰቦችን ቃል መቀበላቸውን ተናግረዋል። በተፈጸመው ድርጊት የደረሰው ጉዳት ልብ የሚነካ፣ በኢትዮጵያ ታሪክ ይደረጋል ተብሎ የማይጠበቅ አሰቃቂ አገዳድል የተፈጸመበት አሳዛኝ ክስተት ነው … [Read more...] about “የጥላቻው ምንጭ … ፖለቲከኞች፣ ብሔረተኞች፣ የጥላቻ ሰለባዎችና ጽንፈኞች የሚተፉት መርዝ ነው” ኦባንግ
“ራሴን እንዳጠፋ ይፈቀድልኝ” በሃጫሉ ግድያ ተጠርጣሪው ጥላሁን
በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ወንጀሉን መፈፀሙን አመነ። አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረው አቶ ጥላሁን ያሚ የተባለው ግለሰብ ወንጀሉን ስለመፈፀሙ ለፖሊስ በሰጠው የእምነት ክህደት ቃል አረጋገጠ። ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ መገደሉን ተከትሎ በግድያ ወንጀል የተጠረጠሩት ጥላሁን ያሚ እና አብዲ አለማየሁ ለሶስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። በተጠርጣሪዎቹ ላይ መርማሪ ፖሊስ ከዚህ ቀደም በተሰጠው የተጨማሪ ስምንት ቀን ጊዜ የሰራውን የምርመራ ሥራ የገለጸ ቢሆንም በዋናነት ከተጠርጣሪዎች ጋር በግድያ ዙሪያ የተጠረጠሩት ላይም ምርመራ ማድረግ ጀምሯል። የስልክ ግንኙነትን በተመለከተም ቃል የመቀበል ስራ መሥራቱንም አስታውቋል። የተለያዩ … [Read more...] about “ራሴን እንዳጠፋ ይፈቀድልኝ” በሃጫሉ ግድያ ተጠርጣሪው ጥላሁን
የሀጫሉ አስከሬን ወደ አምቦ እንዳይሄድ አድርገዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ ቀን ተፈቀደ
የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የወንጀል ችሎት የድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ አስከሬን ወደ አምቦ እንዳይሄድ ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጋር በጋራ ተንቀሳቅሰዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ለመጨረሻ ጊዜ በማለት 12 ቀናት ፈቀደ። ተጠርጣሪዎች አዲሱ ቶሎሳ፣ ደስታ ሽኩር ፣ጥላሁን ለታ፣ አበራ ሁንዴ፣ ሙስተዋሪድ አደም፣ አረፋት አቡበከር፣ አማን ቃሎ፣ ሱልጣን በድያ፣ ውቢ ቡርቃ፣ ሀቢቢ ሳፈው፣ ጉቱ ሙሊሳ፣ ሲሳይ በቀለ፣ ሮባ አዳነ እና ጉልማ ከፈና ናቸው። እንደ ፖሊስ የምርመራ መዝገብ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉት የሟች አስከሬን ወደ አምቦ ሳይደርስ አዲስ አበባ ተመልሶ ወደ ኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ይዘው ሲገቡ የተገኙ ናቸው። ከእነ አቶ ጃዋር ጋር በመሆን አስከሬኑ ወደ … [Read more...] about የሀጫሉ አስከሬን ወደ አምቦ እንዳይሄድ አድርገዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ ቀን ተፈቀደ
የእስክንድር የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ሆነ፤ የአስራት ቲቪ ሠራተኞችና በሃይማኖት በዳዳ ግድያ የተጠረጠሩ ፍርድቤት ቀረቡ
የፖሊስ ምርመራ ቡድን ፍርድ ቤቱ በሰጠው የምርመራ ጊዜ ያገኘውን የምርመራ ሥራ ለፍርድ ቤቱ አብራርቶ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎችም የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል። በምርመራ ቡድኑ አፈፃፀም እና ቀጣይ ጥያቄ ዙሪያ የተጠርጣሪ ጠበቆች እና የምርመራ ቡድኑ ያደረጉትን ክርክር የመረመረው ችሎቱ፣ የፖሊስን የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ጥያቄ አልተቀልኩም ብሏል። ጠበቆችም አቶ እስክንድር ነጋ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ የጠየቁ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል። ምክንያቱ ደግሞ መርማሪ ቡድኑ አቶ እስክንድር የጠረጠረበት ወንጀል ሞት ያስከተለ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከ15 ዓመት በላይ ሊያስቀጣቸው ስለሚችል ነው ብሏል። በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአቶ እስክንድር ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል እንዲከፈት የወሰንኩ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ይስጠኝ በማለት … [Read more...] about የእስክንድር የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ሆነ፤ የአስራት ቲቪ ሠራተኞችና በሃይማኖት በዳዳ ግድያ የተጠረጠሩ ፍርድቤት ቀረቡ
“በትግራይ ያለውን የወጣቶች እንቅስቃሴ ሕዝቡ … መደገፍ ይኖርበታል” ዶ/ር አብርሃም
ካልተወም በግፊት እንዲተው ማስገደድ ያስፈልጋል ብዬ አምናለሁ በትግራይ እያታየ ያለው የወጣቶች እንቅስቃሴ ህዝባዊ ዓላማ እስከአለው ድረስ ህዝቡ የእኔ ነው ብሎ መደገፍና ሥርዓት ይዘው እንዲንቀሳቀሱ ማድረግ ይኖርበታል ሲሉ የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ አስታወቁ። የህወሀት ጥገኛ ቡድን እንቅስቃሴ የኢትዮጵያን ህዝብ ፍላጎት በተለይ ደግሞ የትግራይን ህዝብ የማይመጥን እንደሆነም አመለከቱ። ህዝቡ የወጣቶቹን እንቅስቃሴ ሊቀበልና ሊደግፍ እንደሚገባ ዶክተር አብርሃም ጠቅሰው፣ በትግራይ ያለው አፋኝ አገዛዝ ወይም ፓርቲ ወጣቶችን እንዳያሰቃያቸው ከለላ መሆን ያለበትም ህዝቡ መሆኑን አስገንዝበዋል። ለህዝብ ጥያቄ የተንቀሳቀሰ ወጣት ሲገደል እንዲሁም ለምን ተናገርክ ተብሎ ሲጨፈጨፍና ሲታሰር ካየ፤ ለህዝብ ብሎ … [Read more...] about “በትግራይ ያለውን የወጣቶች እንቅስቃሴ ሕዝቡ … መደገፍ ይኖርበታል” ዶ/ር አብርሃም
“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ” የሚሉ “ከህወሃት በምንም አይሻሉም” የአርሲ ወጣት
* “በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት (የለብንም)” የአርሲ ወጣት ሃገርን ለማፈራረስ የሚሰሩ የጸረ-ሰላም ኃይሎችን ሴራ በማክሸፍ የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ የአርሲ ዞን ወጣቶች ገለጹ። ከአርሲ ዞን 26 ወረዳዎችና የአሰላ ከተማን ጨምሮ ከሶስት የከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ ወጣቶች የተሳተፉበት የሰላምና የልማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአሰላ ከተማ ተካሒዷል። ከኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ከማል ንጉሴ “ሀገሪቷን ለማስቀጠል እኛ ወጣቶች በአንድነት ሆነን የጥፋት ሃይሎችን እንታገላለን ” ብሏል። “ወጣቶች በስሜት ተነሳስተን ጥፋት በማስከተል ሳይሆን በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት፣ የዜጎችን ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም አንድም ለውጥ አይመጣም” ብሏል። ለመንግስት … [Read more...] about “ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ” የሚሉ “ከህወሃት በምንም አይሻሉም” የአርሲ ወጣት
የእነ ጃዋር ጉዳይ ከተጠርጣሪነት ወደ ተከሳሽነት እያመራ ነው
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አቶ ጃዋር መሀመድና እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 14 ተጠርጣሪዎች ላይ አቃቤ ህግ የቅደመ ምርመራ ምስክሮችን እንዲያሰማ ብይን ሰጠ። አቶ ጃዋር መሀመድ፣ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ሐምዛ አዳነን ጨምሮ 14 ተጠርጣሪዎች በዛሬው ዕለት (ሐሙስ) በፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበዋል። የዐቃቤ ሕግ ጥያቄ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ጃዋርን ጨምሮ አጠቃላይ 14 ተጠርጣሪዎች አቶ ጃዋር መሃመድ በሚል መዝገብ በመዝገብ ቁጥር 215585 ላይ የቅድመ ምርመራ መዝገብ የከፈተ ሲሆን፥ በዚህ መዝገብ ላይ ሁከትና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል የተጠረጠረ ጋዜጠኛም ተካቷል። አቃቤ ህግ አቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ በ14ቱም ተጠርጣሪዎች ላይ በመዝገብ ቁጥር 215585 የቀዳሚ ምርመራ እንዲደረግባቸው ጠይቋል። በተጨማሪም የፌደራል … [Read more...] about የእነ ጃዋር ጉዳይ ከተጠርጣሪነት ወደ ተከሳሽነት እያመራ ነው
የበቀለ ገርባ የክስ ዝርዝር
ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ ከወር በፊት በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ ያሉት አቶ በቀለ ገርባ፣ የእርስ በርስ ግጭት በማነሳሳትና ሌሎች ወንጀሎች እንደሚከሰሱ መወሰኑን ዓቃቤ ሕግ ረቡዕ ዕለት አስታወቀ። አቶ በቀለ በበኩላቸው እንደተናገሩት የሃጫሉ ሞትን ምክንያት በማድረግ የተቀሰቀሰው ሁከትና ግጭት፣ በራሱ በሕዝቡ የተመራ እንጂ እሳቸው ይህንን ማድረግ የሚያስችል ሠራዊት እንደሌላቸው ገልጸው፣ መንግሥት ፍርድ ቤትን በመጠቀም ተቀናቃኙን ለማጥፋት እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል። የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቢያነ ሕግ ማክሰኞ ሐምሌ 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ልደታ ማስቻያ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበው እንደተናገሩት፣ ተጠርጣሪው አቶ በቀለ በምን እንደሚከሰሱ ተወስኗል ብለዋል። ክስ የሚመሠረትባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት … [Read more...] about የበቀለ ገርባ የክስ ዝርዝር
“ወያኔ የኦነግ ሠራዊትንና ደጋፊዎችን በጅብ ሲበሉ ታይ ነበር፣ ኦነግ የማፍያ ድርጅት ነው” የኦነግ አባል
የህወሓትን ሆድ ዕቃ ቦርቡሮ የጨረሰው የውስጥ ትግሉ ነው። አሁን የመጣው ውዝግብ የሥልጣን ጥማት እንጂ ሌላ አለመሆኑንን ዶ/ር ጀማል መሀመድ ገምታ ተናገሩ። ልክ እንደ ሃጫሉ የሞት ማስፈራሪያ ደርሷቸው እንደነበርም ስም ጠቅሰው አስታወቁ። ኦህዴድን የከዱ አክቲቪስቶችን በመጋለብ ኦሮሚያ ላይ ቀውስ የሚፈጥረውን ጃዋርን ሆ ብሎ የሚከተለውን ሲያዩ እንደ ኦሮሞ ኃፍረት እንደሚሰማቸው አስታወቁ። ባሌ ተወልደው፣ የህክምና ዲግሪያቸውን ካገኙ በኋላ ኦነግን ተቀላቅለው የነበሩት ሐኪም ጀማል ወደ ኦነግ በመሆናቸው ብቻ አስር ዓመታትን በእስር አሳልፈው ወደ ሎንዶን ተሰደዋል። በእስር ወቅት የደረሰባቸውን ስቃይ ለልጆቻቸውና ንጹህ ኅሊና ላላቸው ስለማይጠቅም ከመግለጽ እንደሚቆጠቡ አስታውቀው የተናገሩት ለኢሳት ነው። አሁን በኢትዮጵያም ሆነ በኦሮሚያ የተፈጠረው ችግር የሥልጣን ጥማት እንደሆነ … [Read more...] about “ወያኔ የኦነግ ሠራዊትንና ደጋፊዎችን በጅብ ሲበሉ ታይ ነበር፣ ኦነግ የማፍያ ድርጅት ነው” የኦነግ አባል