• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእስክንድር የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ሆነ፤ የአስራት ቲቪ ሠራተኞችና በሃይማኖት በዳዳ ግድያ የተጠረጠሩ ፍርድቤት ቀረቡ

August 7, 2020 06:17 pm by Editor Leave a Comment

የፖሊስ ምርመራ ቡድን ፍርድ ቤቱ በሰጠው የምርመራ ጊዜ ያገኘውን የምርመራ ሥራ ለፍርድ ቤቱ አብራርቶ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎችም የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።

በምርመራ ቡድኑ አፈፃፀም እና ቀጣይ ጥያቄ ዙሪያ የተጠርጣሪ ጠበቆች እና የምርመራ ቡድኑ ያደረጉትን ክርክር የመረመረው ችሎቱ፣ የፖሊስን የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ጥያቄ አልተቀልኩም ብሏል።

ጠበቆችም አቶ እስክንድር ነጋ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ የጠየቁ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።

ምክንያቱ ደግሞ መርማሪ ቡድኑ አቶ እስክንድር የጠረጠረበት ወንጀል ሞት ያስከተለ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከ15 ዓመት በላይ ሊያስቀጣቸው ስለሚችል ነው ብሏል።

በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአቶ እስክንድር ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል እንዲከፈት የወሰንኩ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ይስጠኝ በማለት አመልክቷል።

በዚህም ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝ ዐቃቤ ሕግ ለቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚያቀርበው አቤቱታ እስከነምስክሮች ዝርዝር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ዐቃቤ ሕግ በሚያቀርበው አቤቱታ የጠበቆች መቃወሚያ ካለም እሰማለሁ ብሏል።

ይህ እስከሚሆን ድረስ ግን ተጠርጣሪው አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ አዝዟል።

ከዐቃቤ ሕግ ባገኘነው መረጃ መሠረት ከአቶ እስክንድር ጋር ስንታየሁ ቸኮል እና ቀለብ ስዩም የተባሉ ተጠርጣሪዎች በዚሁ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል ውስጥ የሚካተቱ ይሆናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሁከት እና ግጭት በማስነሳት ወንጀል የተጠረጠሩ የአስራት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች እና በጥቁር አንበሳ የህክምና ቤተ ሙከራ ህይወቷ አልፎ የተገኘችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 7 የጥበቃ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ።

መርመራ ፖሊስ በአስራት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ላይ ከህገ መንግስት እና ከሙያ ስነ ምግባር ውጭ ያፈነገጠ የሃይማኖትና የብሄር ግጭት የሚያስነሳ ፕሮግራም ሰርተዋል ሲል ይህንን አስመልክቶ የሰራውን ስራ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

በፕሮግራሙ ላይም የሰነድ ማስረጃ ማሰባሰቡን ገልፆ እጃቸው ላይ ያገኘውን የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) እንዲመረምር እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስም ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቃ በበኩሉ 4 ኪሎ የሚገኘው የአስራት ቴሌቪዥን በቂ ምርመራ ተደርጎበታል ተጨማሪ ምርመራ አደርጋለሁ መባሉም አግባብ አይደለም ሲል ተከራክሯል።

አየር ላይ የዋሉ ፕሮግራሞች ከዩ ቲዩብ እና ሌሎች ድረ ገፆች ላይ ማግኘት ይችላሉ፤ የተጠርጣሪዎች የተናጠል ድርሻ ሊቀርብ ይገባል ያለ ሲሆን የዋስትና መብታቸው ሊከበር እንደሚገባም ጠይቋል።

ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እንዳልተደረገላቸው ገልፀው ስጋት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ሶስተኛ ተጠርጣሪ የጤና ሁኔታውን ገልፆ አያያዛቸው እንዲስተካከል የጠየቀ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ሁሉም ተጠርጣሪዎች ጤንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን አዟል።

ከቤተሰብ ጋርም በጥንቃቄ እንዲገናኙ ትዕዛዝ አስተላልፎ ለተጨማሪ ምርመራ 12 ቀን ፈቅዷል።

በተያያዘ ዜና በጥቁር አንበሳ የህክምና ክፍል ቤተ ሙከራ ውስጥ ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ህይወቷ አልፎ የተገኘችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያዘ የተጠረጠሩ 7 የጥበቃ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ።

በእነ ሃብቴ ጓቤ መዝገብ የቀረቡት እነዚህ ተጠርጣሪዎች ላይ መርማሪ ፖሊስ እየሰራ ያለውን ስራ አስመልክቶ ተጨማሪ ጊዜ የጠየቀ ሲሆን ግድያ ፈጽሜያለሁ በሚል የእምነት ክህደት ቃሉን ከሰጠው ደግነት ወርቁ በተጨማሪም እነዚህ ተጠርጣሪዎች ከግድያው ጀርባ ያላቸው ግንኙነት እየለየ መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።

ሟች ተማሪ በአማካሪዋ ተደውሎላት ወደ ጥቁር አንበሳ የሄደች ሲሆን የስልክ ልውውጡን ፖሊስ እየመረመረ መሆኑን አስረድቷል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን ሁለተኛ ተጠርጣሪ በወቅቱ የኤጀንሲ ጠባቂዎች መሆናቸውን በመጥቀስ ተማሪ ሃይማኖት ህይወቷ አልፎ የተገኘበት ህንፃ በበጀት ጉድለት ምክንያት ጠባቂ እንደሌለው ተናግረዋል።

የዋስትና መብታችን ይጠበቅ ያሉ ጠይቀዋል ፍርድ ቤት በበኩሉ መርማሪ ፖሊስ የተናጠል ተሳትፏቸውን እንዲያቀርብ በማዘዝ የ7 ቀን ጊዜ ፈቅዷል። ምንጭ፤ ©ፋና

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: chilot, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule