• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእስክንድር የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ሆነ፤ የአስራት ቲቪ ሠራተኞችና በሃይማኖት በዳዳ ግድያ የተጠረጠሩ ፍርድቤት ቀረቡ

August 7, 2020 06:17 pm by Editor Leave a Comment

የፖሊስ ምርመራ ቡድን ፍርድ ቤቱ በሰጠው የምርመራ ጊዜ ያገኘውን የምርመራ ሥራ ለፍርድ ቤቱ አብራርቶ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎችም የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።

በምርመራ ቡድኑ አፈፃፀም እና ቀጣይ ጥያቄ ዙሪያ የተጠርጣሪ ጠበቆች እና የምርመራ ቡድኑ ያደረጉትን ክርክር የመረመረው ችሎቱ፣ የፖሊስን የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ጥያቄ አልተቀልኩም ብሏል።

ጠበቆችም አቶ እስክንድር ነጋ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ የጠየቁ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።

ምክንያቱ ደግሞ መርማሪ ቡድኑ አቶ እስክንድር የጠረጠረበት ወንጀል ሞት ያስከተለ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከ15 ዓመት በላይ ሊያስቀጣቸው ስለሚችል ነው ብሏል።

በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአቶ እስክንድር ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል እንዲከፈት የወሰንኩ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ይስጠኝ በማለት አመልክቷል።

በዚህም ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝ ዐቃቤ ሕግ ለቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚያቀርበው አቤቱታ እስከነምስክሮች ዝርዝር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ዐቃቤ ሕግ በሚያቀርበው አቤቱታ የጠበቆች መቃወሚያ ካለም እሰማለሁ ብሏል።

ይህ እስከሚሆን ድረስ ግን ተጠርጣሪው አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ አዝዟል።

ከዐቃቤ ሕግ ባገኘነው መረጃ መሠረት ከአቶ እስክንድር ጋር ስንታየሁ ቸኮል እና ቀለብ ስዩም የተባሉ ተጠርጣሪዎች በዚሁ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል ውስጥ የሚካተቱ ይሆናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሁከት እና ግጭት በማስነሳት ወንጀል የተጠረጠሩ የአስራት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች እና በጥቁር አንበሳ የህክምና ቤተ ሙከራ ህይወቷ አልፎ የተገኘችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 7 የጥበቃ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ።

መርመራ ፖሊስ በአስራት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ላይ ከህገ መንግስት እና ከሙያ ስነ ምግባር ውጭ ያፈነገጠ የሃይማኖትና የብሄር ግጭት የሚያስነሳ ፕሮግራም ሰርተዋል ሲል ይህንን አስመልክቶ የሰራውን ስራ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

በፕሮግራሙ ላይም የሰነድ ማስረጃ ማሰባሰቡን ገልፆ እጃቸው ላይ ያገኘውን የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) እንዲመረምር እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስም ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቃ በበኩሉ 4 ኪሎ የሚገኘው የአስራት ቴሌቪዥን በቂ ምርመራ ተደርጎበታል ተጨማሪ ምርመራ አደርጋለሁ መባሉም አግባብ አይደለም ሲል ተከራክሯል።

አየር ላይ የዋሉ ፕሮግራሞች ከዩ ቲዩብ እና ሌሎች ድረ ገፆች ላይ ማግኘት ይችላሉ፤ የተጠርጣሪዎች የተናጠል ድርሻ ሊቀርብ ይገባል ያለ ሲሆን የዋስትና መብታቸው ሊከበር እንደሚገባም ጠይቋል።

ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እንዳልተደረገላቸው ገልፀው ስጋት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ሶስተኛ ተጠርጣሪ የጤና ሁኔታውን ገልፆ አያያዛቸው እንዲስተካከል የጠየቀ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ሁሉም ተጠርጣሪዎች ጤንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን አዟል።

ከቤተሰብ ጋርም በጥንቃቄ እንዲገናኙ ትዕዛዝ አስተላልፎ ለተጨማሪ ምርመራ 12 ቀን ፈቅዷል።

በተያያዘ ዜና በጥቁር አንበሳ የህክምና ክፍል ቤተ ሙከራ ውስጥ ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ህይወቷ አልፎ የተገኘችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያዘ የተጠረጠሩ 7 የጥበቃ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ።

በእነ ሃብቴ ጓቤ መዝገብ የቀረቡት እነዚህ ተጠርጣሪዎች ላይ መርማሪ ፖሊስ እየሰራ ያለውን ስራ አስመልክቶ ተጨማሪ ጊዜ የጠየቀ ሲሆን ግድያ ፈጽሜያለሁ በሚል የእምነት ክህደት ቃሉን ከሰጠው ደግነት ወርቁ በተጨማሪም እነዚህ ተጠርጣሪዎች ከግድያው ጀርባ ያላቸው ግንኙነት እየለየ መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።

ሟች ተማሪ በአማካሪዋ ተደውሎላት ወደ ጥቁር አንበሳ የሄደች ሲሆን የስልክ ልውውጡን ፖሊስ እየመረመረ መሆኑን አስረድቷል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን ሁለተኛ ተጠርጣሪ በወቅቱ የኤጀንሲ ጠባቂዎች መሆናቸውን በመጥቀስ ተማሪ ሃይማኖት ህይወቷ አልፎ የተገኘበት ህንፃ በበጀት ጉድለት ምክንያት ጠባቂ እንደሌለው ተናግረዋል።

የዋስትና መብታችን ይጠበቅ ያሉ ጠይቀዋል ፍርድ ቤት በበኩሉ መርማሪ ፖሊስ የተናጠል ተሳትፏቸውን እንዲያቀርብ በማዘዝ የ7 ቀን ጊዜ ፈቅዷል። ምንጭ፤ ©ፋና

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: chilot, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule