• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእስክንድር የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ሆነ፤ የአስራት ቲቪ ሠራተኞችና በሃይማኖት በዳዳ ግድያ የተጠረጠሩ ፍርድቤት ቀረቡ

August 7, 2020 06:17 pm by Editor Leave a Comment

የፖሊስ ምርመራ ቡድን ፍርድ ቤቱ በሰጠው የምርመራ ጊዜ ያገኘውን የምርመራ ሥራ ለፍርድ ቤቱ አብራርቶ ለቀሪ የምርመራ ሥራዎችም የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።

በምርመራ ቡድኑ አፈፃፀም እና ቀጣይ ጥያቄ ዙሪያ የተጠርጣሪ ጠበቆች እና የምርመራ ቡድኑ ያደረጉትን ክርክር የመረመረው ችሎቱ፣ የፖሊስን የተጨማሪ ምርመራ ጊዜ ጥያቄ አልተቀልኩም ብሏል።

ጠበቆችም አቶ እስክንድር ነጋ የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ የጠየቁ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ አድርጓል።

ምክንያቱ ደግሞ መርማሪ ቡድኑ አቶ እስክንድር የጠረጠረበት ወንጀል ሞት ያስከተለ በመሆኑ ጥፋተኛ ሆኖ ከተገኘ ከ15 ዓመት በላይ ሊያስቀጣቸው ስለሚችል ነው ብሏል።

በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ በአቶ እስክንድር ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል እንዲከፈት የወሰንኩ በመሆኑ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ይስጠኝ በማለት አመልክቷል።

በዚህም ችሎቱ በሰጠው ትዕዛዝ ዐቃቤ ሕግ ለቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚያቀርበው አቤቱታ እስከነምስክሮች ዝርዝር እንዲያቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ዐቃቤ ሕግ በሚያቀርበው አቤቱታ የጠበቆች መቃወሚያ ካለም እሰማለሁ ብሏል።

ይህ እስከሚሆን ድረስ ግን ተጠርጣሪው አቶ እስክንድር ነጋ በፖሊስ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ አዝዟል።

ከዐቃቤ ሕግ ባገኘነው መረጃ መሠረት ከአቶ እስክንድር ጋር ስንታየሁ ቸኮል እና ቀለብ ስዩም የተባሉ ተጠርጣሪዎች በዚሁ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል ውስጥ የሚካተቱ ይሆናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሁከት እና ግጭት በማስነሳት ወንጀል የተጠረጠሩ የአስራት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች እና በጥቁር አንበሳ የህክምና ቤተ ሙከራ ህይወቷ አልፎ የተገኘችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 7 የጥበቃ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ።

መርመራ ፖሊስ በአስራት ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች ላይ ከህገ መንግስት እና ከሙያ ስነ ምግባር ውጭ ያፈነገጠ የሃይማኖትና የብሄር ግጭት የሚያስነሳ ፕሮግራም ሰርተዋል ሲል ይህንን አስመልክቶ የሰራውን ስራ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

በፕሮግራሙ ላይም የሰነድ ማስረጃ ማሰባሰቡን ገልፆ እጃቸው ላይ ያገኘውን የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢንሳ) እንዲመረምር እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስም ተጨማሪ 14 ቀን ለምርመራ ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።

የተጠርጣሪ ጠበቃ በበኩሉ 4 ኪሎ የሚገኘው የአስራት ቴሌቪዥን በቂ ምርመራ ተደርጎበታል ተጨማሪ ምርመራ አደርጋለሁ መባሉም አግባብ አይደለም ሲል ተከራክሯል።

አየር ላይ የዋሉ ፕሮግራሞች ከዩ ቲዩብ እና ሌሎች ድረ ገፆች ላይ ማግኘት ይችላሉ፤ የተጠርጣሪዎች የተናጠል ድርሻ ሊቀርብ ይገባል ያለ ሲሆን የዋስትና መብታቸው ሊከበር እንደሚገባም ጠይቋል።

ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እንዳልተደረገላቸው ገልፀው ስጋት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

ሶስተኛ ተጠርጣሪ የጤና ሁኔታውን ገልፆ አያያዛቸው እንዲስተካከል የጠየቀ ሲሆን ፍርድ ቤቱም ሁሉም ተጠርጣሪዎች ጤንነታቸው የተጠበቀ እንዲሆን አዟል።

ከቤተሰብ ጋርም በጥንቃቄ እንዲገናኙ ትዕዛዝ አስተላልፎ ለተጨማሪ ምርመራ 12 ቀን ፈቅዷል።

በተያያዘ ዜና በጥቁር አንበሳ የህክምና ክፍል ቤተ ሙከራ ውስጥ ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ህይወቷ አልፎ የተገኘችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያዘ የተጠረጠሩ 7 የጥበቃ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ።

በእነ ሃብቴ ጓቤ መዝገብ የቀረቡት እነዚህ ተጠርጣሪዎች ላይ መርማሪ ፖሊስ እየሰራ ያለውን ስራ አስመልክቶ ተጨማሪ ጊዜ የጠየቀ ሲሆን ግድያ ፈጽሜያለሁ በሚል የእምነት ክህደት ቃሉን ከሰጠው ደግነት ወርቁ በተጨማሪም እነዚህ ተጠርጣሪዎች ከግድያው ጀርባ ያላቸው ግንኙነት እየለየ መሆኑን ፖሊስ አስረድቷል።

ሟች ተማሪ በአማካሪዋ ተደውሎላት ወደ ጥቁር አንበሳ የሄደች ሲሆን የስልክ ልውውጡን ፖሊስ እየመረመረ መሆኑን አስረድቷል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን ሁለተኛ ተጠርጣሪ በወቅቱ የኤጀንሲ ጠባቂዎች መሆናቸውን በመጥቀስ ተማሪ ሃይማኖት ህይወቷ አልፎ የተገኘበት ህንፃ በበጀት ጉድለት ምክንያት ጠባቂ እንደሌለው ተናግረዋል።

የዋስትና መብታችን ይጠበቅ ያሉ ጠይቀዋል ፍርድ ቤት በበኩሉ መርማሪ ፖሊስ የተናጠል ተሳትፏቸውን እንዲያቀርብ በማዘዝ የ7 ቀን ጊዜ ፈቅዷል። ምንጭ፤ ©ፋና

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: chilot, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule