• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሀጫሉ አስከሬን ወደ አምቦ እንዳይሄድ አድርገዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ተጨማሪ ቀን ተፈቀደ

August 7, 2020 06:40 pm by Editor Leave a Comment

የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የወንጀል ችሎት የድምፃዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ አስከሬን ወደ አምቦ እንዳይሄድ ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጋር በጋራ ተንቀሳቅሰዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ለመጨረሻ ጊዜ በማለት 12 ቀናት ፈቀደ። 

ተጠርጣሪዎች አዲሱ ቶሎሳ፣ ደስታ ሽኩር ፣ጥላሁን ለታ፣ አበራ ሁንዴ፣ ሙስተዋሪድ አደም፣ አረፋት አቡበከር፣ አማን ቃሎ፣ ሱልጣን በድያ፣ ውቢ ቡርቃ፣ ሀቢቢ ሳፈው፣ ጉቱ ሙሊሳ፣ ሲሳይ በቀለ፣ ሮባ አዳነ እና ጉልማ ከፈና ናቸው። 

እንደ ፖሊስ የምርመራ መዝገብ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉት የሟች አስከሬን ወደ አምቦ ሳይደርስ አዲስ አበባ ተመልሶ ወደ ኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ይዘው ሲገቡ የተገኙ ናቸው። 

ከእነ አቶ ጃዋር ጋር በመሆን አስከሬኑ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ 10 ቀን ተለቅሶ የሚኒሊክ ሐውልትን በማፍረስ ቤተመንግስቱን መቆጣጠር የሚለውን ዓላማ ሲያራምዱ የተገኙ መሆናቸውንም ጠቅሷል ፖሊስ በምርመራ መዝገቡ። 

ከተጠርጣሪዎች  ሲሳይ በቀለ የተባለው፣ “ሟች ዘመዴ ነው ለቅሶ ልደርስ ሄጄ አስከሬኑ ወደ አዲስ አበባ ሲመለስ አብሬ ተመልሼ ከኦሮሚያ ብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ተያዝኩ እንጂ የፈፀምኩት ጥፋት የለም፤ የዋስትና መብቴ ይጠበቅልኝ” በማለት አመልክቷል። 

ሌላኛው ወቢ ቡርቃ የተባለው ተጠርጣሪ ያጠፋው ጥፋት እንደሌለ እና የዩኒቨርስቲ ተማሪ እንደመሆኑ መጠን “የነገ ተስፋዬን በማየት ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብቴን ይጠብቅልኝ” ብሏል። 

በእስር ሆኖ በኮሮና ቫይረስ ተይዞ 15 ቀን በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ሲታከም ሕመሙን ተገናዝቦ እንደ ታካሚ ሳይሆን እንደ እስረኛ ሆኖ 15 ቀኑን በመጥፎ ሁኔታ ማሳለፉንም ለችሎቱ ገልጿል። 

ጠበቆችም እንዲሁ የተጠርጣሪዎች የየግል ጥፋት ተለይቶ አልተቀመጠም፣ ያጠፉት ጥፋትም የለም፤ በዚህም የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅላቸው ጠይቀዋል። 

የምርመራ ቡድን የሰጠውን ምላሽ ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ተፈፀመ ከተባለው ወንጀል ስፋት አንጻር የተጠየቀውን የዋስትና ጥያቄ አልተቀበለም። 

የፖሊስን የምርመራ መዝገብ እየተመለከተ መሆኑን በመጥቀስ ፖሊስ ከጠየቀው 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ 12 ቀናቱን ለመጨረሻ በማለት ፈቅዷል። 

ወቢ ቡርቃ የተባለው ተጠርጣሪ በኤካ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ሕመምተኛ ሁኖ የቆየበትን ሁኔታ ሆስፒታሉ በጽሁፍ እንዲያስረዳም አዝዟል። 

ውጤቱን ለመጠበቅ ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 13 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። (ምንጭ፤ ጥላሁን ካሳ፤ ኢብኮ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Right Column, Uncategorized Tagged With: chilot, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule