• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ራሴን እንዳጠፋ ይፈቀድልኝ” በሃጫሉ ግድያ ተጠርጣሪው ጥላሁን

August 7, 2020 07:30 pm by Editor Leave a Comment

በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረው ግለሰብ ወንጀሉን መፈፀሙን አመነ። አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ላይ ጥይት ተኩሶ በመግደል ወንጀል የተጠረጠረው አቶ ጥላሁን ያሚ የተባለው ግለሰብ ወንጀሉን ስለመፈፀሙ ለፖሊስ በሰጠው የእምነት ክህደት ቃል አረጋገጠ።

ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ መገደሉን ተከትሎ በግድያ ወንጀል የተጠረጠሩት ጥላሁን ያሚ እና አብዲ አለማየሁ ለሶስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

በተጠርጣሪዎቹ ላይ መርማሪ ፖሊስ ከዚህ ቀደም በተሰጠው የተጨማሪ ስምንት ቀን ጊዜ የሰራውን የምርመራ ሥራ የገለጸ ቢሆንም በዋናነት ከተጠርጣሪዎች ጋር በግድያ ዙሪያ የተጠረጠሩት ላይም ምርመራ ማድረግ ጀምሯል።

የስልክ ግንኙነትን በተመለከተም ቃል የመቀበል ስራ መሥራቱንም አስታውቋል።

የተለያዩ መሥሪያ ቤቶች ማስረጃ ማሰባሰብ፣ ከኢትዮ ቴሌኮም የተላከ የስልክ መልዕክት ሰፊ መሆኑን ተከትሎ የትንተና ሥራ እየሠራ መሆኑንም አመልክቷል።

ከተጠርጣሪዎች እጅ የተገኙ ስልኮችን ለብሄራዊ መረጃ ደህንነት በመላክ ሌሎች የምርመራ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑንም ተናግሯል መርማሪ ፖሊስ።

ፍርድ ቤቱ በበኩሉ ከዚህ በፊት ከሰራችሁት ስራ ውጭ ምን የተለየ ውጤት ተገኘ ሲል ላቀረበው ጥያቄ መርማሪ ፖሊስ ከተጠርጣሪዎች በስተጀርባ ሌሎች ተጠርጣሪዎች መኖራቸውን የሚያመላክት መረጃ መገኘቱን ጠቅሷል። እንዲሁም ከወንጀሉ በስተጀርባ የተቀነባበረ ወንጀልን ለመለየት ስራ ላይ መሆኑን የተናገረው መርማሪ ፖሊስ ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀን ይሰጠኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።

ተጠርጣሪው “ይህንን ተልእኮ የሰጡኝ ሰዎች ድርጊቱን መፈፀምህን በሚስጥር የማትይዝ ከሆነ በቤተሰቦችህ ላይ ጉዳት እናደርሳለን” በማለት እንዳስጠነቀቁት ለፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፣ የአራዳ ምድብ፣ አንደኛ ወንጀል ችሎት ተናግሯል።

በዚህም “ለቤተሰቦቼ በቂ ጥበቃ እንዲደረግላቸው እና የኔም ጉዳይ በፍጥነት እልባት እንዲያገኝ” በማለት ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል።

“የፀሀይ ብርሀን አግኝቼ አላውቅም፣ ካቴና ከእጄ አላወለቀም፣ ክስ እስከሚመሰረትብኝ እንኳን ከሌሎች ተጠርጣሪዎች ጋር እንድቀላቀል ይደረግልኝ” በማለት ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርቧል።

ተጠርጣሪው ባለፈው የጊዜ ቀጠሮ በዚሁ ችሎት ቀርቦ “እራሴን እንዳጠፋ ይፈቀድልኝ” ማለቱን ችሎቱ አስታውሷል። በዚያው ቀጠሮው መርማሪ ፖሊስ ካቴናው ከእጁ የማይወልቀው ተጠርጣሪው እራሱን እንዳያጠፋ ለመከላከል መሆኑንም ችሎቱ ገልጿል።

መርማሪ ፖሊስ በዛሬው ቀጠሮው ተጠርጣሪው የካቴናውን ጉዳይ ዳግም በማንሳቱ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሚመለከተው የስራ ሀላፊ በቀጣይ ቀጠሮው ስለሁኔታው ያስረዳ ብሏል ችሎቱ።

ፖሊስ ባለፈው የተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ያከናወነውን የምርመራ ስራ ያደመጠው ፍርድ ቤቱ በቀጣይ በተለይም በቁጥጥር ስር ከሚገኙ ተጠርጣሪዎች ጀርባ ድርጊቱን ያቀነባበሩ አካላትን በቁጥጥር ስር ለማዋል እና ሌሎች የሰነድ ማስረጃዎችን ለማደራጀት ከጠየቀው 14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፍርድ ቤቱ 11 ቀን ፈቅዷል።

በግብረአበርነት የተጠረጠረው አብዲ አለማየሁ የተባለው ግለሰብም በዛሬው ችሎት ከጥላሁን ያሚ ጋር ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር።

ፍርድ ቤቱ ውጤቱን ለመጠባበቅም ለነሀሴ 12 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። (ምንጭ፤ ኢብኮ እና ፋና (ፎቶ፤ ከኢንተርኔት የተገኘና ለማሳየነት የቀረበ))

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Left Column, News Tagged With: chilot, jawar massacre, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule