• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ” የሚሉ “ከህወሃት በምንም አይሻሉም” የአርሲ ወጣት

August 6, 2020 09:26 pm by Editor Leave a Comment

* “በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት (የለብንም)” የአርሲ ወጣት

ሃገርን ለማፈራረስ የሚሰሩ የጸረ-ሰላም ኃይሎችን ሴራ በማክሸፍ የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ የአርሲ ዞን ወጣቶች ገለጹ።

ከአርሲ ዞን 26 ወረዳዎችና የአሰላ ከተማን ጨምሮ ከሶስት የከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ ወጣቶች የተሳተፉበት የሰላምና የልማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአሰላ ከተማ ተካሒዷል። 

ከኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ከማል ንጉሴ “ሀገሪቷን ለማስቀጠል እኛ ወጣቶች በአንድነት ሆነን የጥፋት ሃይሎችን እንታገላለን ” ብሏል።

“ወጣቶች በስሜት ተነሳስተን ጥፋት በማስከተል ሳይሆን በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት፣ የዜጎችን ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም አንድም ለውጥ አይመጣም” ብሏል።

ለመንግስት የሚቀርብ ጥያቄ ቢኖር እንኳን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከርና በመወያየት መፍታት እንደሚቻል ገልጾ፤ በክልሉ የተፈፀመው ተግባር ቄሮንም ሆነ ኦሮሞን እንዲሁም ማንኛውንም የህብረተሰብ ክፍል የማይወክል መሆኑን ተናግሯል።

“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ፣ በገበያ ላይ አድማ አድርጉ፣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አግቱ ብለው ትዕዛዝ የሚያስተላልፉ አካላት በተመቻቸ ኑሮ ላይ ሆነው የደሃ ልጆችን ያስቀጥፋሉ ከትናንትናው ህወሃት በምንም አይሻሉም” ብሏል።

“የኦሮሞ ህዝብ በባህሉ ሌላውን ብሔር በጉዲፈቻና ሞጋሳ ወደ ራሱ በማምጣት አቃፊነትን መቻቻልና አብሮነትን ያስተማረ ነው” ያለው ደግሞ ወጣት ሙሐመድ ተሲ ነው።

“እኛ የኦሮሞ ወጣቶች ሀገር ማፍረስ ሳይሆን ከአባቶቻችን በወረስነው ጀግንነትና አንድነት ሀገሪቷን ገንብተን ማለፍ ነው” ብሏል።

ሌላኛው አስተያያት ሰጪ ወጣት ድሪባ ንጉሴ በበኩሉ “በመንግስት መዋቅር ውስጥ ሆነው ከውጭ ጠላት ጋር የሚሰሩ፣ የጥፋት መመሪያ የሚያስተላልፉ አመራሮች በህግ መጠየቅ አለባቸው” ብሏል።

“የኦሮሞ ህዝብ መቻቻልና አብሮነትን ከገዳ ስርዓት ነው የተማረው” ያለው ወጣት ድሪባ “ወጣቶች በተደላደለ ህይወት ውስጥ ቁጭ ብለው ትዕዛዝ የሚሰጡትን ሃይሎች መስማት የለባቸውም” ብሏል።

የአሰላ ከተማ ከንቲባ አቶ ገብሬ ዑርጌሶ በበኩላቸው የከተማዋ ወጣቶች ንብረት እንዳይወድም ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል።

ጥቂት ሰዎች የጥፋት ተልእኮ ተቀብለው ሀገር የመበጥበጥ ዓላማ እንዳላቸው ወጣቶች የተረዱበት መድረክ መሆኑንም ጠቅሰው ወጣቶች ጥፋትን ከመከላከል ባለፈ የአፍራሽ ተልዕኮ አስፈፃሚ እንዳይሆኑ የእናትና አባታቸውን ንብረትና ባህል እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

የአርሲ ዞን አስተዳደር አቶ ጀማል አሊይ እንደገለጹት የትራንስፖርት፣የንግድና የገበያ እንቅስቃሴ እንዳይኖር የሚያደርጉ የጥፋት ሃይሎች በወጣቱ ዘንድ ቦታ እንደሌላቸው ከመድረኩ መረዳታቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለሱንም ተናግረዋል።

ወጣቶች መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ከጀመረው በጎ ተግባር ጎን እንደሚቆሙ ማረጋገጣቸውን የገለጹት አቶ ጀማል፤ ንብረት በማውደምና በማቃጠል የሚገኝ ውጤት ባለመኖሩ በሰላም ማስፈን ላይ አሁንም ተባብረው መስራት እንደሚገባቸው አስገዝበዋል።

መድረኩን የመሩት የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ፕሬዘዳንት አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው መንግስት የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥና አጥፊዎችን ለህግ ከማቅረብ ጎን ለጎን ንብረት የተጎዳባቸውን መልሶ ለማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

“በአሁኑ ወቅት የምግብ፣ አልባሳት፣ የዘርና የአፈር ማደባሪያ ጭምር ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው” ያሉት አቶ አወሉ የዞኑ ማህበረሰብ ተጎጂዎችን በራሱ መልሶ ለማቋቋምና ወደ ቀደመው ህይወት እንዲመለሱ ለማድረግ በየወረዳው ኮሚቴ ተደራጅቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።

በድርጊቱ የተሳተፉ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥና በህብረተሰቡ ዘንድም ያሉ የጥፋት ተልእኮ ፈፃሚዎችን ለህግ እንዲቀርቡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

የአርቲስት ሃጫሉን ሞት ተከትሎ በአሰላ ከተማና በአርሲ ዞን በተፈጠረው ሁከትና ግርግር የሰው ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም የተጠረጠሩ ከ1ሺህ 300 በላይ ግለሰቦች ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከአስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: arsi, jawar massacre

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule