• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ” የሚሉ “ከህወሃት በምንም አይሻሉም” የአርሲ ወጣት

August 6, 2020 09:26 pm by Editor Leave a Comment

* “በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት (የለብንም)” የአርሲ ወጣት

ሃገርን ለማፈራረስ የሚሰሩ የጸረ-ሰላም ኃይሎችን ሴራ በማክሸፍ የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ የአርሲ ዞን ወጣቶች ገለጹ።

ከአርሲ ዞን 26 ወረዳዎችና የአሰላ ከተማን ጨምሮ ከሶስት የከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ ወጣቶች የተሳተፉበት የሰላምና የልማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአሰላ ከተማ ተካሒዷል። 

ከኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ከማል ንጉሴ “ሀገሪቷን ለማስቀጠል እኛ ወጣቶች በአንድነት ሆነን የጥፋት ሃይሎችን እንታገላለን ” ብሏል።

“ወጣቶች በስሜት ተነሳስተን ጥፋት በማስከተል ሳይሆን በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት፣ የዜጎችን ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም አንድም ለውጥ አይመጣም” ብሏል።

ለመንግስት የሚቀርብ ጥያቄ ቢኖር እንኳን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከርና በመወያየት መፍታት እንደሚቻል ገልጾ፤ በክልሉ የተፈፀመው ተግባር ቄሮንም ሆነ ኦሮሞን እንዲሁም ማንኛውንም የህብረተሰብ ክፍል የማይወክል መሆኑን ተናግሯል።

“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ፣ በገበያ ላይ አድማ አድርጉ፣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አግቱ ብለው ትዕዛዝ የሚያስተላልፉ አካላት በተመቻቸ ኑሮ ላይ ሆነው የደሃ ልጆችን ያስቀጥፋሉ ከትናንትናው ህወሃት በምንም አይሻሉም” ብሏል።

“የኦሮሞ ህዝብ በባህሉ ሌላውን ብሔር በጉዲፈቻና ሞጋሳ ወደ ራሱ በማምጣት አቃፊነትን መቻቻልና አብሮነትን ያስተማረ ነው” ያለው ደግሞ ወጣት ሙሐመድ ተሲ ነው።

“እኛ የኦሮሞ ወጣቶች ሀገር ማፍረስ ሳይሆን ከአባቶቻችን በወረስነው ጀግንነትና አንድነት ሀገሪቷን ገንብተን ማለፍ ነው” ብሏል።

ሌላኛው አስተያያት ሰጪ ወጣት ድሪባ ንጉሴ በበኩሉ “በመንግስት መዋቅር ውስጥ ሆነው ከውጭ ጠላት ጋር የሚሰሩ፣ የጥፋት መመሪያ የሚያስተላልፉ አመራሮች በህግ መጠየቅ አለባቸው” ብሏል።

“የኦሮሞ ህዝብ መቻቻልና አብሮነትን ከገዳ ስርዓት ነው የተማረው” ያለው ወጣት ድሪባ “ወጣቶች በተደላደለ ህይወት ውስጥ ቁጭ ብለው ትዕዛዝ የሚሰጡትን ሃይሎች መስማት የለባቸውም” ብሏል።

የአሰላ ከተማ ከንቲባ አቶ ገብሬ ዑርጌሶ በበኩላቸው የከተማዋ ወጣቶች ንብረት እንዳይወድም ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል።

ጥቂት ሰዎች የጥፋት ተልእኮ ተቀብለው ሀገር የመበጥበጥ ዓላማ እንዳላቸው ወጣቶች የተረዱበት መድረክ መሆኑንም ጠቅሰው ወጣቶች ጥፋትን ከመከላከል ባለፈ የአፍራሽ ተልዕኮ አስፈፃሚ እንዳይሆኑ የእናትና አባታቸውን ንብረትና ባህል እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

የአርሲ ዞን አስተዳደር አቶ ጀማል አሊይ እንደገለጹት የትራንስፖርት፣የንግድና የገበያ እንቅስቃሴ እንዳይኖር የሚያደርጉ የጥፋት ሃይሎች በወጣቱ ዘንድ ቦታ እንደሌላቸው ከመድረኩ መረዳታቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለሱንም ተናግረዋል።

ወጣቶች መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ከጀመረው በጎ ተግባር ጎን እንደሚቆሙ ማረጋገጣቸውን የገለጹት አቶ ጀማል፤ ንብረት በማውደምና በማቃጠል የሚገኝ ውጤት ባለመኖሩ በሰላም ማስፈን ላይ አሁንም ተባብረው መስራት እንደሚገባቸው አስገዝበዋል።

መድረኩን የመሩት የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ፕሬዘዳንት አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው መንግስት የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥና አጥፊዎችን ለህግ ከማቅረብ ጎን ለጎን ንብረት የተጎዳባቸውን መልሶ ለማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

“በአሁኑ ወቅት የምግብ፣ አልባሳት፣ የዘርና የአፈር ማደባሪያ ጭምር ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው” ያሉት አቶ አወሉ የዞኑ ማህበረሰብ ተጎጂዎችን በራሱ መልሶ ለማቋቋምና ወደ ቀደመው ህይወት እንዲመለሱ ለማድረግ በየወረዳው ኮሚቴ ተደራጅቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።

በድርጊቱ የተሳተፉ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥና በህብረተሰቡ ዘንድም ያሉ የጥፋት ተልእኮ ፈፃሚዎችን ለህግ እንዲቀርቡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

የአርቲስት ሃጫሉን ሞት ተከትሎ በአሰላ ከተማና በአርሲ ዞን በተፈጠረው ሁከትና ግርግር የሰው ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም የተጠረጠሩ ከ1ሺህ 300 በላይ ግለሰቦች ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከአስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: arsi, jawar massacre

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule