• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ” የሚሉ “ከህወሃት በምንም አይሻሉም” የአርሲ ወጣት

August 6, 2020 09:26 pm by Editor Leave a Comment

* “በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት (የለብንም)” የአርሲ ወጣት

ሃገርን ለማፈራረስ የሚሰሩ የጸረ-ሰላም ኃይሎችን ሴራ በማክሸፍ የክልሉን ሰላም ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ የአርሲ ዞን ወጣቶች ገለጹ።

ከአርሲ ዞን 26 ወረዳዎችና የአሰላ ከተማን ጨምሮ ከሶስት የከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ ወጣቶች የተሳተፉበት የሰላምና የልማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአሰላ ከተማ ተካሒዷል። 

ከኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች መካከል ወጣት ከማል ንጉሴ “ሀገሪቷን ለማስቀጠል እኛ ወጣቶች በአንድነት ሆነን የጥፋት ሃይሎችን እንታገላለን ” ብሏል።

“ወጣቶች በስሜት ተነሳስተን ጥፋት በማስከተል ሳይሆን በተማረ ጭንቅላት ብቻ ታግለን ማሸነፍ አለብን እንጂ መንገድ በመዝጋት፣ የዜጎችን ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም አንድም ለውጥ አይመጣም” ብሏል።

ለመንግስት የሚቀርብ ጥያቄ ቢኖር እንኳን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመመካከርና በመወያየት መፍታት እንደሚቻል ገልጾ፤ በክልሉ የተፈፀመው ተግባር ቄሮንም ሆነ ኦሮሞን እንዲሁም ማንኛውንም የህብረተሰብ ክፍል የማይወክል መሆኑን ተናግሯል።

“ውጭ ቁጭ ብለው መንገድ ዝጉ፣ በገበያ ላይ አድማ አድርጉ፣ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አግቱ ብለው ትዕዛዝ የሚያስተላልፉ አካላት በተመቻቸ ኑሮ ላይ ሆነው የደሃ ልጆችን ያስቀጥፋሉ ከትናንትናው ህወሃት በምንም አይሻሉም” ብሏል።

“የኦሮሞ ህዝብ በባህሉ ሌላውን ብሔር በጉዲፈቻና ሞጋሳ ወደ ራሱ በማምጣት አቃፊነትን መቻቻልና አብሮነትን ያስተማረ ነው” ያለው ደግሞ ወጣት ሙሐመድ ተሲ ነው።

“እኛ የኦሮሞ ወጣቶች ሀገር ማፍረስ ሳይሆን ከአባቶቻችን በወረስነው ጀግንነትና አንድነት ሀገሪቷን ገንብተን ማለፍ ነው” ብሏል።

ሌላኛው አስተያያት ሰጪ ወጣት ድሪባ ንጉሴ በበኩሉ “በመንግስት መዋቅር ውስጥ ሆነው ከውጭ ጠላት ጋር የሚሰሩ፣ የጥፋት መመሪያ የሚያስተላልፉ አመራሮች በህግ መጠየቅ አለባቸው” ብሏል።

“የኦሮሞ ህዝብ መቻቻልና አብሮነትን ከገዳ ስርዓት ነው የተማረው” ያለው ወጣት ድሪባ “ወጣቶች በተደላደለ ህይወት ውስጥ ቁጭ ብለው ትዕዛዝ የሚሰጡትን ሃይሎች መስማት የለባቸውም” ብሏል።

የአሰላ ከተማ ከንቲባ አቶ ገብሬ ዑርጌሶ በበኩላቸው የከተማዋ ወጣቶች ንብረት እንዳይወድም ሰላምን በማስጠበቅ ረገድ ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን ተናግረዋል።

ጥቂት ሰዎች የጥፋት ተልእኮ ተቀብለው ሀገር የመበጥበጥ ዓላማ እንዳላቸው ወጣቶች የተረዱበት መድረክ መሆኑንም ጠቅሰው ወጣቶች ጥፋትን ከመከላከል ባለፈ የአፍራሽ ተልዕኮ አስፈፃሚ እንዳይሆኑ የእናትና አባታቸውን ንብረትና ባህል እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

የአርሲ ዞን አስተዳደር አቶ ጀማል አሊይ እንደገለጹት የትራንስፖርት፣የንግድና የገበያ እንቅስቃሴ እንዳይኖር የሚያደርጉ የጥፋት ሃይሎች በወጣቱ ዘንድ ቦታ እንደሌላቸው ከመድረኩ መረዳታቸውን ገልጸዋል።

በዞኑ አስተማማኝ ሰላም በመስፈኑም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለሱንም ተናግረዋል።

ወጣቶች መንግስት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ከጀመረው በጎ ተግባር ጎን እንደሚቆሙ ማረጋገጣቸውን የገለጹት አቶ ጀማል፤ ንብረት በማውደምና በማቃጠል የሚገኝ ውጤት ባለመኖሩ በሰላም ማስፈን ላይ አሁንም ተባብረው መስራት እንደሚገባቸው አስገዝበዋል።

መድረኩን የመሩት የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ፕሬዘዳንት አቶ አወሉ አብዲ በበኩላቸው መንግስት የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥና አጥፊዎችን ለህግ ከማቅረብ ጎን ለጎን ንብረት የተጎዳባቸውን መልሶ ለማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

“በአሁኑ ወቅት የምግብ፣ አልባሳት፣ የዘርና የአፈር ማደባሪያ ጭምር ድጋፍ እየተደረገላቸው ነው” ያሉት አቶ አወሉ የዞኑ ማህበረሰብ ተጎጂዎችን በራሱ መልሶ ለማቋቋምና ወደ ቀደመው ህይወት እንዲመለሱ ለማድረግ በየወረዳው ኮሚቴ ተደራጅቶ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል።

በድርጊቱ የተሳተፉ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥና በህብረተሰቡ ዘንድም ያሉ የጥፋት ተልእኮ ፈፃሚዎችን ለህግ እንዲቀርቡ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል።

የአርቲስት ሃጫሉን ሞት ተከትሎ በአሰላ ከተማና በአርሲ ዞን በተፈጠረው ሁከትና ግርግር የሰው ህይወት በማጥፋትና ንብረት በማውደም የተጠረጠሩ ከ1ሺህ 300 በላይ ግለሰቦች ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ከአስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። (ኢዜአ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: arsi, jawar massacre

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule