የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከደቡብ ሱዳን አቻው ናሽናል ሴኩሪቲ ሰርቪስ ጋር በጋራ ለመስራት በደረሰው ስምምነት መሰረት ለሀገሪቱ የደኅንነት ተቋም አመራሮች በከፍተኛ የመረጃና ደህንነት አመራር ኪነሙያ ስልጠና በመስጠት አስመርቋል፡፡በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ስር በሚገኘው ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ስልጠና የወሰዱት የደቡብ ሱዳን የደኅንነት ተቋም አባላት የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ የተገኙት የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ የሁለቱ ሀገራት የደህንነት ተቋማት በመረጃ ልውውጥ፤ ሽብርተኝነትን በመዋጋት፤ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመቆጣጠር እና ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን በመከላከል ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን በጋራ ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ የጋራ የደኅንነት ስጋቶችን ለማስወገድ እንዲሁም … [Read more...] about የኢትዮጵያ ደኅንነት የደቡብ ሱዳን ደኅነቶችን አሠልጥኖ አስመረቀ
Archives for February 2022
ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው
በፌደራል እና በክልል የፀጥታ ኃይሎች ጠንካራ እርምጃ ተወስዶበት ከተበታተነ በኋላ ንፁሃን ላይ ጥቃት እየፈፀመ ያለውን አሸባሪው ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው ሲል የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ። ጠንካራ የህዝብ አደረጃጀት በመፍጠር በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተሰራው ኦፕሬሽን የሽብር ቡድኑ ከበፊት ቁመናው እና ይዞታው መዳከሙን የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰዋል። ጠንካራ እርምጃ ተወስዶበት የተበታተነው አሸባሪው ቡድን በተለያዩ ቦታዎች ንፁሃንን የማጥቃት የተለመደ የጥፋት ድርጊቱን እየፈፀመ ነው ብለዋል። ይህን የጥፋት ድርጊቱን ለማስቆም በፌደራል እና በክልል የፀጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መልኩ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት። በመንግሥት መዋቅር ላይ ሆነው ከአሸባሪው ሸኔ ጋር በማበር በህዝብ እና … [Read more...] about ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው
የቦይንግ አዉሮፕላን በተከሰከሰበት ስፍራ ለተጎጂዎች መታሰቢያ ሊገነባ ነው
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ 302 ቦይንግ 737-800 ማክስ አውሮፕላን የመከስከስ አደጋ በደረሰበት ስፍራ ለሚገነባው ሀውልትና ፓርክ የወጣውን ዓለም አቀፍ የንድፍ ውድድር የኢትዮጵያዊው አርክቴክት አለበል ደስታ ድርጅት አሸናፊ መሆኑ ታውቋል። በምስራቅ ሸዋ ዞን ግምቢቹ ወረዳ ለሚሰራው ይሄው የመታሰቢያ ሀውልት እና ፓርክ በ4 ሄክታር መሬት ላይ ሊገነባ የታሰበ ሲሆን ቦታው የማስታወሻ፣ የአረንጓዴ ቦታና የውጪ መሰብሰቢያ ስፍራ ያካተተ ነው ተብሏል። የአርክቴክት አለበል ደስታ ድርጅት ውድድሩን በማሸነፉ የ10 ሺህ ዶላር ሽልማት ሲያገኝ ሁለተኛ የወጣው ባይቦን አማካሪ አርክቴክቶችና መሀንዲሶች ድርጅት 7ሺህ ዶላር እንዲሁም በረከት ተስፋዬ አማካሪ አርክቴክቶችና መሀንዲሶች ድርጅት ሶስተኛ በመውጣት የ5 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆነዋል። አርክቴክቱ ከዚህ ቀደምም … [Read more...] about የቦይንግ አዉሮፕላን በተከሰከሰበት ስፍራ ለተጎጂዎች መታሰቢያ ሊገነባ ነው
“ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት ውይይት አድርገዋል። ከውይይታቸው በኋላም የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል። ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ የተሰጠ መግለጫ በዛሬው እለት የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በመስቀል አደባባይና በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ቦታዎች በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ የጋራ ውይይት አድርገናል፡፡ ውይይቱ በፍጹም ቅን ልቡና፣ መደማመጥና መግባባት በተሞላበት ስሜት ተካሂዷል፡፡ በመሆኑም በውይይቱ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመስቀል አደባባይና … [Read more...] about “ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ
ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥና 19 ሺህ ጥይት በቁጥጥር ሥር ዋለ
ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሳንጃ ከተማ በሁለት ባጃጆች ተጭኖ በድብቅ ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥና 19 ሺህ ጥይት በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ። ሽጉጡና ጥይቱ በቁጥጥር ሥር የዋለው በላይ አርማጭሆ ወረዳ ልዩ ስሙ "ኢትዮጵያ ካርታ" በተባለው ቦታ መሆኑን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ሚዲያ ዋና ክፍል ሃላፊ ኮማንደር እንየው ውብነህ ተናግረዋል። ትናንት ከቀኑ 7 ሰዓት አካባቢ በባጃጆች ተጭኖ ወደ ጎንደር ከተማ ለማስገባት ሲሞከር የፀጥታ ሃይሉ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ መቆጣጠር መቻሉን አስታውቀዋል። ሽጉጡና ጥይቱ በሰሌዳ ቁጥር 1-25591 እና 1-39321 አ.ማ በሆኑ ሁለት ባለ ሦስት እግር ባጃጆች አማካኝነት ተደብቆ በመጓጓዝ ላይ ሳለ እንደተገኘ ኮማንደሩ ገልጸዋል። ኮማንደር እንየው እንዳሉት፤ በአሁኑ ወቅት … [Read more...] about ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥና 19 ሺህ ጥይት በቁጥጥር ሥር ዋለ
የትምህርት ሚኒስቴር እና ኢንሳ በጋራ ለመስራት መከሩ
ፈተና መስረቅ መላ ሊበጅለት ይሆን? የትምህርት ሚኒስቴር እና ኢመደኤ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የምርምር፣ ልማት እና ስልጠናዎች ላይ በጋራ መስራት መከሩ። የትምህርትሚኒስቴር እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን (ኢመደኤ) የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የምርምር፣ ልማት እና ስልጠናዎች ላይ በጋራ መስራት በሚያስችላቸዉ ጉዳይ ላይ መምከራቸው ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን (ኢመደኤ) ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸው ወቅት የኤጀንሲውን የሳይበር ተሰጥዎ ልማት ማዕከልን፣ በኤጀንሲዉ ለምተዉ በዲጂታል ኤግዚብሽን ማዕከል የቀረቡ ምርት እና አገልግሎትን እንዲሁም የኢመደኤ ሠራተኞችና የኃላፊዎችን ቢሮዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሚኒስትሩ ከኢመደኤ ከፍተኛ … [Read more...] about የትምህርት ሚኒስቴር እና ኢንሳ በጋራ ለመስራት መከሩ
“ነገርን ከሥሩ ውሃን ከጥሩ”
የአማራ ሕዝብ ምንም አይነት የመሰረተ ልማት ባልነበረበት፣ የግንኙነት አውታሮች እጅግ ኋላ ቀር በሆኑበት ሁኔታ አንድነቱን አስጠብቆ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን ገንብቷል። የባህል መስተጋብሩና ሌሎች ማህበራዊ እውነታዎቹ ከራሱ አልፎ ኢትዮጵያን ድርና ማግ ሆኖ አስተሳስሯል። የሁለቱ ታላላቅ ኃይማኖቶች (ክርስትና እና እስልምና) መንፈሳዊ መሪዎች መፍለቂያ መሆኑ አጥር የማይበጅለት አቃፊና ተጋሪ የማንነት ባለቤት አድርጎታል። ለዚህ በርካታ ማሳያዎችን ማቅረብ የሚቻል ቢሆንም የነገረ-ፍሬየ መዳረሻ አይደለምና እዘለዋለሁ። ሊሰመርበት የሚገባው የአማራ ሕዝብ አንድነት ግን የሰላሳ ዓመታት ሳይሆን በሺህ የሚቆጠሩ ዓመታትን የተሻገረ ነው። የዳማት ዙፋን ወራሽ፣ የአክሱም ሥልጣኔ ባለቤት ነው!! ይህ የአማራ ያገጠጠ ሃቅ በትህነግ ዘመን ለመፍጠር ከታሰበው አማራ እና ፖለቲካዊ … [Read more...] about “ነገርን ከሥሩ ውሃን ከጥሩ”