ከአራት ቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ለ“ካቢኔያቸው” ወደ ሁለት ሰዓት የሚፈጅ ሥልጠና ሰጥተዋል። ይህ በሥነአመራር ጥበብ ላይ ያተኮረው የጠ/ሚ/ሩ ገለጻ በኮሌጅ ደረጃ የሚሰጥ ትምህርት ተጨምቆ የቀረበበት ነው። በካቢኔ አባልነት የተቀመጡት ግለሰቦች አንዳንዶቹ በመደነቅ፣ ሌሎቹ በመገረም፣ አፋቸውን በመያዝ አንዳንዶች በመናደድ ሌሎች ደግሞ አልገባ ብሏቸው ግራ በመጋባት ሲያደምጡ ተስተውለዋል። በርካታዎቹ ከየ“ዲግሪ ወፍጮ ቤቱ” የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃን ተብለው ከሚችሉት በላይ ዲግሪ ተሸክመው የሚንገዳገዱ በመሆናቸው የጠቅላዩ ንግግር አቅማቸውን የማይመጥን ሆኖ እንዳገኙት ከፊታቸው ላይ የሚታይ ነበር። ምክንያቱም እነርሱን ወደዚህ ዓይነት ማዕረግ እንዲመጡ ያደረጋቸው ራሱ ከዲግሪ ወፍጮ ቤቶቹ በአንዱ በፖሰታ ቤት ዲግሪውን የተቀበለው መለስ ዜናዊ ነበር። መለስ አካባቢውን … [Read more...] about ጠ/ሚ/ሩና ውቅር የማይገባው “የዲግሪ ወፍጮ” ምሩቃን ካቢኔ
Archives for May 2018
ጠባብነት እና ትምክህት
ከ2 አመት በፊት፦ ጠባብነት እና ትምክህት ኢህአዴግ እንደ ፓርቲና መንግስት የችግሮች ሁሉ መንስዔ አድርጎ የሚወስደው የጥገኝነት አስተሳሰብና ተግባራትን ነው። ለህዝቡ ሰላም እና ለፌደራል ሥርዓቱ አደጋ ናቸው ከሚላቸው ውስጥ፡- ጠባብነት እና ትምክህተኝነት የሚሉት በዋናነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ ቃላት በመንግስት ድክመት ምክንያት ለተፈጠሩ ችግሮች ሌሎችን ተጠያቂ (externalize) ለማድረግ ነው። በመሠረቱ “ትምክህተኛ” የሚለው እሳቤ የአማራ ብሔር ተወላጆችን በባህላቸውና በታሪካቸው ላይ ያላቸውን የራስ መተማመን ስሜት የሚሸረሽር ነው። በዚህ መልኩ የሚደረገው ተፅዕኖ በአማራ ልሂቃን ላይ የማንነት ቀውስ (identity crisis) ይፈጥራል። በዚህ መሰረት፣ አንድ ሰው በአማራነቱ ብቻ “ትምክህተኛ” እየተባለ ታሪኩና ማንነቱ እንደ ጥፋት ሲቆጠር በውስጡ የብሔርተኝነት ስሜት … [Read more...] about ጠባብነት እና ትምክህት
ታሪክ የወረሰ ትውልድ፣ ያልተወለዱ ህልሞችና የማዋለጃው መንገድ
የዛሬ 150 ዓመት በሕይወት ብንኖር ኑሮ ብዙዎቻችን ምንአልባት ሁላችንም በዘመኑ ከኖሩት አባቶቻችን ጋር በአንድ የአስተሳሰብና የኑሮ ዘይቤ ምህዋር ላይ እንደምንተም እገምታለሁ። የነበረውን የህይወት ከባቢ እንደዘላለማዊና የማይቀየር እውነት በመቁጠር እንደምንመላለስ አስባለሁ። ፈጣሪ በማይቋረጠው የዘመናት ጐዳና ላይ በየዘመኑ የሚያስነሳቸው ታላላቆች ግን ጨለማ ባጠቆረው ሰማይ ላይ እንደሚበር አብሪ ኮከብ ለሁሉም እንዲታዩ ሆነው ይምዘገዘጋሉ። ኢትዮጵያ በታሪክ ደርሳናቷ ላይ የሚንቦገቦጉ፣ የዘመንን ጢሻ እየመነጠሩ ከትውልዶች ጋር የሚተሙ ኢትዮጵያውያን ጀግኖች ነበሯት። አሏት። ከእነርሱ መካከል ዛሬ ከምንዘክራቸው አፄ ቴዎድሮስ አስቀድመን የመጀመሪያው እረድፍ ላይ ማንን ልናቆም እንችላለን? እውቁ የዘመናዊ ታሪክ ፀሐፊው ሊቀ - ጠበብት ባህሩ ዘውዴ Society and State in … [Read more...] about ታሪክ የወረሰ ትውልድ፣ ያልተወለዱ ህልሞችና የማዋለጃው መንገድ
ወልቃይት እንደ ካሽሚር
የወልቃይት መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች እና የዋልድባ መነኮሳትን ጨምሮ ከመቶ በላይ ከእስር ቤት የተለቀቁ የዴሞክራሲና የፍትህ ተቆርቋሪ ታጋዮች በታሪካዊቷ ጎንደር ከተማ ግንቦት 2 ቀን 2010 ዓ.ም በተደረገላቸው የክብር ራት ግብዣ ላይ የተገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ለታዳሚው ያደረገውን ንግግር ከተመስገን ባገኘነው ፈቃድ መሠረት ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ አንባቢያን እንደወረደ በሚከተለው መንገድ አቅርበነዋል። በዕለቱም ለህሊና እስረኞች የተለያየ ስጦታም እንደተበረከተ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል። እዚህ የተሰበሰባችሁ ታላላቆቼም፣ ታናናሾቼም በመጀመሪያ እንኳን ለዚህ ዕለት አበቃችሁ፤ አበቃን። በተለይም ባለፉት ሁለት አስርታት የወልቃይትን ሕዝብ የማንነት፣ የፍትሕ፣ የዴሞክራሲ እና የፖለቲካ ጥያቄ አደባባይ እንዲወጣ በተወለዳችሁበት አፈር ላይ ተተክላችሁ ለከፈላችሁት ውድ ዋጋ ጥልቅ … [Read more...] about ወልቃይት እንደ ካሽሚር
የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ ፓርቲ መግለጫ
መግለጫውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው። … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሔራዊ ፓርቲ መግለጫ
ጠ/ሚ/ር ዓቢይ እና ህወሓቶች፡ ለይቶ ማሰር ወይስ አብሮ መሥራት?
ኢህአዴግ ውስጥ ስለተደረገው አመራር ለውጥና ለውጡ የተካሄደበትን ሁኔታ አስመልክቶ የተለያዩ ሃሳቦችና አስተያየቶች ይሰጣሉ፡፡ አንዳንድ ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ የአመራር ለውጥ ያደረገው በሀገሪቱ እየታየ ያለውን ህዝባዊ አመፅና ተቃውሞ ለመግታት እንደሆነ ሲገልፁ ይሰማል፡፡ በሌላ በከል አንዳንድ የህወሓት/ኢህአዴግ ደጋፊዎች የአመራር ለውጡ የተካሄደው በተለመደው የፓርቲው ደንብና ስርዓት እንደሆነና የአዲሱ ሊቀመንበር ምርጫ በአባል ድርጅቶች የጋራ መግባባት የተመሠረተ እንደሆነ ሲገልፁ ይሰማል፡፡ ነገር ግን፣ ሁለቱም አመለካከቶች በተሳሳተ ግንዛቤ ላይ የተመሠረቱ ናቸው፡፡ ምክንያቱም እንዲህ ያሉ አስተያየቶች፤ አንደኛ፦ የለውጡን መነሻ ምክንያት በጥልቀት ካለመረዳት፣ ሁለተኛ፦ የአመራር ለውጡ የተካሄደበትን ሁኔታ በግልፅ ካለመገንዘብ የመነጩ ናቸው፡፡ ኢህአዴግ የአመራር ለውጥ እንዲያደርግ … [Read more...] about ጠ/ሚ/ር ዓቢይ እና ህወሓቶች፡ ለይቶ ማሰር ወይስ አብሮ መሥራት?
አማራ የሚፈናቀለው ሆነ የሚገደለው በመንግስት ፍቃድ ነው!
ትላንት (May 15) በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አበጥር ወርቁ በተባለ የአማራ ብሔር ተወላጅ ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ግፍ ተመልክተናል፡፡ ይህ ከመሆኑ ከአንድ በፊት ደግሞ ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ527 በላይ አባወራዎች በድምሩ 2000 ከሚሆኑ ቤተሰቦቻቸው ተፈናቅለዋል፡፡ እነዚህ “ሕገ ወጥ ናችሁ” በሚል ሰበብ ተዘርፈውና ተደብድበው የተፈባቀሉት አማራዎች ህጋዊ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ያላቸው ናቸው፡፡ በባለቤትነት ለሚያስተዳድሩት መሬት በአግባቡ ግብር ይከፍላሉ! በፎቶው የሚታዩት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተሮች ባህርዳር ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ተጠልለው የሚገኙ ሶስት አባውራዎች ናቸው። እነዚህ ሰዎች ያለ ምንም መነሻ ምክንያት ከመሬታቸው አልተፈናቀሉም፣ በግፍ አልተገደሉም፡፡ ከዚህ በስተጀርባ በጥላቻና ማንአለብኝነት የናወዙ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግስት … [Read more...] about አማራ የሚፈናቀለው ሆነ የሚገደለው በመንግስት ፍቃድ ነው!
የጠ/ሚ/ር አብይን የለውጥ መንገድ ለመርዳት ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
የሚፈለገው ለውጥ ዋናው ዓላማ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈለገውን አስተዳዳሪዎቹንና የአስተዳደር ሥርዓትን በነፃነትና በዴሞክራሲ መንገድ ሊመርጥ የሚችልበትን ሥርዓት መመሥረት ነው። ህወሃት የዘረፋ ሥርዓቱን ለማቀላጠፍ እንዲመቸው ዘንድ ኢ-ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መመሪያ በማድረግ ፖለቲካውን የማጭበርበሪያ፣ ኢኮኖሚውን የመዝረፊያ፤ ዳኝነትን የመበቀያ፣ ደህነነትን የማሸበሪያና መከላከያን የማጥቂያ መዋቅሮች አድርጎ ለሃያ ሰባት አመት በኢትዮጵያ ሕዝብና በአገር ላይ ከባድ ግፍና መከራ እየፈፀመ ቆይቷል። የኢትዮጵያ ሕዝብ የመጀመሪያ ዋና ጥያቄ ይህንን ሕዝቡንና አገሪቷን ከላይ እስከ ታች በኢ-አብዮታዊ ዴሞክራሲና በኢ-ዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት በመጠፍነግ ለጥቂቶች ገነት ለአብዛኛው ሕዝብ ግን መከራና ስቃይ የሆነውን ሥርዓት በሰላማዊ መንገድ መለወጥ ነው። ዶ/ር አብይ ከሚናገሩትም ሆነ ከገዱ ቡድንና … [Read more...] about የጠ/ሚ/ር አብይን የለውጥ መንገድ ለመርዳት ምን ማድረግ ያስፈልጋል?
ዘራፊዎችን ለማጋለጥ ሁሉም ይተባበር!!
በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው በደል፥ ሰቆቃ፥ ስደታና ሞት ቀጥሎሏል። በአንድአማራ ጽኑ እምነት አሁን ካለው የባሰና የከፋ ከመምጣቱ በፊት ጠላት በመቀነስ ላይ ያተኮረ ትግል መደረጉ ተገቢ ነው በሚል ሙሉ እምነት ይዘን ዘረኛውና እብሪተኛው የትግራይ ጽንፈኛ ቡድን ላይ በማነጣጠር ትግላችንን አጠናክረን ይዘን እንገኛለን። ይህ ጽንፈኛ ተገንጣይ የትግራይ ወያኔ ቡድን አማራውን በግንባር ቀድምትነት ጠላት አድርጎ በመፈረጅ በተመቸው አጋጣሚ ሁሉ በደል እየፈጸመ ይገኛል። በቅርቡ የተቀየሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም የአማራውን ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄና የመኖር ህልውና በማረጋገጥ ረገድ እየሰሩ አለመሆናቸዉን ሁሉም የሚያውቀው ሃቅ ነው። ምንም እንኳን ጠ/ሚ አብይ አማራው የሚፈልገውን ጥያቄ ለመመለስ ባይችሉም በሚያደርጓቸው ትግሎች ላይ የጋራ ጠላታችንን የሚያነጣጥር ከሆነ አብረን … [Read more...] about ዘራፊዎችን ለማጋለጥ ሁሉም ይተባበር!!
ነፃ ያልወጣች ሠንደቅ
አዎ፤ አውሮፓዊው ቅኝ ገዢ ጣሊያን አድዋ ላይ ድል ሆኗል በ1888 ዓ/ም። በኢትዮጵያና ኢትዮጵያን በሚወክለው ቀስተ ደመናዊ ሠንደቅ ዓላማዋ ላይ ግን ከትውልድ የዘለለ ቂም ቋጥሮ የደማ ልቡን በመዳፉ ደግፎ በተቆረጠው ቋንጃው እያነከሰ አንድ እግሩን ኤርትራ ላይ ልብና ሌላ እግሩን ጣሊያን - አውሮፓ ላይ አድርጎና ጠቅላይ ሚኒስትሩን ፍራንቺስኮ ክሪስፒን ከሥልጣን አባርሮ ድፍን ጣሊያን ሀዘን ተቀመጠ። አርባ ዓመት ሲታመምና ሲያገግም ኖረ። ጣሊያን በኢትዮጵያና በሠንደቋ ላይ ለአርባ ዓመት ያረገዘው ቂም ዱቼንና ፋሽስት ፓርቲን ወለደ። ለጣሊያን ትንሳዔ ኢትዮጵያ መሥዋዕት መሆን አለባት ሲል እነሆ ዱቼ በሮም አደባባይ ተጣራ። ሙሶሎኒ ኢትዮጵያን በመሥዋዕትነት ለተዋረደችው ጣሊያን ትንሳኤ አቀረበ። አውሮፓ አጨበጨበ፤ ቪቫ ዱቼ ሲል ደገፈ። ጥቁር ለባሽ የፋሽስት ጦር ከጣሊያን ጫፍ እስከ ጫፍ … [Read more...] about ነፃ ያልወጣች ሠንደቅ