• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አማራ የሚፈናቀለው ሆነ የሚገደለው በመንግስት ፍቃድ ነው!

May 17, 2018 06:44 am by Editor 1 Comment

ትላንት (May 15) በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አበጥር ወርቁ በተባለ የአማራ ብሔር ተወላጅ ላይ የተፈፀመውን አሰቃቂ ግፍ ተመልክተናል፡፡ ይህ ከመሆኑ ከአንድ በፊት ደግሞ ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ከ527 በላይ አባወራዎች በድምሩ 2000 ከሚሆኑ ቤተሰቦቻቸው ተፈናቅለዋል፡፡

እነዚህ “ሕገ ወጥ ናችሁ” በሚል ሰበብ ተዘርፈውና ተደብድበው የተፈባቀሉት አማራዎች ህጋዊ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ያላቸው ናቸው፡፡ በባለቤትነት ለሚያስተዳድሩት መሬት በአግባቡ ግብር ይከፍላሉ! በፎቶው የሚታዩት የይዞታ ማረጋገጫ ደብተሮች ባህርዳር ጊዮርጊስ ቤተ ክርስትያን ተጠልለው የሚገኙ ሶስት አባውራዎች ናቸው።

እነዚህ ሰዎች ያለ ምንም መነሻ ምክንያት ከመሬታቸው አልተፈናቀሉም፣ በግፍ አልተገደሉም፡፡ ከዚህ በስተጀርባ በጥላቻና ማንአለብኝነት የናወዙ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎች እጅ አለበት፡፡ ለምሳሌ ከላይ የተጠቀሱት አባወራዎች በሚያዚያ ወር መጀመሪያ ላይ ከመፈናቀላቸው በፊት ለምሳሌ የበሎ ዲዴሣ ቀበሌ ሃላፊ የሆነው አቶ ንጉሱ ጀርሞሣ በቀን 16/07/2010 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ መሠረት እስከ መጋቢት 30/2010 ዓ.ም በአከባቢው የሚኖሩ አማራዎች ንብረታቸውን ሸጠው ወይም ጥለው እንዲወጡ አዝዟል፡፡

በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የሚኖሩ አማራዎችን ያለ አግባብ እንዲፈናቀሉና እንዲገደሉ የሚያደርጉት እንደ አቶ ንጉሱ ያሉ የቀበሌ ሃላፊዎች አይደሉም፡፡ ከዚያ ይልቅ፣ በወረዳ፥ ዞን፥ ክልል፥ እንዲሁም በፌደራል ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎች እጅ አለበት፡፡ ከታች እስከ ላይ ያሉት የመንግስት ሃላፊዎች ለአማራ ህዝብ ባላቸው ሥር-የሰደደ ጥላቻ ምክንያት በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አማራዎችን በማፈናቀልና በመግደል ተሳታፊ ባይሆኑ እንኳን አማራዎች ለሚያሰሙት ብሶትና ቅሬታ ግድየለሽ መሆናቸው እርግጥ ነው፡፡ ላለፉት 27 አመታት በኦሮሚያ፥ ደቡብ፥ ጋምቤላ፥ ትግራይ፥ እንዲሁም በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የአማራ ብሔር ተወላጆች ሲገደሉና ሲፈናቀሉ ማስቆም ይችሉ ነበር፡፡

ዛሬ ላይ ከ2000 በላይ አማራዎች ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈናቀሉት፣ አበጥር ወርቁ በተባለው ግለሰብ ላይ አሰቃቂ ግፍ የተፈፀመው ትላንት ተመሣሣይ ድርጊት የፈፀሙ ሰዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው የማያዳግም እርምጃ ባለመወሰዱ ነው፡፡ባለፈው የሚያዚያ ወር አማራዎች ከክልሉ የተፈናቀሉት መጋቢት ላይ የበሎ ዲዴሣ ቀበሌ ሃላፊ የሆነው አቶ ንጉሱ ጀርሞሣ በፖሊስ ለፍርድ ባለመቅረቡ ነው፡፡ አቶ ንጉሱ በአከባቢው የሚኖሩ አማራዎች እንዲፈናቀሉና እንዲገደሉ የሚያደርገውን ትዕዛዝ ያስተላለፈው የቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል የርዕሰ መስተዳደር እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ለፍርድ ባለመቅረባቸው ነው፡፡

የቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል የርዕሰ መስተዳደር እና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጂሬኛ በዚህ አመት የጥቅምት ወር (እ.አ.አ በ04/03/2017 ዓ.ም ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ “የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የትግራይ ክልል ተወላጆችን 600ሺህ ብር እና የአውሮፕላን ትኬት ሸፍኖ ልኳቸዋል”። በክልሉ የሚገኙ የአማራ ክልል ተወላጆች በተመለከተ ደግሞ “በሕገ ወጥ መንገድ የያዙት መሬት እንዲለቁና ወደ መጡበት ክልል እንዱመለሱ ተደርጓል” ብለው ነበር፡፡ ይህ የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣን ህወሓት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ በደቡብ አፍሪካ የወደቀው የአፓርታይድ ስርዓት ዛሬም ድረስ ኢትዮጲያ ውስጥ በተግባር እንዳለ በመንግስት ሚዲያ ላይ በይፋ ተናግሮ ማንም ምንም አላለውም፡፡

አቶ ሰለሞን ጂሬኛ የቤኒሻንጉል ግሙዝ ክልል በአማራዎች ላይ ተግባራዊ ያደረገውን አድልዎና ግፍ በይፋ በራሱ አንደበት ያረጋገጠበት ምክንያት ምንድነው? አጭርና ግልፅ፣ መንግስታዊ ስርዓቱ በአማራ ህዝብ ላይ የፈለገውን አሰቃቂ ተግባር እንዲፈፅም ይፈቅድለታል፡፡ ምክንያቱም በህወሓት መሪነት የተዘረጋው መንግስታዊ ስርዓት ዓላማና ግቡ የአማራን ህዝብ መበቀል ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ “የአማራ የበላይነት፥ ነፍጠኛ፥ ትምክህተኛ፥ የድሮ ስርዓት ናፋቂ፥…” እያለ በአማራ ህዝብ ላይ ዘወትር ጥላቻ ይሰብካል፡፡

በዚህ መሠረት በቂም-በቀል የታወሩ ሰዎች በኦሮሚያ፥ ደቡብ፥ ጋምቤላ፥ ትግራይና ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልሎች በሚገኙ አማራዎች ላይ በማንአለብኝነት አሰቃቂ ግፍና በደል ሲፈፀሙ በሁሉም ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ሃላፊዎች ነገሩን በቸልታና ግድየለሽነት እንዳልሰማ-እንዳላየ ሆነው ያልፉታል፡፡ በመሆኑም በአማራ ህዝብ ላይ አሰቃቂ በደልና ግፍ እንዲፈፀም በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ፈቅደዋል፡፡ በአጠቃላይ የአማራ ህዝብ የሚፈናቀለው ሆነ የሚገደለው በመንግስት ፍቃድ ነው!

ስዩም ተሾመ

ምንጭ፤ Ethiopian Think Thank Group by Seyoum Teshome

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: abiy, amhara, andm, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Eunetu Yeneger says

    May 24, 2018 05:34 pm at 5:34 pm

    ሰው ከመሆን ደረጃ ለምን ወደ ዘር ወርድን?
    የትኛው ይቀድማል?ሰውነት ወይስ ትግሬነት/ኦሮሞነት አማራነት/ሃድያነት/ ወዘተ?

    የአማራ ሕዝብ መከራ ምንጩ በእውነት ምንድነው?
    መከራ ያበዙበትን እነዚህን ሰዎች በእውነት ምን አድርጓቸው ነው?
    በእውነት አማራ በአማራነቱ በትግራይ፣ በኦሮሞና በሌሎች ላይ የሠራው ግፍ አለ?
    አማራና አማርኛ ለምን በራሳችን ወገኖች ተጠላ?

    የሰማሁትን እንካችሁ፡

    1)አንድ የኤርትራ ሕጻን ስታድግ ምን መሆን ትሻለህ ሲባል
    የጦር አውሮፕላን አብራሪ! ለምን እሱን ሥራ መረጥክ?
    ኢትዮጵያያን ለመደብደብ ብሎ እርፍ!
    በወላጆቹና በሰፈሩ ቂመኛ ሰዎች ሲባል የሰማውን!!

    2) አንድ ለጋብቻ የደረሰ እውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ፡
    አብራው ቤ/ክ የምታመልክን የወለጋ ወጣት ሴት
    ለጋብቻ ከልቡ በእውነት ይጠይቃታል፤
    አንተን በፍጹም አላገባሃም ብላው እርፍ!
    ምነው???? ሲላት
    አማራ ስለሆንክ ነው።
    /ኢሕአዴግ በገባ ከ3 ዓመት በኋላ የተፈጸመ እውነት/

    ከዚህ የበለጠ ከሰውነት ደረጃ መውረድ ምን አለ????
    ኧረ እናስተውል???ምነው ሰው ሰው መሆኑን እረሳ??

    ልጄ ሰለሞን ሆይ!
    ሰው ሁን!!!
    /1ኛ ነገሥት 2፡1-4/

    Therefore, are we really CHRISTIAN ?????

    Eunteu Yeneger

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule