• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠባብነት እና ትምክህት

May 20, 2018 06:07 am by Editor 3 Comments

ከ2 አመት በፊት፦ ጠባብነት እና ትምክህት

ኢህአዴግ እንደ ፓርቲና መንግስት የችግሮች ሁሉ መንስዔ አድርጎ የሚወስደው የጥገኝነት አስተሳሰብና ተግባራትን ነው። ለህዝቡ ሰላም እና ለፌደራል ሥርዓቱ አደጋ ናቸው ከሚላቸው ውስጥ፡- ጠባብነት እና ትምክህተኝነት የሚሉት በዋናነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ ቃላት በመንግስት ድክመት ምክንያት ለተፈጠሩ ችግሮች ሌሎችን ተጠያቂ (externalize) ለማድረግ ነው።

በመሠረቱ “ትምክህተኛ” የሚለው እሳቤ የአማራ ብሔር ተወላጆችን በባህላቸውና በታሪካቸው ላይ ያላቸውን የራስ መተማመን ስሜት የሚሸረሽር ነው። በዚህ መልኩ የሚደረገው ተፅዕኖ በአማራ ልሂቃን ላይ የማንነት ቀውስ (identity crisis) ይፈጥራል። በዚህ መሰረት፣ አንድ ሰው በአማራነቱ ብቻ “ትምክህተኛ” እየተባለ ታሪኩና ማንነቱ እንደ ጥፋት ሲቆጠር በውስጡ የብሔርተኝነት ስሜት ያቆጠቁጣል።

በተመሣሣይ “ጠባብ ብሔርተኛ” የሚለው እሳቤ የኦሮሞ ህዝብ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ያለውን ድርሻ የሚያንኳስስ፤ በሀገሪቱ አንድነት ላይ ያለውን የምሶሶነት ሚና ወደ አንድ ግንጣይ ቅርጫፍነት የሚያሳንስ ነው። በሀገሪቱ የፖለቲካ መዋቅር ውስጥ የሚገባውን መጠየቁ እንደ ጥፋት ተቆጥሮ “በጠባብነት” ሲፈረጅ በኃይል ሚዛኑን ውስጥ የሚገባውን ድርሻ ለመያዝ በራሱ መንቀሳቀስ ይጀምራል።

ከላይ በተገለፀው መሠረት ላለፉት 25 አመታት ኦሮሞ “ጠባብ ብሔርተኛ” እየተባለ በሀገሪቱ አንድነት ውስጥ የሚገባውን ጥቅምና ኃላፊነት ተነፍጎ ስለቆየ የፖለቲካ አሰላለፉን በሂደት ከብሔርተኝነት ወደ “የኢትዮጵያ አንድነት” እየቀየረ መጥቷል። አማራ ደግሞ “የትምክህት አንድነት” በሚል እንደ ብሔር የሚገባውን ጥቅምና ኃላፊነት ተነፍጎ ስለቆየ የፖለቲካ አሰላለፉን በሂደት ከአንድነት ወደ “አማራ ብሔርተኝነት” እየቀየረ መጥቷል። በዚህ የሽግግር ሂደት የሁለቱ ሕዝቦች ጥያቄ ከተቃራኒ ጫፎች ወደ መሃል በመምጣት አሁን ላይ ያልተጠበቀ ጥምረት ፈጥሯል።

ይህ አንደ ቀድሞው በሁለት ተቃራኒ ፅንፈኞች መካከል የተፈጠረ ጥምረት አይደለም። ከዚያ ይልቅ፣ ሁለቱም ሕዝቦች በሆኑትና በሚገባቸው ልክ ጥቅምና ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ በሚያደርጉት የጋራ እንቅስቃሴው የተፈጠረ ጥምረት ነው። በመሆኑም፣ የኦሮሞና አማራ ህዝቦች የፖለቲካ እንቅስቃሴ ረገድ እየታየ ያለው ጥምረት በእኩልነት መርህ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን አስችሎታል።

ከ2 አመት በኋላ፦ ጠባብነት እና ትምክህት

“ኦሮማራ” በሚል የሚታወቀው የሁለቱ ህዝቦች ትብብርና አንድነት በሀገራችን ፖለቲካ ውስጥ ትልቅ ለውጥ አምጥቷል። በዋናነት በኦህዴድና ብአዴን መካከል የተፈጠረውን ጠንካራ ጥምረት መጥቀስ ይቻላል። በሀገራችን ፖለቲካ መሠረታዊ ችግር የነበረው የህወሓት የበላይነት እንዲያከትም በማድረጉ ሂደት የማይተካ ሚና ተጫውቷል። ስለዚህ አዲሱ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣት የቻሉት በዚህ ጥምረት አማካኝነት ነው።

ስለዚህ ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን ከመጣበት ግዜ ጀምሮ ቅድሚያ ሊሰጣቸው ከሚገቡ ተግባራት ጠባብነት እና ትምክህት ከመንግስት መዝገበ-ቃላት ውስጥ መሰረዝ ነው። ምክንያቱም፣ አንደኛ፦ የእነዚህ ቃላት አጠቃቀም የኦሮሞና አማራ ህዝቦችን የእኩልነት ጥያቄ ለማፈን፥ ለማጣጣል፥ ለማንኳሰስና ተቀባይነት እንዳያገኙ ለማድረግ ያለመ ነው። ሁለተኛ፦ በኢህአዴግ የአመራር ለውጥ እንዲመጣ የቻለው እነዚህን አፍራሽ ቃላትና አመለካከት በመቃወም በተፈጠረ የኦሮማራ ጥምረት አማካኝነት ነው።

በመሆኑም ዶ/ር አብይ ጠ/ሚኒስትር ሆኖ ከተመረጠበት ዕለት አንስቶ ጠባብነት እና ትምክህት የሚሉት ቃላት ከስነ-ምግባር ሆነ ነባራዊ እውነታ ያፈነገጡ እንደሆኑ ታሳቢ በማድረግ ከመዝገበ-ቃላት ውስጥ መሰረዝ ነበረባቸው። ነገር ግን፣ ዶ/ር አብይ ወደ ስልጣን ከመጣ ከሁለት ወራት በኋላ እነዚህ ቃላት በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ ይገኛል። ለምሳሌ የፌዴራል መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት 27ኛው የግንቦት 20 የድል በዓልን አስመልክቶ ባዘጋጀው የመወያያ ሰነድ ላይ ጠባብነት እና ትምክህት የኢትዮጵያ ፌዴራል ስርዓት ዋና ተግዳሮቶች መሆናቸው ተገልጿል፦

በተጠቀሰው ሰነድ መሠረት የፌዴራል ስርዓቱ የመጀመሪያ ተግዳሮት “ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት አለመዳበር” እንደሆነ ይገልፃል፦

“ብዝሃነትን በብቃት ለማስተናገድ የሚያስችል የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ በሚፈለገው ደረጃ ባለመዳበሩ ሳቢያ ጥበትና ትምክህት በብሄር ካባ የግል ጥቅም ማሳደጃ መሆን በመጀመራቸው የፌዴራል ስርዓታችን የመጀመሪያ ተግዳሮቶች ሆነዋል። የዴሞክራሲያዊ ብሔርተኝነትና የዴሞክራሲያዊ አንድነት ጠላት የከረረ ብሔርተኝነት ነው። የከረረ ብሔርተኝነት ትምክህትን ወይንም ጠባብነትን ይወልዳል። ትምክህት በገዥ መደብነት በመሰለፍ የሁሉንም ብሄር ብሄረሰቦች ማንነት በስመ ኢትዮጵያዊነት ካባ የሚንድ አስተሳሰብ ነው። ጠባብነት ደግሞ ተስፈኛ የሆነ የገዥ መደብ አስተሳሰብ ሲሆን ጭቆናን ምክንያት በማድረግ ያለአግባብ በሚሰጠው መፍትሄ የብሄሩ ገዥ መደብ የመሆን ፍላጎትን የሚያሳይ ነው። ሁሉም አስተሳሰቦች ፀረ እኩልነትና ፀረ ዴሞክራሲ ናቸው። እነዚህ አስተሳሰቦች ኢ-ምክንያታዊነትን በማጎልበትና በማሳደግ አንዱን ህዝብ በማቅረብ ሌላውን በማራቅ ፋሺስታዊ የዘር ፍጅትን የሚያመጡ አስተሳሰቦች ናቸው። በተለይም በአሁኑ ጊዜ ጥገኝነት፣ ኪራይ ሰብሳቢነት የጋራ አጀንዳቸው በመሆኑ ምክንያት ጠባብነትና ትምክህት በአንድነት የሚሰለፉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። በዓለማችን በከረረ ብሔርተኝነት የተነሳ በጀርመን እንዲሁም በ1990ዎቹ መጀመሪያ በጎረቤታችን ሩዋንዳ ለሚሊዮን ህዝቦች እልቂት ምክንያት ሆኗል።”

የፌዴራል ስርዓቱ ሁለተኛው ተግዳሮት “የልማታዊነት አስተሳሰብ የበላይነት አለመረጋገጥ” ሲሆን ለዚህም በመንስዔነት የተጠቀሱት ጠባብነትና ትምክህት ናቸው፦

“የፌዴራል ስርዓት ተግዳሮት ተደርገው ከሚወሰዱት መካከል ኪራይ ሰብሳቢነትና ውላጆቹ የሆኑት ትምክህትና ጥበት ናቸው። እነዚህ ሁለት ፅንፎች እርስ በርስ በመጓተት የአገራችንን የፌዴራል ስርዓት በመፈታተን ላይ ናቸው። የትምክህት ሃይሉ የቀድሞው አህዳዊ ስርዓት መመለስ አለበት፤ እኛ ካላስተዳደርነው “አንድነትና ኢትዮጵያዊነት” ሊኖር አይችልም እኛ አዋቂ ነን በማለት ኢትዮጵያዊነትን በሃይል ለመጫን የሚፈልጉ አካላት ናቸው።… ሌላኛው አካል ደግሞ አብረው የኖሩ ህዝቦችን ለመነጣጠል፣ ኢትዮጵያ የሚለውን ስያሜ ፈጽሞ መስማት የማይፈልግ፣ አብሮ የመኖር ፈይዳ የማይታያቸው፣ ያለፈው ስርዓቶች አደረሱ የተባለውን በደል አሁን ላይ ያለው ትውልድ ለማወራረድ ህዝቦችን የሚያነሳሱ፣ ንጹሃንን በማጋጨት ወደ ስልጣን መሰላል መሰቀል የሚፈልጉ ናቸው። ሁሉም ፀረ ልማትና ዕድገት ሆነው በአንድ ጎራ ተሰልፈው ፌዴራላዊ ሥርዓቱን እየተፈታተኑት ይገኛሉ።”

ምንጭ፤ Ethiopian Think Thank Group by Seyoum Teshome

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: abiy, gedu, Left Column, lemma, oromara

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    May 22, 2018 09:03 pm at 9:03 pm

    ጎልጉሎች!እንዲያው ኣሰሱን ገሰሱን ያለ ጥናት፤ ኦሮሞ ጠባብ፤ ኣማራ ትምክህተኛ ብላችሁ፤ ድፍድፉን ኣቀረባችሁልን። ጥበት እንዴት ይመነጫል?መንስዔውስ? መፍትሄውስ? የሚለውን ማየት ተገቢ ነው። ትምክህትንም እንደዚሁ። ከላይ የቀረበው የዘንጋዳ ቂጣ፤ ጠላ ወይም ስዋ ወይም ጽራይ ወይም ጉሽ ሆኖ ኣልቀረበም። ልንጠጣው ኣልቻልንም። ኣብራራልን የምትሉኝ ከሆነ፤ ኣሰማምረዋለሁ።

    Reply
  2. ኪሮስ says

    May 24, 2018 04:27 pm at 4:27 pm

    ጎልጉሎችና ሙሉጌታ፣ ትግሬ ጠባብና ትምክህተኛ እንደ ሆነ ዘነጋችሁ!

    Reply
    • Mulugeta Andargie says

      May 25, 2018 05:19 pm at 5:19 pm

      እሱንማ እኔም አልክድም። ያልኩት ጎልጉሎች አብራራልኝ እንደማለት ድፍድፉን አቀረቡልን ነው!! ቂቂቂ!

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule