• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጠ/ሚ/ር ዓቢይ እና ህወሓቶች፡ ለይቶ ማሰር ወይስ አብሮ መሥራት?

May 17, 2018 08:09 pm by Editor 2 Comments

ኢህአዴግ ውስጥ ስለተደረገው አመራር ለውጥና ለውጡ የተካሄደበትን ሁኔታ አስመልክቶ የተለያዩ ሃሳቦችና አስተያየቶች ይሰጣሉ፡፡ አንዳንድ ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ የአመራር ለውጥ ያደረገው በሀገሪቱ እየታየ ያለውን ህዝባዊ አመፅና ተቃውሞ ለመግታት እንደሆነ ሲገልፁ ይሰማል፡፡ በሌላ በከል አንዳንድ የህወሓት/ኢህአዴግ ደጋፊዎች የአመራር ለውጡ የተካሄደው በተለመደው የፓርቲው ደንብና ስርዓት እንደሆነና የአዲሱ ሊቀመንበር ምርጫ በአባል ድርጅቶች የጋራ መግባባት የተመሠረተ እንደሆነ ሲገልፁ ይሰማል፡፡ ነገር ግን፣ ሁለቱም አመለካከቶች በተሳሳተ ግንዛቤ ላይ የተመሠረቱ ናቸው፡፡ ምክንያቱም እንዲህ ያሉ አስተያየቶች፤ አንደኛ፦ የለውጡን መነሻ ምክንያት በጥልቀት ካለመረዳት፣ ሁለተኛ፦ የአመራር ለውጡ የተካሄደበትን ሁኔታ በግልፅ ካለመገንዘብ የመነጩ ናቸው፡፡

ኢህአዴግ የአመራር ለውጥ እንዲያደርግ ያስገደደው ምንድነው? በመጀመሪያ ደረጃ ከሌሎች ክልሎች በተለየ ህዝባዊ አመፅና ተቃውሞ ቀድሞ የተጀመረው በኦሮሚያ ክልል መሆኑ ይታወሳል፡፡ በተመሣሣይ ከሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በተለየ የአመራር ለውጥ ያደረገው ኦህዴድ እንደሆነ ይታወሳል፡፡ በመቀጠል ኢህአዴግ ውስጥ የአመራር ለውጥ እንዲመጣ ግንባር-ቀደም ሚና የተጫወተው አዲሱ የኦህዴድ መሆኑ እርግጥ ነው፡፡

በመጨረሻም የኢህአዴግ ሊቀመንበርና የሀገሪቱ ጠ/ሚኒስትር የሆነው የኦህዴድ ሊቀመንበር ዶ/ር አብይ አህመድ ናቸው፡፡ በመሆኑም በኢህአዴግ ውስጥ የተደረገውን የአመራር ለውጥ ለመገንዘብ፤ በኦህዴድ አመራሮች እና በክልሉ ህዝብ፣ እንዲሁም በኦህዴድ እና በተቀሩት የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች አመራሮች መካከል የነበረውን ግንኙት በዝርዝር ማየት ያስፈልጋል፡፡

በተለይ ህዝባዊ አመፅና ተቃውሞ ከፍተኛ ደረጃ በደረሰበት ወቅት በቄሮዎች እና በኦህዴድ አመራሮች መካከል የነበረው ግንኙነት በጠላትነት ስሜት የሚመራ ነበር፡፡ በ2008 ዓ.ም አጋማሽ በተለይ በቀበሌ፥ ወረዳና ዞን ደረጃ ላይ የሚገኙ የኦህዴድ ባለስልጣናትና የፀጥታ ሰራተኞች ህይወትና ንብረት ጠፍቷል፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ባቀረበው ሪፖርት መሠረት በስድስት ወር ውስጥ ብቻ 14 የፀጥታ ሰራተኞች እና 14 የመንግስት ባለስልጣናት ተገድለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በተለይ በወረዳና ዞን ደረጃ የሚገኙ የኦህዴድ ባለስልጣናት ቤትና ንብረት ወድሟል፡፡ ቄሮዎች በወሰዱት ቀጥተኛ የሃይል እርምጃ የክልሉ ባለስልጣናትና የፀጥታ ሰራተኞች የህዝቡን ጥያቄ እንዲቀበሉና ከቄሮዎች ጎን እንዲቆሙ አስገድዷቸዋል፡፡

በ2008 ዓ.ም መጨረሻ በዞንና ወረዳ ደረጃ የሚገኙ ኦህዴዶች ከክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ስብሰባ የቄሮዎችን ጥያቄ በመቀበል ከህዝቡ ጎን ከመቆም በስተቀር ሌላ ምርጫ እንደሌላቸው በግልፅ ተናግረዋል፡፡ የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ይህን ማድረግ ከተሳናቸው የድርጅቱ ህልውና ያከትማል፣ የባለስልጣናቱ ህይወትና ንብረት ይወድማል፡፡ ስለዚህ ኦህዴዶች በወቅቱ የነበራቸው አማራጭ የመኖር ወይም የመጥፋት ነበር፡፡ በአንድ በኩል ኦህዴድ ከክልሉ ህዝብ ጎን ከቆመ ድርጅቱ ህልውናውን ያረጋግጣል፣ የህወሓት የበላይነት ያከትማል፡፡ ነገር ግን፣ ኦህዴድ እንደቀድሞው ተገዢ ሆኖ የሚቀጥል ከሆነ የህወሓት የበላይነት ይቀጥላል፣ የኦህዴድ ህልውና ግን ያከትማል፡፡

በዚህ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ አዲሱ የኦህዴድ አመራር ወደ ስልጣን የመጣው፡፡ የኦቦ ለማ አመራር ወደ ስልጣን እንደመጣ ቀዳሚ ተግባሩ ከክልሉ ህዝብ ጎን በመቆም እንደ ፖለቲካ ድርጅት ህልውናውን ማረጋገጥ ነው፡፡ ነገር ግን፣ ኦህዴድ ህልውናውን ለማረጋገጥ የሚወስደው እርምጃ የህወሓትን የበላይነት የሚፃረር ነው፡፡ ምክንያቱም ህወሓት ከአመሠራረቱ ጀምሮ ዓላማው የራሱን የበላይነትና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው፡፡ ስለዚህ ኦህዴድ የኦሮሞን ህዝብ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚወስደው ማንኛውም ዓይነት የለውጥ እርምጃ በህወሓት ላይ ቀጥተኛ የህልውና አደጋ ይጋርጣል፡፡

ጠ/ሚ አብይ አህመድ

በአጠቃላይ በኦህዴድ እና ህወሓት መካከል ያለው ግንኙነት የመኖር ወይም የመጥፋት ነው፡፡ ኦህዴድ ካሸነፈ የህወሓት የበላይነት ያከትማል፣ ህወሓት ካሸነፈ ደግሞ የኦህዴድ ህልውና ያከትማል፡፡ ስለዚህ አዲሱ የኦህዴድ አመራር እና ህወሓት ያላቸው አማራጭ ከመጥፋታቸው በፊት አጥፊያቸውን ቀድሞ ማጥፋት ነው፡፡ በዚህ ረገድ ህወሓት በህዝቦች መካከል ያለመተማመን መንፈስና ግጭት በመፍጠር ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ዜጎች ገድሏል፣ አፈናቅሏል፡፡ በዚህ መሠረት ዜጎችን ሰላምና ደህንነት በማሳጣት ህወሓት ተቀባይነት ለማግኘት፣ ኦህዴድን ደግሞ ለማሳጣት ከፍተኛ ጥረት አድርጏል፡፡ ኦህዴድ ደግሞ በብሔሮች መካከል ያለውን ግንኙነትና የትብብር መንፈስ በማጠናከር በሀገር-አቀፍ ደረጃ ያለው ተቀባይነት ለማሳደግ፣ ህወሓትን ደግሞ ተቀባይነት ለማሳጣት ከፍተኛ ትግል አድርጏል፡፡

ህወሓት በዚህ አመት የመጀመሪያ ወራት ባደረገው 35 ቀናት የፈጀ ስብሰባ ዋና የመወያያ አጀንዳ የነበረው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ዳግም በማወጅ፣ “ህዝበኞች – Populist” ያሏቸውን የኦህዴድና ብአዴን መሪዎች ማሰርና የለውጡን ንቅናቄ መቀልበስ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት፣ በመጀመሪያ በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል ላይ ብቻ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ለማወጅ ሞከሩ፡፡ ይህ ሙከራ ከኦህዴድና ብአዴን ባጋጠመው ጠንካራ ተቃውሞ ውድቅ ተደረገ፡፡ በመቀጠል “ብሔራዊ የደህንነት ምክር” በማቋቋም በእጅ አዙር የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ለማወጅ ሞከሩ፡፡ በተለይ ከኦሮሚያና አማራ ክልል መስተዳደሮች ተቀባይነት በማጣቱ ምክንያት ተግባራዊ ሳይሆን ቀረ፡፡

በመጨረሻም በ17ቱ ቀን የኢህአዴግ ስብሰባ ህወሓት ስልታዊ ማፈግፈግ አደረገ፡፡ በዚህ መሠረት፣ ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ፣ በአንፃሩ ‘ሁከትና ብጥብጥ ከተነሳ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ለማወጅ ከስምምነት ላይ ደረሰ፡፡ በድርድሩ ወቅት የህወሓት መሠረታዊ ዓላማ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ በማወጅ ፀረ-ህወሓት አቋም የሚያራምዱና በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸውን የኦህዴድና ብአዴን አመራሮች በማሰር የለውጡን እንቅስቃሴ መቀልበስ ነው፡፡ ሆኖም ግን ከህወሓት ፍላጎትና ምርጪ ውጪ ከደኢዴን እና ብአዴን ጋር በፈጠረው ጥምረት ኦህዴድ የጠ/ሚኒስትርነት ቦታውን ያዘ፡፡

የዶ/ር አብይ መመረጥ የኦህዴድና ብአዴን አመራሮችን በማሰር የለውጡን እንቅስቃሴ መቀልበስ ለሚሻው ህወሓት የህልውና አደጋ ነው፡፡ የአዲሱ አመራር የመወሰን አቅምና ነፃነት የሚረጋገጠው ደግሞ የህወሓትን የበላይነት በማስወገድ ነው፡፡ በመሆኑም የዶ/ር አብይ ውጤታማነት የሚወሰነው የህወሓት ልሂቃን በፖለቲካና ኢኮኖሚው ውስጥ የነበራቸውን አድራጊ-ፈጣሪነት እንዲያከትም በማድረግ ነው፡፡ ስለዚህ የዶ/ር አብይ አፈፃፀም ብቃት የሚለካው የህወሓትን የበላይነት በማስወገድ ሲሆን የህወሓት ህልውና ደግሞ በፖለቲካና ኢኮኖሚው ረገድ የነበረውን የበላይነት በማስቀጠል ነው፡፡

ህወሓቶች በተለያዩ ብሔሮች መካከል ግጭት በመፍጠር የለውጡን ንቅናቄ ለማኮላሸት ጥረት አድርገዋል፡፡ ይህን የማድረጉ ዋና ዓላማ በሀገሪቱ ላይ የፍርሃትና ስጋት ድባብ በመፍጠር በተለይ አዲሱን የኦህዴድ አመራር ተቀባይነት ማሳጣት ነበር፡፡ ይህን ማድረግ ሲሳናቸው ደግሞ በተለይ በቀድሞ ጠ/ሚ ሃይለማሪያም ደሳለኝ አማካኝነት፣ እንዲሁም በመከላከያ፥ ደህንነቱ እና የፍትህ ተቋማት ላይ ያላቸውን የበላይነት ተጠቅመው አዲሱን የኦህዴድ አመራሮችን በማሰር የፖለቲካ ስልጣናቸውን እና በህዝቡ ዘንድ የነበራቸውን ተቀባይነት ለማሳጣት ጥረት አድርገዋል፡፡

የዶ/ር አብይን መመረጥ ተከትሎ ህወሓቶች በሥራ አስፈፃሚው ላይ የነበራቸውን ስልጣን አጥተዋል፡፡ ነገር ግን በተለይ በመከላከያና ደህንነት መዋቅሩ ላይ የነበራቸውን ስልጣን ሙሉ በሙሉ አጥተዋል ማለት አይቻልም፡፡ ስለዚህ በእነዚህ ተቋማት አማካኝነት ያላቸውን የበላይነት ተጠቅመው በዜጎች ላይ የፍርሃትና ስጋት ሊፈጥሩ ይችላሉ፡፡ በዚህ መልኩ አዲሱ አመራር በህዝብ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት ለማሳጣት ከመንቀሳቀስ ወደኋላ አይሉም፡፡ በሌላ በኩል፣ ዶ/ር አብይ ያለውን የፖለቲካ ስልጣን በመጠቀም በህዝብ ላይ ፍርሃትና ሽብር ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱትን የህወሓት አመራሮችና ልሂቃን ማሰር ይችላል፡፡

በዚህ መሠረት ህዝቡን ከህወሓቶች እኩይ ተግባር በመከላከል ተቀባይነቱን ማሳደግ ይችላል፡፡ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማስከበር ከተሳነው ግን ተቀባይነቱንና የመወሰን ስልጣኑን ያጣል፡፡ ህወሓቶች የኦህዴድና ብአዴን አመራሮችን ማስር የተሳናቸው፤ አንደኛ፦ አመራሮቹ በህዝብ ዘንድ አንፃራዊ ተቀባይነት ስለነበራቸው፣ ሁለተኛ፦ አመራሮቹን ለማሰር የሚያስችል ተጨባጭ ማስረጃ ስላልነበራቸው ነው፡፡ ቀንደኛ በሆኑ የህወሓት አመራሮች ላይ ማስረጃ ማግኘት ግን በጣም ቀላል ነው፡፡ በመሆኑም አፍራሽ በሆኑ ተግባራት የተሰማሩና ሊሰማሩ የሚችሉት የህወሓት አመራሮች በማሰር ለፍርድ ማቅረብ ይችላል፡፡ ይህን በማድረግ የህወሓትን የበላይነት ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ማስወገድ ይችላል፡፡

ምንጭ፤ Ethiopian Think Thank Group by Seyoum Teshome

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: abiy, andm, ethnic politics, Full Width Top, Middle Column, opdo, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    May 19, 2018 06:12 pm at 6:12 pm

    ጭከና ምን ያደርጋል? ቂሊንጦና ቃሊቲ እንደ ስብሃት ሽምግሌ ለሆነ ሰው አይመችም!ባይሆን ወደ ዐድዋ ወይም ወደ አረብ ምድር ቢሄድ ይሻላል።

    Reply
  2. Gezahegn Woldemariam says

    May 24, 2018 06:11 pm at 6:11 pm

    ሕወአት ኢትዮጵያን ለ27 አመት ሲገዛ ልማት አምጥቻለሁ ቢልም፤ በአንፃራዊነት የመጣ ልማት ያለ ቢሆንም፤ በልዩነት ላይ ቢሰራም፤ አንድነትን ግን ማምጣት ተስኖታል(አይፈልግምም)።
    ለዚህም ምክንያቶቹ ብዙ ናቸው፤ ብዙ ጊዜ ለኢት ሕዝብ በስብሰናል፣ ኪራይ ሰብሳቢ ሆነናል፤ ጥገኛ ዝቅጠት፣ ጥበት፣ ትምክሕተኝነት፣ አካበቢነት ወዘተ እያለ፤ ተሐድሶ፣ የእውነት መታደስ፣ ጥልቅተሐድሶ በማለት ሕዝብን ማሞኘቱ ሳያንሰው፤ አሁን እነደ ከዘህ በፊቱ የውሸት አይደለም ከምር ታድሰናል ። ብለው ጠሚ የነበሩት ሐ/ማርያም ደሳለኝ የእረኛውን ና የቀበሮ ተረት በአሰፋ እናት ህመም ቀይረው የተናገሩት ያስታውሷል። ከዚህ በላይ በሕዝብ መቀለድ ያለ አይመስለኝም። ሕዝቡም ከዳር እስከ ዳር ውሸት ሰለቸን ብሎ ፤ ብንቸገርም በኢትዮጵያዊነት አንድ ሆነን፣ ትህ አግኝተን፣ በአስተሳሰባችን ም/ት መታሰር ና መገደል እንዲሁም በኢኮኖሚ መሳሪያዎች መመታት ሰለቸን ስላለ ህወሀቶች የሕዝብን ድምፅ ና ሀሳብ አክብራችሁ ለቆማችሁለት ለትግራይ ሕዝብም ብታስቡ ና የሚመጣውን በፀጋ ብትቀበሉ እንጂ ከዚህ በኋላ እንደከዚህ ቀደሙ ሕዝብን በማበጣበጥ(በዘር ና በጎሳ) የመረጣችሁትን ጠሚ ለማሳጣት የኢኮኖሚ ሞተሩን ይዘናል ብላችሁ ወከባ መፍጠር ተገቢ የልሆነ ና ለማንም የማይጠቅም መሆኑን አምናችሁ ከጎኑ በመሆን ብታግዙ የተሻለ ነው። ሕዝብ ከጠላ፣ ከተፋ ና ከነቃ በኋላ ማንን ለመምራት ነው?እራስን መርምሮ፣ አድሶ፣ የተለየ(የተሻለ) ሐሳብ በማምጣት ና ከዘህ በፊት ለጠፋው ይቅርታ በመጠየቅ፣ ወደውጪ የተከማቸውን የኢትዮጵያ ገንዘብ ና አንጡራ ሐብት በመመለስ ከህዝብ መታረቅ ይቻላል።
    …ቆሜለታለሁ ለምትሉት ሕዝብ ለልጆቿችሁም ጭምር አስቡ።
    …የሌባ ዘር (ልጅ) እየተባሉ በታሪካቸው እንዳይኮሩ አታርጓቸው፤ ልክ እንደ ጋዳፊ ና ናዚ ሒትለር

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule