በቅርቡ አሜሪካ የሚኖሩት ወገኖቻችን በተባበረ ጥረታቸው ለብዙ ጊዜ ሲዋጉለት የነበረውንና የኢትዮጵያን መንግሥት ቢያንስ ቢያንስ ወደ ተከላካይነት ሊያወርደው ይችላል ተብሎ የታመነበት የአሜሪካ ኮንግረስ ውሳኔ በአደባባይ ለመላው ዓለም ሲታወጅ የተሰማን ደስታ ወሰን አልነበረውም። እኛ የአንጋፋው ትውልድ፣ ከሩቅ ሆነን ሲመቸን ብቻ “በርቱ” እያልን “ድጋፍ” ስንሰጣቸው የነበርነውን ይህን ያህል ያስደስተን፣ በቦታው ሆነው ሌት ተቀን ሳይታክቱ ከስቴት ወደ ስቴት እየተደዋወሉ በተወካዮቻቸው የኮንግረስ አባላት ዘንድ በመደወልና በመጻፍ ተጽዕኖ እያሳደሩ በመጨረሻ ላይ የለፉለት ግቡን ሲመታ ምንኛ እንደተደሰቱ ገምቼ እኔም በጣም ተደሰትኩላቸው። ብዙዎቹ እንደነገሩኝ ከሆነ፣ ያን ቀን በጥዋት ተነስተው ወደ ካፒቶል በማምራት፣ አሰልቺውን የጸጥታ ምርመራ በትዕግሥት አልፈው ወደ ኮንግሬስ ተወካዮቻቸው ቢሮ … [Read more...] about ኤች አር 128 ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የኛ ሚና
Opinions
የኔ ሃሳብ
የአማራ ብሔረተኝነት ለስር ነቀል ለውጥ መሰረት፣ ለኢትዮጵያም መዳኛ መድሃኒት ነው
የአማራን ህዝብ በቃላት መሸንገል የማይቻልበት ደረጃ ተደርሷል። የህዝቡ ንቃተ ህሊናው በስልጣን ላይ ከሚገኙት ከፓለቲከኞቹ ቀድሞ ሄዷል። ወጣቱ የነብር ጣቱ - እሳት ትውልድ ሆኗል። ገና ከመነሻው ወያኔ/ትህነግ በ1967 ዓ.ም ባፀደቀው በማኒፌስቶው ላይ አማራ ጠላቴ ነው በማለት የአማራ ህዝብ መቃብር ላይ የትግራይን ሪፕብሊክ እመሰርታለሁ፣ የአማራን ህዝብ ማህበራዊ ሰላም አሳጠዋለሁ ብሎ ሸፈተ። በርሃ ሳለ በአማራው ተወላጅ ላይ ከፍተኛ በደልና ወንጀል ሲፈጽም ከቅምየ በኋላ በተለት የአለም አቀፍና የሃገር ውስጥ ሁኔታዎች በደርግ መንግስት ላይ በፈጠሩት ጫና በለስ ቀንቶት የመንግስት ስልጣን ከተቆጣጠረበት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በጥናትና በእቅድ በተጠናከረ ሁኔታ በአማራ ህዝብ ላይ የሙፈጽመውን በደልና ቀጠለበት። ጫካ እያለ ያፀደቀውን ፀረ አማራ ፕሮግራሙን ለማታለያነት ከካናዳና ከሌሎች … [Read more...] about የአማራ ብሔረተኝነት ለስር ነቀል ለውጥ መሰረት፣ ለኢትዮጵያም መዳኛ መድሃኒት ነው
የዶ/ር ዓቢይን “መጨረሻ ለማየት ቢያንስ ስድስት ወራት እንጠብቅ”
ዶር. ዓቢይና አቶ ለማ መገርሳ በኢትዮጵያ መድረክ ላይ መታየት ሲጀምሩ ኢትዮጵያ የተአምር አገር መሆንዋን አስታወስሁና እግዚአብሔር ፊቱን ወደኢትዮጵያ መመለሱን ተረዳሁ፤ ከዚያም በላይ ያለፈው ጠቅላይ ሚኒስትር እናቱን በመውቀስና በመመጻደቅ ጀመረ፤ አዲሱ ደግሞ እናቱን በማወደስ መጀመሩ ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ላይ ያለውን እምነት በአደባባይ ደጋግሞ በመግለጹ አከበርሁት፤ አከብረዋለሁ። ከዚህ በፊት ሦስት ጊዜ በፌስቡክ የጻፍሁትን ልድገመው፤ አንድ፤ በ1965 በወሎ ችጋር ዘመን በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች እርዳታ ለማድረግ በምንሯሯጥበት ጊዜ አንዳንድ የኢሕአፓ አባሎች ለተራቡት እርዳታ መሰብሰብ አብዮቱ እንዳይመጣ ማድረግ ነው እያሉ ይቃወሙን ነበር፤ ነፍሱን ይማረውና አብርሃም ደሞዝና እኔ ተቆጥተንና አስፈራርተን አደብ እንዲገዙ አድርገናቸው ነበር፤ ዛሬ ደግሞ … [Read more...] about የዶ/ር ዓቢይን “መጨረሻ ለማየት ቢያንስ ስድስት ወራት እንጠብቅ”
የዶ/ር አብይ አህመድ አዋላጅነት ጉዳይ
ቃሉ የሕዝብ ነው። ቃሉንም በተግባር የሚተረጉመው ሕዝብ ነው። የወንዝ ውሃ ሽቅብ እንደማይፈስ ሁሉ፥ ይህም ቃል ወደ ተግባር ሳይቀየር ይቀለበሳል ብሎ መጠበቅ ተገቢ አይደለም። ይልቁንስ ይህን ቃል ለመተግበር የዶ/ር አብይ ድርሻ ምንድነው ብሎ አውቆ በዚያው ሚዛን ብቻ እርሳቸውን መመዘን ያስፈልገናል። ለሕዝብ ታማኝ ባይሆኑ፥ እሳቸው ከታሪካዊነት ይጎድላሉ እንጂ የሕዝብ ቃል ዕውን መሆኑ አይቀሬ ነው። ዶ/ር አብይ አህመድ የሚናገሩት ቃል እርሳቸው የፈለሰፉት ስለሆነ አይደለም የተወደደው። ቃሉ የሕዝብ ቃል ስለሆነ ነው እንጂ። ይህ ሰሚ ያጣ ሕዝብ በትግሉ የራሱን ቃል የሚያስተጋባ ጠ/ሚ ሊያመጣ ቻለ። ታዲያ ይህን ቃል የዶ/ር አብይ የግል ንብረት ተደርጎ፥ ቃል ዋጋ የለውም ብሎ ቃሉን ማጣጣል ለኢትዮጵያ አይጠቅምም። የውልጃ አብሳሪ የሆነ ቃል በውልደት ቀን ዋዜማ ሲሰማ፥ በተስፋና በትጋት ይህን … [Read more...] about የዶ/ር አብይ አህመድ አዋላጅነት ጉዳይ
PM Abiy and a call to build the capacity of stakeholders
In my latest commentary, I shared the second leadership attribute of Dr. Abiy, one of the New Breed Leaders of Africa. I pointed out that since he had done his homework and developed his personal growth very well that he outgrew his past leadership positions and outlived the challenges he had been facing. This is my hope that this same quality is one of the virtues that could empower him to lead the country’s transformation successfully. However, before I cover his third leadership attribute on … [Read more...] about PM Abiy and a call to build the capacity of stakeholders
የጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ
እንደ መግቢያ ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ስለዶ/ር አብይ ያለኝ የጠለቀ እውቀት ወይም ከነበሩበትና ከተነሱበት ፓርቲና ፓርቲው ከሚያራምደው የፖለቲካ አመለካከት ጋር ያለኝ ጠብ ወይም ዝምድና አይደለም። ይልቁንም እንደ አንድሀገር-ወዳድ ኢትዮጵያዊ ባለው የህወሃት የበላይነትን የተከተለ ፍጹም ዘረኛ ጉዞ ሄደን ሄደን የደረስንበት ደረጃ በጣም አሳሳቢ መሆኑን በመመልከት ነው። በዘረኛው የወያኔ ከሩብ ምእተ አመት የዘለለ የጥፋት ጉዞ ውስጥ ከተጓዙና ከጉያቸው የበቀሉ ዘረኛው ስርአት ከሚያራምደው የተለየና የተሻለ ራእይ ያለው ጉዞን የመረጠ የኦሮሞ፣ የአማራ እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ ወጣቶች በደምና በህይወት ጭምር ዋጋ የከፈሉበትን ትግል ባዳመጠ መልኩ የተቃኘ ‘ቲም ለማ’ ከተባለ የለውጥ አራማጆች ውስጥ የበቀሉት የዶ/ር አብይ ራእይ ምን ቢሆን ለሐገር የሚበጅ መድህን ይሆናል የሚለውን … [Read more...] about የጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ
HR 128 መጽደቅ ለመሰረታዊ የመብት ትግላችን ታላቅ ድጋፍ ነው
ሸንጎ ህጉን ይደግፋል፤ ለተፈጻሚነቱም ተግቶ ይፋለማል HR 128 ተብሎ የሚታወቀው ባሜሪካ ኮንግረስ (ፓርላማ) ውስጥ ለውሳኔ ቀርቦ የነበረው በኢትዮጵያ መንግስት የመብት አያያዝ ላይ ያተኮረ የህግረቂቅ እነሆ ትናንት መጽደቁ ተነገረ። በውጭ አገር ያሉ የሰብዓዊ መበት ተከራካሪዎችና የተደራጁ ኢትዮጵያውያን ይህ የህግ ረቂቅ እንዲጸድቅና በስራ ላይ እንዲውል ለረጅም ጊዜ ከፍተኛ ተጋድሎ ሲያድርጉ ቆይተዋል። ሸንጎ ለዚህ ስኬት ታጥቀው ለታገሉ ሃይሎች በሙሉ ያለውን አድናቆትና ክብር እያስታወቀ፤ የረቂቁ ህግ ሆኖ መጽደቅ ለኢትዮጵያ ህዝበና ለመላው የዴሞክራሲ ሃይሎች ታላቅ ድል መሆኑን ይገልጻል። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ … [Read more...] about HR 128 መጽደቅ ለመሰረታዊ የመብት ትግላችን ታላቅ ድጋፍ ነው
አምቦ ትናንትና ዛሬ!
አምቦ ስሟ ሲጠራ የብዙዎቻችን ልብ በሃሴት እንደሚሞላ ሁሉ ወያኔዎችና አሽቃባጮቻቸው አጥንታቸው ድረስ የሚዘልቅ ብርድ እንደሚሰማቸው ግልፅ ነው። ያች ምድር የብዙ ጀግኖች መፈጠርያ ናት። ጣልያንን ብርክ ያስያዙ ጀግኖቿን ታሪክ ሲያስታውሳቸው ቢኖርም ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው የአባቶቻቸውን ጋሻ አንስተው የሃገር ጠላት የሆነን ስርዓት በመፋለም ለሌላውም አንቂና አበረታች ሆነው እነሆ እነሱም ታሪክ ሠሩ። አምቦዎች ወያኔን መፋለም የጀመሩት ገና ከመጀመርያው ነው። ከሁሉም በላይ ባለፈው ሶስት ዓመት የአምቦና የአካባቢ ጀግኖች፣ ቄሮዎች የለኮሱት አመፅ መላ አገሪቷን ከዳር ዳር አዳርሶ እነሆ ዲያስፖራንም አነቃንቆ HR 128 በማስወሰን በወያኔ አንገት ገመድ አጥልቆለታል። አምቦና ወያኔ ዐይንና ናጫ ናቸው። ወያኔ በጎንደር፣ በጎጃምና በወለጋ አቆራርጦ ሲገሰግስ ሊሞት አንድ ሃሙስ የቀረው ደርግ … [Read more...] about አምቦ ትናንትና ዛሬ!
ያልታሰበው H. Res. 128 ውሳኔ እና የህወሃት መብረክረክ
ያልታሰበ ነው። ፈጽሞ ያልተገመተ። አገዛዙን እንደ ቀትር መብረቅ ያስደነገጠ ውሳኔ። በጸረ-ሽብር ስም በሚተውኑት የፖለቲካ ድራማ ሳብያ አሜሪካ ይህን አይነት ውሳኔ አጋር በሆነ አካል ላይ ትፈጽማለች ብለው ለአፍታ እንኳን አስበውት አያውቁም። በዚያ ላይ ደግሞ በሚሊዮን ዶላር የሚከፈላቸው ሎቢስቶች ጉዳዩን ይዘውልናል ብለው ተዘናግተዋል። “ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አሕመድ ዕድል እንስጥ” የሚለው የኦክሎሃማው ሴናተር ጄምስ ኢንሆፍ ሃሳብ ያሸንፋል የሚል ግምትም ነበራቸው። ንቀታቸው እና ትዕቢታቸው የት እንደደረሰ የተመለከትነው፤ ሰነዱ ምክር ቤት ሊቀርብ ቀናት ሲቀረው እንኳ ዜጎችን ከእኩይ ተግባራቸው ያልመቆጠባቸው ነው። በሽብር የወነጀሏቸውን የዋልድባ መነኮሳት አሁንም እያሰቃዩዋቸው ይገኛሉ። ሰነዱ ሊጸድቅ አንዲት ቀን ሲቀረው በምስራቅ ሀረርጌ፤ ቆቦ ከተማ ነፍሰጡርዋን በጥይት … [Read more...] about ያልታሰበው H. Res. 128 ውሳኔ እና የህወሃት መብረክረክ
ልጄ ሆይ፤ ሰው ሁን!
እነሆ ሰንበት ነበረ። ምዕመኑ በሚኖርበት ከተማ በምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅድሰት ቤተ ክርስቲያን እንዳለፉት አያሌ ሰንበቶች ሁሉ ባለፈው ሰንበትም ተገኝቷል። ቃሉን ሊሰማ፤ ስለ ቃሉም ለመኖር ብርታትን ሊያገኝ፤ ስለራሱና ስለቤተሰቦቹ፤ ስለ ህዝቦቹና ስለ ሀገሩም ሊፀልይ፤ እጆቹንም ወደ ሰማይ አንስቶ ሊለምን። ማረን ለማለት። እግዚኦታም ለማቅረብ። ከትጉሁና ትሁቱ ካህንም ቃለ ህይወት ሊሰማ። ቃለ ህይወትንም ሊማር። እነሆም ካህኑ ቅዳሴውንና ፀሎቱን ይመራሉ። ድምፃቸውም በመንፈሳዊ ቅላፄ በመቅደሱ ይሞላል። ዲያቆናቱም ይቀበላሉ። ምዕመናኑም ይደግማሉ። ወይ ተንበርክከውና አንገታቸውን ከመሬት ደፍተው፤ ወይ ቀጥ ብለው በመቆም እጆቻቸውን ወደ ፈጣሪ ዘርግተው። የካህኑ ድምፅ በፀሎትና በቅዳሴ ዜማ እንዲህ ይላል - አምላካችን ክርስቶስ ሆይ፤ የተጨነቀችይቱን ነፍስ ሁሉ አሳርፍ፤ … [Read more...] about ልጄ ሆይ፤ ሰው ሁን!










