• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ያልታሰበው H. Res. 128 ውሳኔ እና የህወሃት መብረክረክ

April 11, 2018 06:21 am by Editor 1 Comment

ያልታሰበ ነው። ፈጽሞ ያልተገመተ። አገዛዙን እንደ ቀትር መብረቅ ያስደነገጠ ውሳኔ። በጸረ-ሽብር ስም በሚተውኑት የፖለቲካ ድራማ ሳብያ አሜሪካ ይህን አይነት ውሳኔ አጋር በሆነ አካል ላይ ትፈጽማለች ብለው ለአፍታ እንኳን አስበውት አያውቁም። በዚያ ላይ ደግሞ በሚሊዮን ዶላር የሚከፈላቸው ሎቢስቶች ጉዳዩን ይዘውልናል ብለው ተዘናግተዋል። “ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አሕመድ ዕድል እንስጥ” የሚለው የኦክሎሃማው ሴናተር ጄምስ ኢንሆፍ ሃሳብ ያሸንፋል የሚል ግምትም ነበራቸው። ንቀታቸው እና ትዕቢታቸው የት እንደደረሰ የተመለከትነው፤ ሰነዱ ምክር ቤት ሊቀርብ ቀናት ሲቀረው እንኳ ዜጎችን ከእኩይ ተግባራቸው ያልመቆጠባቸው ነው። በሽብር የወነጀሏቸውን የዋልድባ መነኮሳት አሁንም እያሰቃዩዋቸው ይገኛሉ። ሰነዱ ሊጸድቅ አንዲት ቀን ሲቀረው በምስራቅ ሀረርጌ፤ ቆቦ ከተማ ነፍሰጡርዋን በጥይት ደበደቧት። በመጀመርያ አስገድደው ደፈሯት። ከዚያ ገደሏት።

ለሰብዓዊ ክብር የቆመ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደርን የሚደግፍ ሰነድ፤ ውሳኔ H.Res 128። በዩናይትድ ስቴይትስ ምክር ቤት ፊት ቀርቦ ያለ አንዳች ተቃውሞ ጸድቋል። ይህ አስደንጋጭ ውሳኔ የሁለቱን ሃገራት ግንኙነትን ወደ ሌላ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ይመስላል።

ይህ ሰነድ አያሌ መሰናክሎችን አልፎ ለውሳኔ በቀረበበት ቅጽበት አምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን፤ ለአሜሪካ ኮንግረስ አንድ የተማጽኖ ደብዳቤ ልከው ነበር። እኚህ ሰው ከተለመደው የጸረ-ሽብር ማስፈራረያ ወጣ ብለው፤ መንግስታቸው ለለውጥ እያሳየ ያለውን ቁርጠኝነት ተናግረዋል። በነገሩ ላይ በግልጽ ለመምከር፤ ለጋራ ውይይትም ጋብዘዋል። “ውሳኔ ከማስተላለፍ ተቆጠቡ” ብለው የሕግ መምሪያ ምክር ቤቱን ቢጠይቁም፤ ጅብ ካለፈ… ሆነና አልተሳካም።

“በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ይቁም፤ ለሁሉም እኩል የሆነች ኢትዮጵያ እውን ትሁን!” የሚል ሰነድ ማውጣት፤ ከፋቱ ምኑ ላይ እንደሆነ የሚረዱት የአገዛዙ ተጠቃሚዎች ብቻ ናቸው። ይሁን እንጂ “አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወርራታል” የሚለው የዘወትር የህወሃት ነጠላ ዜማ አሁን ስለተበላ ጨዋታቸውን የቀየሩ ይመስላል።

የእነ ስብሃት ነጋ “አይጋ ፎረም”፤ እንደ ደብተራ ክታብ በቀይ እና በጥቁር ቀለም አሸብርቆ አሜሪካን መሳደብ ጀምሯል። ውሳኔው አስገዳጅ ያልሆነ እና ተፈጻሚነትም እንደማይኖረው አይጋ ነግሮናል። በዚህ አላበቃም። በሃገር ጉዳይ ጣልቃ አትግቡ ሲልም የአሜሪካ ኤምባሲን ያስጠነቅቃል። የአሜሪካው አምባሳደር በኢትዮጵያ የጀመሩትን “የብተና ተልዕኮ” አስመልክቶ ጠ/ሚንስትር አብይ አህመድ ጠንካራ መልዕክት እንዲያስተላልፉም ያሳስባል።

የነ አባይ ጸሃይ “ትግራይ ኦንላይን” ድረ-ገጽም፤ የተለመደው የኒዮ ሊብራል ትርክት ይዞ ታላቋ አሜሪካን ለመሳደብ አፉን ከፍቷል። የሰብአዊ መብቱን ጉዳይ ሳይሆን የቻይና ጣልቃ ገብነት አሜሪካን እንዳላስደሰተ ሊነግረን ሞክሯል።

የወያኔ ብሎገሮችም ዝም አላሉም። የአንዳንዶቹ ሃሳብ እንደ ፔንዱለም መዋዠቁ ግን የተስፋ መቁረጡ እና የፍርሃቱን መጠን ይገልጸዋል። አንዱ ብሎገር “ውሳኔውን የሀዘን መግለጫ ነገር ነው። ለዛ ነው ድምጽ ራሱ ያልተሰጠበት።” ሲል ጽፏል።

“የሃዘን መግለጫ” ያሉት ይህ ውሳኔ እንዳያልፍ ከ80 ሚልዮን ብር በላይ ለምን እንዳወጡበት ግን ሊነግረን አይደፍርም። ውሳኔው “ምንም አያመጣም” ካሉን ታዲያ አሁን ሲጸድቅ ለምን ብርክ ያዛቸው?

ይህ ሰነድ ውሳኔ ሊሰጥበት የነበረው ባለፈው አመት ኦክቶበር 2/2017 ነበር። በወቅቱ በገጠመው የታሰበ እክል እንዲራዘም ተደረገ። የተራዘመበት ምክንያትም ግልጽ ነው። “ይህ ሕግ ካለፈ ከአሜሪካ ጋራ የሚኖረን ጸረ-ሽብርተኝነትን ድጋፍ እናቆማለን” በማለት የወያኔ መንግስት በይፋ ተናግሮ ነበር። ምክንያቱን ልብ በሉ! በንግድ ልውውጥ አይደለም። በባህልና ቱሪዝም ጉዳዮችም አይደለም። በጸረ-ሽብር ላይ አብሬ አልሰራም ነው ያሉት። የአሜሪካን ጦርነት የኢትዮጵያ ልጆች እንዲወጡት፤ ሁለቱ አካላት በፊት ለፊት ሳይሆን በጓሮ በር የተፈራረሙትን ሰነድ እንቀድደዋለን ሲሉ ነበር ያስፈራሩት። አንድ የአሜሪካ ዜጋ በሶማሊያ ምድር ላይ ከሚሞት ብለው፤ አንድ ሺህ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ስንገብር ነበር።

ሰነዱ እንዲሞት አገዛዙ ከፍተኛ የማባበል (ሎቢ) እና የማስፈራራት ስራ አየሰራ እንደነበር የተከበሩ እንደራሴ ማይክ ኮፍማን ተናግረዋል። ሾልኮ የወጣው መረጃ እንደሚጠቁመን አገዛዙ ይህን ለሚሰሩ ሎቢስቶች በወር 150ሺህ ዶላር ይከፍላል። ይህ ረቂቅ እዚህ ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ሃገሪቱ ካላት ውስን የውጭ ምንዛሪ 1.8 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሏል። እየገደሉ መኖርን መብታቸው ካላደረጉት በስተቀር ይህንን ያህል ገንዘብ ለባዕድ ደላሎች ከማዋል ይልቅ በገንዘቡ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እና ክሊኒኮችን ይገነቡበት ነበር።

“በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ክብር የቆመ ሁሉን አቀፍ አስተዳደር እንዲኖር”፤ በማለት የሚጀምረው ይህ ሰነድ በኢትዮጵያ እየታዩ ያሉትን የመብት ጥሰቶችና በደሎች ያወግዛል። የአገዛዙ አካል ከልክ ያለፈ ሃይል መጠቀም እንዲያቆም። በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተካሄደው ግድያ እና ስቃይ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ገዳዮቹ/አስገዳዮቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚሉ ጫና ሊፈጥሩ የሚችሉ ጠንካራ ድንጋጌዎችን ይዟል። ድንጋጌዎቹ ተፈጻሚ ካልሆኑ የሚወሰዱ እርምጃዎችም በአፈጻጸሙ ላይ ተገልጸዋል።

አሜሪካ እና አውሮፓውያን ላለፉት ሶስት አስርተ-ዓመታት ለራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም ሲሉ፤ የኢትዮጵያ ችግር ችላ ብለው እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። የኢትዮጵያ ችግር አሁን ካለበት ጫፍ ደርሶ፤ ስርዓቱ ህዝባዊ እንቢተኝነት መንገዳገድ ሲጀምር የአሜሪካ የፖሊሲ ማሻሻል ለማድረግ መሞከርዋ፤ እንደተለመደው ሃይል ሚዛኑን ተከትሎ ቢሆንም አሁንም አልረፈደም። ህወሃት ሕዝባዊ መሰረት የሌለው፤ በመሳርያ ሃይል ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተቀመጠ ደካማ ድርጅት ነው። የአሜሪካ የገንዘብ እና ወታደራዊ ድጋፍ ባይኖረው ኖሮ እስካሁን በስልጣን ላይ ሊቆይ እንደማይችል ሁሉም ይገነዘባል።

በአሜሪካ ሳንባ የሚተነፍሱት የአውሮፓ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም ከዚህ በኋላ ዝምታቸውን ይሰብራሉ። የዚህን ሰነድ መጽደቅ ተከትለው ለጋሽ ሃገሮች ተመሳሳይ እርምጃ በወያኔ ላይ መውሰዳቸው ሳይታለም የተፈታ ነው። ከአመታዊ በጀቱ አንድ ሶስተኛው ገንዘብ የሚመጣው ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ ህብረት ነው። የሰራዊቱን እና የደህንነቱን ደሞዝ እየፈሉ ያኖሩት ሃይሎች ፊታቸውን ሲያዞሩበት በኒዮ-ሪበራል ዜማ አሲዮ ቤሌማን ቢዘፍን አይደንቀንም።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: chris smith, Ethiopia, h res 128, hr 128, Left Column, sgr, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    April 11, 2018 10:52 pm at 10:52 pm

    ቂቂቂ!!! እናያለን ውጤቱን!!! ሞተናላ!!! ጨበርባሪዎች!!! ብርሃኑ ነጋ ቦንገር የከተማችን ከንቲባ ይሆናል። ቂቂቂ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule