• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ያልታሰበው H. Res. 128 ውሳኔ እና የህወሃት መብረክረክ

April 11, 2018 06:21 am by Editor 1 Comment

ያልታሰበ ነው። ፈጽሞ ያልተገመተ። አገዛዙን እንደ ቀትር መብረቅ ያስደነገጠ ውሳኔ። በጸረ-ሽብር ስም በሚተውኑት የፖለቲካ ድራማ ሳብያ አሜሪካ ይህን አይነት ውሳኔ አጋር በሆነ አካል ላይ ትፈጽማለች ብለው ለአፍታ እንኳን አስበውት አያውቁም። በዚያ ላይ ደግሞ በሚሊዮን ዶላር የሚከፈላቸው ሎቢስቶች ጉዳዩን ይዘውልናል ብለው ተዘናግተዋል። “ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አሕመድ ዕድል እንስጥ” የሚለው የኦክሎሃማው ሴናተር ጄምስ ኢንሆፍ ሃሳብ ያሸንፋል የሚል ግምትም ነበራቸው። ንቀታቸው እና ትዕቢታቸው የት እንደደረሰ የተመለከትነው፤ ሰነዱ ምክር ቤት ሊቀርብ ቀናት ሲቀረው እንኳ ዜጎችን ከእኩይ ተግባራቸው ያልመቆጠባቸው ነው። በሽብር የወነጀሏቸውን የዋልድባ መነኮሳት አሁንም እያሰቃዩዋቸው ይገኛሉ። ሰነዱ ሊጸድቅ አንዲት ቀን ሲቀረው በምስራቅ ሀረርጌ፤ ቆቦ ከተማ ነፍሰጡርዋን በጥይት ደበደቧት። በመጀመርያ አስገድደው ደፈሯት። ከዚያ ገደሏት።

ለሰብዓዊ ክብር የቆመ እና ሁሉን አቀፍ አስተዳደርን የሚደግፍ ሰነድ፤ ውሳኔ H.Res 128። በዩናይትድ ስቴይትስ ምክር ቤት ፊት ቀርቦ ያለ አንዳች ተቃውሞ ጸድቋል። ይህ አስደንጋጭ ውሳኔ የሁለቱን ሃገራት ግንኙነትን ወደ ሌላ ምዕራፍ የሚያሸጋግር ይመስላል።

ይህ ሰነድ አያሌ መሰናክሎችን አልፎ ለውሳኔ በቀረበበት ቅጽበት አምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን፤ ለአሜሪካ ኮንግረስ አንድ የተማጽኖ ደብዳቤ ልከው ነበር። እኚህ ሰው ከተለመደው የጸረ-ሽብር ማስፈራረያ ወጣ ብለው፤ መንግስታቸው ለለውጥ እያሳየ ያለውን ቁርጠኝነት ተናግረዋል። በነገሩ ላይ በግልጽ ለመምከር፤ ለጋራ ውይይትም ጋብዘዋል። “ውሳኔ ከማስተላለፍ ተቆጠቡ” ብለው የሕግ መምሪያ ምክር ቤቱን ቢጠይቁም፤ ጅብ ካለፈ… ሆነና አልተሳካም።

“በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና መከራ ይቁም፤ ለሁሉም እኩል የሆነች ኢትዮጵያ እውን ትሁን!” የሚል ሰነድ ማውጣት፤ ከፋቱ ምኑ ላይ እንደሆነ የሚረዱት የአገዛዙ ተጠቃሚዎች ብቻ ናቸው። ይሁን እንጂ “አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወርራታል” የሚለው የዘወትር የህወሃት ነጠላ ዜማ አሁን ስለተበላ ጨዋታቸውን የቀየሩ ይመስላል።

የእነ ስብሃት ነጋ “አይጋ ፎረም”፤ እንደ ደብተራ ክታብ በቀይ እና በጥቁር ቀለም አሸብርቆ አሜሪካን መሳደብ ጀምሯል። ውሳኔው አስገዳጅ ያልሆነ እና ተፈጻሚነትም እንደማይኖረው አይጋ ነግሮናል። በዚህ አላበቃም። በሃገር ጉዳይ ጣልቃ አትግቡ ሲልም የአሜሪካ ኤምባሲን ያስጠነቅቃል። የአሜሪካው አምባሳደር በኢትዮጵያ የጀመሩትን “የብተና ተልዕኮ” አስመልክቶ ጠ/ሚንስትር አብይ አህመድ ጠንካራ መልዕክት እንዲያስተላልፉም ያሳስባል።

የነ አባይ ጸሃይ “ትግራይ ኦንላይን” ድረ-ገጽም፤ የተለመደው የኒዮ ሊብራል ትርክት ይዞ ታላቋ አሜሪካን ለመሳደብ አፉን ከፍቷል። የሰብአዊ መብቱን ጉዳይ ሳይሆን የቻይና ጣልቃ ገብነት አሜሪካን እንዳላስደሰተ ሊነግረን ሞክሯል።

የወያኔ ብሎገሮችም ዝም አላሉም። የአንዳንዶቹ ሃሳብ እንደ ፔንዱለም መዋዠቁ ግን የተስፋ መቁረጡ እና የፍርሃቱን መጠን ይገልጸዋል። አንዱ ብሎገር “ውሳኔውን የሀዘን መግለጫ ነገር ነው። ለዛ ነው ድምጽ ራሱ ያልተሰጠበት።” ሲል ጽፏል።

“የሃዘን መግለጫ” ያሉት ይህ ውሳኔ እንዳያልፍ ከ80 ሚልዮን ብር በላይ ለምን እንዳወጡበት ግን ሊነግረን አይደፍርም። ውሳኔው “ምንም አያመጣም” ካሉን ታዲያ አሁን ሲጸድቅ ለምን ብርክ ያዛቸው?

ይህ ሰነድ ውሳኔ ሊሰጥበት የነበረው ባለፈው አመት ኦክቶበር 2/2017 ነበር። በወቅቱ በገጠመው የታሰበ እክል እንዲራዘም ተደረገ። የተራዘመበት ምክንያትም ግልጽ ነው። “ይህ ሕግ ካለፈ ከአሜሪካ ጋራ የሚኖረን ጸረ-ሽብርተኝነትን ድጋፍ እናቆማለን” በማለት የወያኔ መንግስት በይፋ ተናግሮ ነበር። ምክንያቱን ልብ በሉ! በንግድ ልውውጥ አይደለም። በባህልና ቱሪዝም ጉዳዮችም አይደለም። በጸረ-ሽብር ላይ አብሬ አልሰራም ነው ያሉት። የአሜሪካን ጦርነት የኢትዮጵያ ልጆች እንዲወጡት፤ ሁለቱ አካላት በፊት ለፊት ሳይሆን በጓሮ በር የተፈራረሙትን ሰነድ እንቀድደዋለን ሲሉ ነበር ያስፈራሩት። አንድ የአሜሪካ ዜጋ በሶማሊያ ምድር ላይ ከሚሞት ብለው፤ አንድ ሺህ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ስንገብር ነበር።

ሰነዱ እንዲሞት አገዛዙ ከፍተኛ የማባበል (ሎቢ) እና የማስፈራራት ስራ አየሰራ እንደነበር የተከበሩ እንደራሴ ማይክ ኮፍማን ተናግረዋል። ሾልኮ የወጣው መረጃ እንደሚጠቁመን አገዛዙ ይህን ለሚሰሩ ሎቢስቶች በወር 150ሺህ ዶላር ይከፍላል። ይህ ረቂቅ እዚህ ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ሃገሪቱ ካላት ውስን የውጭ ምንዛሪ 1.8 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሏል። እየገደሉ መኖርን መብታቸው ካላደረጉት በስተቀር ይህንን ያህል ገንዘብ ለባዕድ ደላሎች ከማዋል ይልቅ በገንዘቡ በርካታ ትምህርት ቤቶችን እና ክሊኒኮችን ይገነቡበት ነበር።

“በኢትዮጵያ ለሰብዓዊ ክብር የቆመ ሁሉን አቀፍ አስተዳደር እንዲኖር”፤ በማለት የሚጀምረው ይህ ሰነድ በኢትዮጵያ እየታዩ ያሉትን የመብት ጥሰቶችና በደሎች ያወግዛል። የአገዛዙ አካል ከልክ ያለፈ ሃይል መጠቀም እንዲያቆም። በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተካሄደው ግድያ እና ስቃይ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ገዳዮቹ/አስገዳዮቹ ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚሉ ጫና ሊፈጥሩ የሚችሉ ጠንካራ ድንጋጌዎችን ይዟል። ድንጋጌዎቹ ተፈጻሚ ካልሆኑ የሚወሰዱ እርምጃዎችም በአፈጻጸሙ ላይ ተገልጸዋል።

አሜሪካ እና አውሮፓውያን ላለፉት ሶስት አስርተ-ዓመታት ለራሳቸው ብሄራዊ ጥቅም ሲሉ፤ የኢትዮጵያ ችግር ችላ ብለው እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። የኢትዮጵያ ችግር አሁን ካለበት ጫፍ ደርሶ፤ ስርዓቱ ህዝባዊ እንቢተኝነት መንገዳገድ ሲጀምር የአሜሪካ የፖሊሲ ማሻሻል ለማድረግ መሞከርዋ፤ እንደተለመደው ሃይል ሚዛኑን ተከትሎ ቢሆንም አሁንም አልረፈደም። ህወሃት ሕዝባዊ መሰረት የሌለው፤ በመሳርያ ሃይል ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተቀመጠ ደካማ ድርጅት ነው። የአሜሪካ የገንዘብ እና ወታደራዊ ድጋፍ ባይኖረው ኖሮ እስካሁን በስልጣን ላይ ሊቆይ እንደማይችል ሁሉም ይገነዘባል።

በአሜሪካ ሳንባ የሚተነፍሱት የአውሮፓ ሕብረትና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትም ከዚህ በኋላ ዝምታቸውን ይሰብራሉ። የዚህን ሰነድ መጽደቅ ተከትለው ለጋሽ ሃገሮች ተመሳሳይ እርምጃ በወያኔ ላይ መውሰዳቸው ሳይታለም የተፈታ ነው። ከአመታዊ በጀቱ አንድ ሶስተኛው ገንዘብ የሚመጣው ከአሜሪካ እና ከአውሮፓ ህብረት ነው። የሰራዊቱን እና የደህንነቱን ደሞዝ እየፈሉ ያኖሩት ሃይሎች ፊታቸውን ሲያዞሩበት በኒዮ-ሪበራል ዜማ አሲዮ ቤሌማን ቢዘፍን አይደንቀንም።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: chris smith, Ethiopia, h res 128, hr 128, Left Column, sgr, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    April 11, 2018 10:52 pm at 10:52 pm

    ቂቂቂ!!! እናያለን ውጤቱን!!! ሞተናላ!!! ጨበርባሪዎች!!! ብርሃኑ ነጋ ቦንገር የከተማችን ከንቲባ ይሆናል። ቂቂቂ!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule