• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ

April 18, 2018 05:48 am by Editor Leave a Comment

እንደ መግቢያ

ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ስለዶ/ር አብይ ያለኝ የጠለቀ እውቀት ወይም ከነበሩበትና ከተነሱበት ፓርቲና ፓርቲው ከሚያራምደው የፖለቲካ አመለካከት ጋር ያለኝ ጠብ ወይም ዝምድና አይደለም። ይልቁንም እንደ አንድሀገር-ወዳድ ኢትዮጵያዊ ባለው የህወሃት የበላይነትን የተከተለ ፍጹም ዘረኛ ጉዞ ሄደን ሄደን የደረስንበት ደረጃ በጣም አሳሳቢ መሆኑን በመመልከት ነው።

በዘረኛው የወያኔ ከሩብ ምእተ አመት የዘለለ የጥፋት ጉዞ ውስጥ ከተጓዙና ከጉያቸው የበቀሉ ዘረኛው ስርአት ከሚያራምደው የተለየና የተሻለ ራእይ ያለው ጉዞን የመረጠ የኦሮሞ፣ የአማራ እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ ወጣቶች በደምና በህይወት ጭምር ዋጋ የከፈሉበትን ትግል ባዳመጠ መልኩ የተቃኘ ‘ቲም ለማ’ ከተባለ የለውጥ አራማጆች ውስጥ የበቀሉት የዶ/ር አብይ ራእይ ምን ቢሆን ለሐገር የሚበጅ መድህን ይሆናል የሚለውን ለማየት የአዲሱን ጠቅላይ ሚስተር ራእይ ከተጨባጭና ከሐሳብ ወለድ መንደርደሪያ በመነሳት ጠቃሚ ያልኩዋቸውን ምልከታዎች በማጣመር ለመመልከት እሞክራለሁ።

የዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ እንደማእከላዊ ነጥብ የዶ/ር አብይ ራእይ በማለት መጪውን የሀገሪቱን እጣ ፈንታ ለመመልከት በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ውስጥ ቲም ለማን አካቶ ማየትንና የኒሁ ወጣት የለውጥ አራማጅ መሪን ጉዞ እሳቸውና ቡድናቸው ለወጣት ኢትዮጵያውያን በፈነጠቁት ተስፋና ባሳዩት የኢትዮጵያዊነት ስሜት ላይ በተመሰረተ አላማ ዙሪያ መመልከቱ አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስቴር በወያኔ ዘመን ከተለመደውና በአንድ ጎሳ ጥቅም ዙሪያ ላይ አነጣጥሮ ከተመሰረተው ፓርቲያቸው (ኦሕዲድ) አላማ በሰፋ መልኩ የኦሮሞና የሌላው ኢትዮጵያዊ አንድነት በማይናወጥ መሰረት ባለው አመላካከታቸው በኢትዮጵያ መፈራረስ የሚምለው ህወሃት የጥፋት ጉዞን በፍርሐት ቆፈን ሳይሆን በተረጋጋ አስትዋይ ኢትዮጵያዊ አእምሮ መመልከታችውን በግልጽ በማሳየታችው ይህንን ራእይ ዘመኑ በፈጠረብን መጠራጥር ውስጥም እንኩዋን ተስፋን ልንቸረው ይገባል ባይ ነኝ።

የአብይን ራእይ በሐይለማሪያም ራእይ (እሱም ከነበረ) ለማወዳደር ባልዳዳም ጠቅላይ ሚኒስትርነት በኢትዮጵያ ምን ያህል የተዋረደና ተራ የአዛውንት ወያኔዎች ተላላኪ ከመሆን የዘለለ ወሳኝ ከፍተኛ የስልጣን ደረጃ መሆኑን ለመመልከት ያለንን ጉጉትና ፍላጎት ከፍ ማድረጉን ግን በንጽጽር መግለጹ ጥሩ ማሳያ ነው የሚል ስሜት አለኝ።

እነዶ/ር አብይ በብዙ ኢትዮጵያን ያተረፉት ቅቡልነት ‘ከሀምሳ ዘመን በላይ ዘርና ዘርን ብቻ ያቀነቀኑ የብሔር ፖለቲከኞት ለምን አላገኙትም?’ ብለን ብንል መልሱ ለኢትዮጵያዊነት የሰጡት ክብርና ስለሓገር አንድነት የተናገሩት መሳጭ ንግግሮቻቸው ለመሆኑ ብዙ አስረጂ የሚጠይቅ ጉዳይ አይመስለኝም።

ስርነቀል ወይስ የጥገና ለውጥ?

በኢትዮጵያ ለውጥ መደረግ የነበረበት የህወሀት የጥፋት መርዝ ስር ሳይሰድ በመጀመሪያወቹ ሁለትና ሶስት አመት የወያኔ የስልጣን ዘመን መሆን እንደነበረበት ቢሰማኝም አሁንም የቆሰለው አውሬ ሳያገግም በተጋጋለው የወጣቶች ትግል ታጅቦ መቀጠሉ የዚህን አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ራእይ የሁላችን የጋራ ራእይ የማድረግ አቅም በመስጠት ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስቴር በብዙ ምክኛቶች ወደሑዋላ ልመልከት ቢሉ እንኳን እንደሎጥ ሚስት እንደጨው አድርቆ የሚያስቀራቸው ይሆናል።

እነዶ/ር አብይ ሚና በለውጥ ሚዛን ሲታይ የጥገና ለውጥ አራማጅ (reformist) ሚናው ጎላ ይላል። ይህ የለውጥ አይነት ብዙዎቻችን ከወያኔ እኩይ ተልእኮ ልምድ በመነሳት የማንቀበለው ቢሆንም በአንጻሩ ከወያኔ ሀገሪቱ የተሰራችበትን ድርና ማግ የመበታተን የሩብ ምእተ አመት እኩይ ስራ በኋላ የሐገሪቱን የፓለቲካ አቅጣጫ በቀላሉ ወደ አዲስ ስርነቀል የለውጥ መንገድ መዘወር የራሱ የሆኑ ተፈጥሮአዊ አደጋውም የከፋ ውጤት ሊያመጣ መቻሉን ማሰተዋል የግድ ይላል። ይህንንም ሂደት የወጣቱ የትግሉ ወላፈን ለኣፍታም እንኳን ሳይቋረጥ ይህንን መሰረታዊ ሊባል የሚችል ግን የጥገና ለውጥ በጥሩ ተስፋና ቅቡልነት መመልክቱ ተገቢ መስሎ ይሰማኛል።

በመጨረሻም ለስር ነቀል ለውጥ ብንጓጓም እንኳን በምድር ላይ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ የስርነቀል ለውጥ አራማጅ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አደረጃጀት የደረሰበት የእድገት ደረጃ እምብዛም የበሰለ ተስፋ ፈንጣቂ አለመሆኑን መመልከታችን ወደቲም ለማ ለማሸብረክና ሐገርን ከጥፋት ለመታደግ የመጣ ቅርብ እድል መሆኑን በማሰብ በተስፋ እንድንመለከተው ያደርገናል።

እንደማጠቃለያ

ይህንን አጭር ጽሁፍ ስሞነጫጭር ዶ/ር አብይ ቃለመሐላ አድርገው የተናገሩትን የመጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትራዊ ንግግራቸውን ደጋግሜ አዳመጥኩ። ፓርቲያቸውን ኢህአዴግን ሲያመሰግኑ ለወያኔ ባለሐብቶችም በህዝብ አመጽ እንዳይዘረፉ ዋስትና ሲሰጡ ባዳምጥም ከለውጣቸው እስትራተጂነት ወይንም ከመሳሰሉ ቀጣይ ቅን መሰል ጉዞዎች በዘለለ መሰሪ ወይንም ግልብጥብጥ ያለ ሐይለማርያማዊ ስነምግባር የጎደለው ተላላኪነት አይመስልም። ከግል የቤተሰባቸው ትርክት፣ ከቀደም የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ከዘረኝነት ጥላቻም ሆነ ለወደቁ ወጣት የለውጥ ተፋላሚዎች ይቅርታ አጠያየቅ ስመለከት በጣም ተመሰጥክ አትበሉኝና ይህ ነው የምለው እንከን አላገኝሁባቸውም።

ይልቁንም በቃላቶቻቸው ለቤተመንግስቱ ርቆ የነበረውን የከበረ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ በድፍረት በመናገራቸው ቤተመንግስቱን የተጥናወተው ተጻራሪ ኢትዮጵያዊ መንፈስ እንዳይተናኮላቸው ሰጋሁ፥፥

እግዚአብሔር አኢትዮጵያን ይጠብቅ አሜን!

ከበቀለ ደገፋ (t.mesafint@gmail.com)
ሚያዝያ 2010 ዓ.ም.


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule