• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ

April 18, 2018 05:48 am by Editor Leave a Comment

እንደ መግቢያ

ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ስለዶ/ር አብይ ያለኝ የጠለቀ እውቀት ወይም ከነበሩበትና ከተነሱበት ፓርቲና ፓርቲው ከሚያራምደው የፖለቲካ አመለካከት ጋር ያለኝ ጠብ ወይም ዝምድና አይደለም። ይልቁንም እንደ አንድሀገር-ወዳድ ኢትዮጵያዊ ባለው የህወሃት የበላይነትን የተከተለ ፍጹም ዘረኛ ጉዞ ሄደን ሄደን የደረስንበት ደረጃ በጣም አሳሳቢ መሆኑን በመመልከት ነው።

በዘረኛው የወያኔ ከሩብ ምእተ አመት የዘለለ የጥፋት ጉዞ ውስጥ ከተጓዙና ከጉያቸው የበቀሉ ዘረኛው ስርአት ከሚያራምደው የተለየና የተሻለ ራእይ ያለው ጉዞን የመረጠ የኦሮሞ፣ የአማራ እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ ወጣቶች በደምና በህይወት ጭምር ዋጋ የከፈሉበትን ትግል ባዳመጠ መልኩ የተቃኘ ‘ቲም ለማ’ ከተባለ የለውጥ አራማጆች ውስጥ የበቀሉት የዶ/ር አብይ ራእይ ምን ቢሆን ለሐገር የሚበጅ መድህን ይሆናል የሚለውን ለማየት የአዲሱን ጠቅላይ ሚስተር ራእይ ከተጨባጭና ከሐሳብ ወለድ መንደርደሪያ በመነሳት ጠቃሚ ያልኩዋቸውን ምልከታዎች በማጣመር ለመመልከት እሞክራለሁ።

የዶ/ር አብይ አህመድ ራእይ እንደማእከላዊ ነጥብ የዶ/ር አብይ ራእይ በማለት መጪውን የሀገሪቱን እጣ ፈንታ ለመመልከት በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ውስጥ ቲም ለማን አካቶ ማየትንና የኒሁ ወጣት የለውጥ አራማጅ መሪን ጉዞ እሳቸውና ቡድናቸው ለወጣት ኢትዮጵያውያን በፈነጠቁት ተስፋና ባሳዩት የኢትዮጵያዊነት ስሜት ላይ በተመሰረተ አላማ ዙሪያ መመልከቱ አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስቴር በወያኔ ዘመን ከተለመደውና በአንድ ጎሳ ጥቅም ዙሪያ ላይ አነጣጥሮ ከተመሰረተው ፓርቲያቸው (ኦሕዲድ) አላማ በሰፋ መልኩ የኦሮሞና የሌላው ኢትዮጵያዊ አንድነት በማይናወጥ መሰረት ባለው አመላካከታቸው በኢትዮጵያ መፈራረስ የሚምለው ህወሃት የጥፋት ጉዞን በፍርሐት ቆፈን ሳይሆን በተረጋጋ አስትዋይ ኢትዮጵያዊ አእምሮ መመልከታችውን በግልጽ በማሳየታችው ይህንን ራእይ ዘመኑ በፈጠረብን መጠራጥር ውስጥም እንኩዋን ተስፋን ልንቸረው ይገባል ባይ ነኝ።

የአብይን ራእይ በሐይለማሪያም ራእይ (እሱም ከነበረ) ለማወዳደር ባልዳዳም ጠቅላይ ሚኒስትርነት በኢትዮጵያ ምን ያህል የተዋረደና ተራ የአዛውንት ወያኔዎች ተላላኪ ከመሆን የዘለለ ወሳኝ ከፍተኛ የስልጣን ደረጃ መሆኑን ለመመልከት ያለንን ጉጉትና ፍላጎት ከፍ ማድረጉን ግን በንጽጽር መግለጹ ጥሩ ማሳያ ነው የሚል ስሜት አለኝ።

እነዶ/ር አብይ በብዙ ኢትዮጵያን ያተረፉት ቅቡልነት ‘ከሀምሳ ዘመን በላይ ዘርና ዘርን ብቻ ያቀነቀኑ የብሔር ፖለቲከኞት ለምን አላገኙትም?’ ብለን ብንል መልሱ ለኢትዮጵያዊነት የሰጡት ክብርና ስለሓገር አንድነት የተናገሩት መሳጭ ንግግሮቻቸው ለመሆኑ ብዙ አስረጂ የሚጠይቅ ጉዳይ አይመስለኝም።

ስርነቀል ወይስ የጥገና ለውጥ?

በኢትዮጵያ ለውጥ መደረግ የነበረበት የህወሀት የጥፋት መርዝ ስር ሳይሰድ በመጀመሪያወቹ ሁለትና ሶስት አመት የወያኔ የስልጣን ዘመን መሆን እንደነበረበት ቢሰማኝም አሁንም የቆሰለው አውሬ ሳያገግም በተጋጋለው የወጣቶች ትግል ታጅቦ መቀጠሉ የዚህን አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ራእይ የሁላችን የጋራ ራእይ የማድረግ አቅም በመስጠት ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስቴር በብዙ ምክኛቶች ወደሑዋላ ልመልከት ቢሉ እንኳን እንደሎጥ ሚስት እንደጨው አድርቆ የሚያስቀራቸው ይሆናል።

እነዶ/ር አብይ ሚና በለውጥ ሚዛን ሲታይ የጥገና ለውጥ አራማጅ (reformist) ሚናው ጎላ ይላል። ይህ የለውጥ አይነት ብዙዎቻችን ከወያኔ እኩይ ተልእኮ ልምድ በመነሳት የማንቀበለው ቢሆንም በአንጻሩ ከወያኔ ሀገሪቱ የተሰራችበትን ድርና ማግ የመበታተን የሩብ ምእተ አመት እኩይ ስራ በኋላ የሐገሪቱን የፓለቲካ አቅጣጫ በቀላሉ ወደ አዲስ ስርነቀል የለውጥ መንገድ መዘወር የራሱ የሆኑ ተፈጥሮአዊ አደጋውም የከፋ ውጤት ሊያመጣ መቻሉን ማሰተዋል የግድ ይላል። ይህንንም ሂደት የወጣቱ የትግሉ ወላፈን ለኣፍታም እንኳን ሳይቋረጥ ይህንን መሰረታዊ ሊባል የሚችል ግን የጥገና ለውጥ በጥሩ ተስፋና ቅቡልነት መመልክቱ ተገቢ መስሎ ይሰማኛል።

በመጨረሻም ለስር ነቀል ለውጥ ብንጓጓም እንኳን በምድር ላይ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ የስርነቀል ለውጥ አራማጅ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አደረጃጀት የደረሰበት የእድገት ደረጃ እምብዛም የበሰለ ተስፋ ፈንጣቂ አለመሆኑን መመልከታችን ወደቲም ለማ ለማሸብረክና ሐገርን ከጥፋት ለመታደግ የመጣ ቅርብ እድል መሆኑን በማሰብ በተስፋ እንድንመለከተው ያደርገናል።

እንደማጠቃለያ

ይህንን አጭር ጽሁፍ ስሞነጫጭር ዶ/ር አብይ ቃለመሐላ አድርገው የተናገሩትን የመጀመሪያ ጠቅላይ ሚኒስትራዊ ንግግራቸውን ደጋግሜ አዳመጥኩ። ፓርቲያቸውን ኢህአዴግን ሲያመሰግኑ ለወያኔ ባለሐብቶችም በህዝብ አመጽ እንዳይዘረፉ ዋስትና ሲሰጡ ባዳምጥም ከለውጣቸው እስትራተጂነት ወይንም ከመሳሰሉ ቀጣይ ቅን መሰል ጉዞዎች በዘለለ መሰሪ ወይንም ግልብጥብጥ ያለ ሐይለማርያማዊ ስነምግባር የጎደለው ተላላኪነት አይመስልም። ከግል የቤተሰባቸው ትርክት፣ ከቀደም የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ከዘረኝነት ጥላቻም ሆነ ለወደቁ ወጣት የለውጥ ተፋላሚዎች ይቅርታ አጠያየቅ ስመለከት በጣም ተመሰጥክ አትበሉኝና ይህ ነው የምለው እንከን አላገኝሁባቸውም።

ይልቁንም በቃላቶቻቸው ለቤተመንግስቱ ርቆ የነበረውን የከበረ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ በድፍረት በመናገራቸው ቤተመንግስቱን የተጥናወተው ተጻራሪ ኢትዮጵያዊ መንፈስ እንዳይተናኮላቸው ሰጋሁ፥፥

እግዚአብሔር አኢትዮጵያን ይጠብቅ አሜን!

ከበቀለ ደገፋ (t.mesafint@gmail.com)
ሚያዝያ 2010 ዓ.ም.


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule