• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዶ/ር አብይ አህመድ አዋላጅነት ጉዳይ

April 20, 2018 05:38 am by Editor 1 Comment

ቃሉ የሕዝብ ነው። ቃሉንም በተግባር የሚተረጉመው ሕዝብ ነው። የወንዝ ውሃ ሽቅብ እንደማይፈስ ሁሉ፥ ይህም ቃል ወደ ተግባር ሳይቀየር ይቀለበሳል ብሎ መጠበቅ ተገቢ አይደለም። ይልቁንስ ይህን ቃል ለመተግበር የዶ/ር አብይ ድርሻ ምንድነው ብሎ አውቆ በዚያው ሚዛን ብቻ እርሳቸውን መመዘን ያስፈልገናል። ለሕዝብ ታማኝ ባይሆኑ፥ እሳቸው ከታሪካዊነት ይጎድላሉ እንጂ የሕዝብ ቃል ዕውን መሆኑ አይቀሬ ነው። ዶ/ር አብይ አህመድ የሚናገሩት ቃል እርሳቸው የፈለሰፉት ስለሆነ አይደለም የተወደደው። ቃሉ የሕዝብ ቃል ስለሆነ ነው እንጂ። ይህ ሰሚ ያጣ ሕዝብ በትግሉ የራሱን ቃል የሚያስተጋባ ጠ/ሚ ሊያመጣ ቻለ። ታዲያ ይህን ቃል የዶ/ር አብይ የግል ንብረት ተደርጎ፥ ቃል ዋጋ የለውም ብሎ ቃሉን ማጣጣል ለኢትዮጵያ አይጠቅምም። የውልጃ አብሳሪ የሆነ ቃል በውልደት ቀን ዋዜማ ሲሰማ፥ በተስፋና በትጋት ይህን የሕዝብ ቃል በክብር መያዝ ይገባል። ይህ ታላቅና አስገራሚ ሕዝብ ቃሉን በአደባባይ ካሳወጀ በሁዋላ፥ ይህ ቃል አይተገበርም ማለት የቃልን ምንነትና የቃሉ ነፀብራቅ የሆነውን ሕዝብ ማንነት ያለማወቅ ነው።

ከአሁን በሁዋላ በምድራችን የሚሆነውን ነገር ለማወቅ ከተፈለገ ወደ ፊት በማየት ማገናዘብ እንጂ ወዳለፈው ታሪካችን እየተመለከትን ሽንፈትን ማስተናገድ አይበጅም። በመጀመሪያ ቃል ተወለደ። ይህ ቃል ቀጥሎ ዲሞክራሲን ይወልዳል። ዲሞክራሲ ሁሉን የኢትዮጵያ ልጆችን አሳትፎ አዲሲቷን ኢትዮጵያ ያስወልዳል። ስለዚህ ይህ የታወጀው ቃል የምጥ መጀመሪያ ነው። ያለፈውን የእርግዝና ወቅት ሳይሆን አሁን ያለውን አዲስ የምጥ ሂደት ማስተናገድ ይገባናል። መወለድን ማስተጓጎል ቀርቶ ማዘግየት የሚቻልበት ወቅት ላይ አይደለንም።

እናስተውል። አሁን ቸኩለን ስለ አዲሲቷ ኢትዮጵያ ማውራትና መጠየቅ አንችልም። አሁን ዶ/ር አብይን በቅድሚያ የዲሞክራሲ አዋላጅነታቸውን ግዴታ እንዲወጡ ብቻ በተጠያቂነት መያዝ ይኖርብናል። ከዚያ ዲሞክራሲ ተቃዋሚ የሆኑትን ሃይላት ወደ አማራጭ ሃይልነት ቀይሮ ተባባሪ አዋላጅ ያደርጋቸዋል። ያኔ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብን ያሳተፈ ሂደት አዲሲቷን ኢትዮጵያ እንድትወለድ መቻልን ያመጣል። ሁሉንም የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚዳኝ ሕዝብ ነው። ለዚያ ዲሞክራሲ የመጀመሪያው መሰረት ነው። ስለዚህ ይህን የሕዝብ ቃል ይዘን ዲሞክራሲ በቅድሚያ ይወለድ ዘንድ ግድ እንበል።

ኢትዮጵያን በጎሰኝነት ከፋፍሎ ሊበትን ጠላት ያቀደው በቃል ነበር። ፈጣሪ ኢትዮጵያን ወደሚጠብቃት ታላቅ ክብርና ሞዴልነት የሚወስዳትን ጉዞ የሚያስጀምረውም በቃል ነው። የአዋላጅነት ተልዕኳቸውን እንዲወጡ ዘብ መቆም እኛም ከአዋላጆቹ ጎራ እንድንመደብ ያደርገናል። ዶ/ር አብይን በብዙ ጉዳይ እያዋከብናቸው እና አፍራሽ ቃል በመጠቀም ጥሪያቸውን እንዳይወጡ ለጠላት መጠቀሚያ እንዳንሆን እንወቅበት። በዶ/ር አብይ አዋላጅነት ሊሆን ያለውን ድል እንቅፋት እንዳንሆን መጠንቀቅ እጅግ ያስፈልገናል። ይህን የኢትዮጵያ ልጅ ለመውቀስም ሆነ ለማሞገስ አንዱንና ብቸኛውን ዲሞክራሲ ላይ ትኩረት በማድረግ መሞገትና ተጠያቂ ማድረግ መልካም ነው።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!

ዶ/ር ዘላለም እሸቴ

ኢሜል: ethioStudy@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Lemma says

    April 25, 2018 07:50 pm at 7:50 pm

    This doctor uses his brain to think positive, and objectively. Endih yemitasibu berket belu, bizu.
    It is clear that reform does not bring us to our goal, but it is, if we take part in utilizing, a step toward our final show-down.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule