በትናንትናው ዕለት በሕይወቴ ለመጀመርያ ጊዜ በኢትዮጵያ የፖሊቲካ ታሪክ ውስጥ ሥልጣን ካንዱ ጠ/ሚንስትር ወደ ሌላው ሲሸጋገር በአደባባይ በማየቴ ለማመን እየተቸገርኩኝ ነው። በጠ/ሚንስትሩ ንግግር ውስጥም ላለፉት አርባ ዓመታት የለመድናቸው “ጠላት” “ጸረ ሰላም ኃይሎች” “እናሸንፋለን” የመሳሰሉ ካድሬያዊ አነጋገሮች ለመጀመርያ ጊዜ በመሪያችን አፍ አለመነገሩን፣ ተፎካካሪ እንጂ ተቃዋሚ እንደሌለ መስማት፣ የተለየ አስተሳሰብ ስላስተናገዱ ብቻ የተገደሉትን የፖሊቲካ መሪዎችና በጨቅላነታቸው የተቀጩትን አስታውሶ ይቅርታ መጠየቅ፣ ከልብ ይቅር ተባብሎ ያለፈውን ምዕራፍ ዘግቶ ወደ ፊት ለመራመድ መጋበዝ፣ ከኤርትራ ጋር በሰላም ለመኖር ከማሰብ አንጻር ንግግር ለመጀመር ዝግጁ መሆን፣ ከሁሉም በላይ ለዘመናት እንደ “ገበና” ተቆጥሮ የማይነገረውን የግልን ህይወት ለአደባባይ ፍጆታ ቀርበው ስናዳምጣቸው … [Read more...] about የጠቅላይ ሚንስትሩ ተስፋ ሰጪ ንግግርና የኛ ሚና!
Opinions
የኔ ሃሳብ
QUE SERA SERA!
Whatever will be, will be! Ethiopia has a new Prime Minister. Actually we never had Prime Ministers so far, for the last almost 27 years but Prime Miseries. None of them talked before, about Ethiopia. Dr Abiy Ahmed Ali talked about Ethiopia. That does sound like the Prime Minister of Ethiopia. Does it? Time will tell. Que sera sera! I have never called the Woyyane House of Cards, the EPRDF, by its fake name. For me, EPRDF was just a cover coat. The real body inside was the TPLF, or the … [Read more...] about QUE SERA SERA!
ህዝባዊ ትግል መቀጠሉ ነው ዋስትናው
የተደራጀ ኃይል ወደተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርዓስት ያደርሰኛል ብሎ ብዙ የጠበቀውና መስዋዕት ሲከፍል የኖረው የኢትዮጵያ ህዝብ ዛሬ በራሱ አመፅ የትግሉ ባለቤት ሆኗል። በኦሮምያ፣ በአማራ፣ በደቡብና በተለያዩ ቦታዎች በአምባገነኖች ጥይት ግንባራቸው እየተመታ የወደቁት፣ በእስር የሚማቅቁት፣ ተፈናቅለው የተሰደዱት ሁሉ የዚህ ወይንም የዚያ ድርጅት አባላት አይደሉም። በተቃውሞ ሰልፍ፣ በመንገድ መዝጋት፣ቤት ውስጥ በመቀመጥ፣ የነዳጅ ትራንስፖርት በማገድ፣ ሱቅ በመዝጋት፣ ግብር ባለመክፈል፣ ትጥቅ ላለመፍታት ገድሎ በመሞት፣ በኳስ ሜዳዎችና በህዝባዊ ስብሰባዎች ዘራፊ አምባገነኖችን በማጋለጥ፣ በመደበኛና በሶሻል ሚድያ ቅስቀሳ በማድረግ ስርዓቱን የሚይዘውና የሚጨብጠው ያሳጣው በዚህ ወይንም በዚያ ድርጅት አመራር የሚንቀሳቀስ አካል ብቻ አይደለም። የዘመናት ብሶት ያደቀቀው በቃኝ ብሎ ለተመሳሳይ ዓላማ … [Read more...] about ህዝባዊ ትግል መቀጠሉ ነው ዋስትናው
ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
በዶ/ር አብይ የሹመት ንግግር ውስጥ፤ ይቅርታ፣ እርቅ፣ ካሳ፣ ዲያስፖራ፣ ኤርትራ፣ ሙስና፣ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ የባከነ እድል፣ ስለ ዘረኝነት በሽታ እና የኢትዮጵያ ታላቅነት ተነስተዋል። “በቅጡ ሳይቧርቁ ሕይወታቸው ለተቀጠፈ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ለስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ቀውስ ለተዳረጉ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከልብ የመነጨ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ሲሉ ጀመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ። በተለያየ ግዜያት መስዋዕትነትን ለከፈሉ፤ የመብት ተከራካሪዎች እና የፖለቲካ ስዎች ለደረሰው ጉዳት፣ ለፈሰሰው ደም እና ለጠፋው ህይወት፤ ይቅርታ ብቻ ብለው አላለፉም። ለተፈጠረው ችግር እልባት፤ ለተበደለ ወገን ደግሞ ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። “ከስህተታችን ተምረን ሃገራችንን የምንክስበት ወቅት ነው!” ማለታቸው ራሱ ንግግራቸውን በተግባር ለመተርጎም ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳየናል። የመርህ … [Read more...] about ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
ዘብ ቆመናል ክቡር የኢትዮጵያ ልጅ ዶ/ር አብይ አህመድ
ሁላችንም ካለንበት አጣብቂኝ ውስጥ መውጫ መንገድ አጥተን ተፋጠን ሰንብተናል። ስንነካከስ እንዳንጠፋፋ በሚያስፈራበት መልኩ ሁላችንም ግብ ግብ ስንገጥም እዚህ ደረስን። መንግስት በጉልበቱ ሲገፋበት፥ ሕዝብ በአመፁ ሲዘልቅበት፥ አማራጭ ኃይል በሁሉ አቀፍ ትግሉ ሲዘምትበት፥ አካሄዱ ሁሉ ሲያስፈራ የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን ያሰኝ ነበር። ሕዝቡ ሁሉ በሁሉም አቅጣጫ ወደ አምላኩ ከመጮህ አልተቆጠበም። በአራቱም አቅጣጫ አንድነቷን እና ብልጽግናዋን በማይወዱ የተከበበች ሀገር ሆና ሳለ፥ ከውስጥ ደግሞ በነውጥ ስትናጥ ተስፋዋ እየመነመነ ጫፍ ደርሶ ነበር። ምን አልባት ታዲያ የማታ ማታ ፈጣሪዋ ኢትዮጵያን ከምጥ ሊገላግላት፣ ውጥረቷን አርግቦ ሰላምን ሊሰጣት አስቦ ይሆን ዶ/ር አብይ እርስዎን ወደ አመራር ያመጣዎት? ካለንበት አጣብቂኝ ለመውጣት ረዥም መንገድ መሄድ እንዳለብን እሙን ነው። ዶ/ር … [Read more...] about ዘብ ቆመናል ክቡር የኢትዮጵያ ልጅ ዶ/ር አብይ አህመድ
ከአንድ አማራ ንቅናቄ የዶ/ር አብይ አህመድ መመረጥን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የአንድ አማራ ንቅናቄ ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውሃገራች ን መስቀለኛ መንገድ ላይ በደረሰችበት በዚህ ወቅት ላይ በመመረጥዎ ሃላፊነትዎን ከመቼውም ግዜ በላይ ወሳኝና ታሪካዊ ያደርገዋል ብለን እናምናለን። የአማራው ሕዝባችን የእርሶን መመረጥ አስመልክቶ የብሄር ፤ የቋንቋና ፤ የማንነትድንበር ሳያግደው ለእርሶ ያሳየው ድጋፍና እምነት በግልጽ የሚታይ ሃቅ ነው:: አማራው ትላንትም ዛሬም ሆነ ወደፊት በሃሳብ ጥራት በስልጡንና ጨዋ የፖለቲካ ባህል ለሚያምን : ሃገራዊና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸውን መሪዎች የሚከተልና የሚያከብር በመሆኑ እርስዎ ከዚህ ቀደም በአደባባይ ካቀረቡት ወገናዊና ስነምግባራዊ አቀራረብ መነሻ በማድረግ ድጋፉን ያለማንገራገር እየገለጸ ይገኛል። ሃገራችን ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት አደጋና ከገባችበት ከፍተኛ የፖለቲካ አጣብቂኝለመላቀቅ ስር ነቀል … [Read more...] about ከአንድ አማራ ንቅናቄ የዶ/ር አብይ አህመድ መመረጥን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የትግላችን መነሻና መዳረሻ ምንድነው?
ብቅ ብቅ ባለ ሣር የተሳበ በሬ፡አፏን ከከፈተች መሬት ይተርፍ ይሆን! ለምን ሕዝባዊ ትግል አስፈለገ?መስዋዕትነቱስ የሚከፈለው ምንስ ለመቀዳጀት ይሆን? ህይወት፤ ዕውቀት፤ጊዜና ገንዘብለሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ነገሮች ናቸው። የሰው ልጅ እነዚህን መሠረታዊ ሀብቶቹን አሳልፎ መስጠት ካለበት በአንጻሩ ብልጫ ያለው ካልሆነም ተመጣጣኝ የሆነ ምላሽ መሻት ይገባዋል። ብሶት ብዙ ጊዜ የሚፈጥረው ትግል፤ በአግባቡ ካልተደራጀና ከታች ወደ ላይ ከላይ ወደ ታች በሚንቀሳቀስ አካሄድ ካልተመራ፣ትግሉ ያልተቀነባበረና ግብታዊነት የሰፈነበት ይሆናል።በንቃት የተደራጀ ከሆነ ቀጣዩን ትግል መልክ ለማስያዝ ጠንካራ ድርሻ ይኖረዋል። በዚህ መልክ ትግሉ ከተመራ የሚከፈለው መሰዋዕትነት በዉጤት የጎመራ ይሆናል። እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባ ዐብይ ጉዳይ በተበታተነ መልክ ለሚደረግ ትግል የሚከፈለውመሰዋዕትነት … [Read more...] about የትግላችን መነሻና መዳረሻ ምንድነው?
የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
እርግጥ እንደ መለስ ዜናዊ ባለ ሙሉ ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል? ከልክ በላይ ለጥጠው፤ እንደ ልብ አንጠልጥል ፊልም ያቆዩትን ፍትግያ ትናንት በዜና ሲሰብሩት ደስታቸውን ይገልጹ የነበሩት ዜጎች ጥቂት አልነበሩም። ወትሮውን በስብሻለው ከሚለን ስራዓት አዲስ ነገር የሚጠብቅ ተስፈኛ ቢደሰት ብዙም አይደንቅም። የጠቅላይ ሚንስትር እንጂ የስራዓት ለውጥ መች ተመለከትን? ዶ/ር አብይ አህመድ በዚህ ቀውጢ ሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ መመረጡ ግን ከክብሩና ከስልጣኑ ይልቅ ፈተናው ያመዝናል። ለሶስት ቀናት ተብሎ የተጀመረው ግብግብ ይሉት ክርክር በተነገረለት ቀን መቋጨት ያለመቻሉ በራሱ የሚነግረን ነገር ነበር። አወዛጋቢው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ፣ ፓርላማ ላይ በጸደቀበት ወቅት ዶ/ር አብይ በስፍራው ባለመገኘታቸው የህወሃት ሰዎች ክፉኛ እንደተበሳጩ አይተናል። ይህንን ቅሬታ በብሎገሮቻቸውም … [Read more...] about የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
Ethiopia arrests 11 journalist, bloggers and activists
AHRE has found that 11 journalists, bloggers and activists arrested during the weekend, including recently released political prisoners, On March 25 2018, Ethiopian Police and Security forces arrested journalists Eskindir Nega and Temesgen Dessalege, activists Andualem Arage, Addisu Getinet, Yidnekachewu Addis, Sintayehu Chekol, Tefera Tesfaye and Woynshet Molla, and bloggers Mahlet Fantahun, Befiqadu Hailu, Zelalem Workagegnhu, and Fekadu Mehatemework, Their arrest was ordered by the Command … [Read more...] about Ethiopia arrests 11 journalist, bloggers and activists
ሲመቱት ይጠብቃል
የኢትዮጵያ ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የሚገባውን እንደዜጋ በነፃነት የመኖር መብት ለመጎናፀፍ ያደረገው ጥረት ሁሉ በአምባገነኖቹ እየተዳጠ አሁን ላለበት ዝቅተኛ ኑሮና ለከት ያጣ ግፍ ተዳርጓል። የግፉ ፅዋ ሞልቶ መፍሰስ በመጀመሩም ከአስከፊው ስርዓት ጨርሶ ለመላቀቅ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት እልህ አስጨራሹን ትግል ተያይዞታል። የአሁኑ ትግል ካለፉት በብዙ መልኩ የተለየ ነው። ህዝባዊ አመፁ ሰከን ያለና ህዝቡን ከዳር ዳር ያሳተፈ ለአምባገነኖቹ ጨርሶ ያልተመቸ፣ ግፈኛውን አገዛዝ ቀስ በቀስ እየደማ እንዲሞት የሚያደርግ ነው። ፈረንጆች ሚስማር ሲመቱት እያደር ይጠብቃል እንዲሉ፤ ባለመዶሻው ወያኔ የህብረተሰቡ አንጓ የሆኑትን ራስ ራሳቸውን መታሁ ሲል የበለጠ ማህበራዊ ትስስሩንና የትግሉን ሂደት ሲያጠብቁት እናያለን። አማራውን በጠላትነት በፕሮግራሙ ነድፎ ከሌላው ህብረተሰብ ጋር በማቃቃር … [Read more...] about ሲመቱት ይጠብቃል










