
የአንድ አማራ ንቅናቄ ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውሃገራች ን መስቀለኛ መንገድ ላይ በደረሰችበት በዚህ ወቅት ላይ በመመረጥዎ ሃላፊነትዎን ከመቼውም ግዜ በላይ ወሳኝና ታሪካዊ ያደርገዋል ብለን እናምናለን።
የአማራው ሕዝባችን የእርሶን መመረጥ አስመልክቶ የብሄር ፤ የቋንቋና ፤ የማንነትድንበር ሳያግደው ለእርሶ ያሳየው ድጋፍና እምነት በግልጽ የሚታይ ሃቅ ነው:: አማራው ትላንትም ዛሬም ሆነ ወደፊት በሃሳብ ጥራት በስልጡንና ጨዋ የፖለቲካ ባህል ለሚያምን : ሃገራዊና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸውን መሪዎች የሚከተልና የሚያከብር በመሆኑ እርስዎ ከዚህ ቀደም በአደባባይ ካቀረቡት ወገናዊና ስነምግባራዊ አቀራረብ መነሻ በማድረግ ድጋፉን ያለማንገራገር
እየገለጸ ይገኛል።
ሃገራችን ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት አደጋና ከገባችበት ከፍተኛ የፖለቲካ አጣብቂኝለመላቀቅ ስር ነቀል የፖለቲካ መፍትሄ በሚያስፈልግበት በዚህ ቀውጢ ጊዜ እንደቀደሙት ጠቅላይ ሚንስትር የሕወሃትን የዘረፋና የጭቆና አገዛዝ ለማስቀጠል በታለመ መልኩ የመሪነት ስልጣኑን ይቀበላሉ ብለን የማናምን በመሆኑ የሃላፊነት ግዜዎን በተስፋና በበጎ ምኞት የምንመለከተው መሆኑን እንገልጻለን።
ዘረኛውና ዘራፊው የትግራይ ነጻ አውጪ ቡድን ከተነሳበት አደገኛ ሕዝባዊ ተቃውሞና ተቀባይነት የማጣት አደጋ ብቸኛው መውጫ መፍትሄው አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር በመቀየር ለውጥ ይመጣል ብለን አናምንም። ነገር ግን የሃገራችን ኢትዮጵያን ስም በመልካምና በክብር አንደበት በመጥራት ላሳዩን ክብር ከጽንፈኛና ዘራፊ የትግራይ እብሪተኞች የተሻሉ ሊሆኑ ይችላሉ በማለት እንገምታለን።
ምንም እንኳን አማራውን በይፋ የወከለ፥ እውነተኛ ወኪል በግልጽ ያልተሳተፈበትምርጫ ፍትሃዊና ሁሉን ያካተተ ነው ባይባልም: በተጨማሪም የብአዴን አመራር አካላት አማራውን ይወክላሉ ብለን ባናምንም እርስዎ ለመመረጥዎ ሙሉ የብአዴን አባላት ድምጻቸውን መስጠታቸው ለማሸነፍዎ ትልቅ ሚና እንዳላው ጠንቅቀው ተረድተዋል ብለን እናምናለን።
ሃገራችን ከገባችበት ችግር አንጻር ዶክተር አብይ አህመድን ለጠቅላይ ሚኒስትርነት በመመረጥዎ ሁኔታውን አጢነን ከታች የሚመለከተውን የምኞትና የተግባር መግለጫ ሰጥተናል።
1. ዘረኛውና ዘራፊው የትግራይ ነጻ አውጪ ቡድን በአማራነታቸው ብቻ ያለምክንያት የታሰሩትን እና ሌሎችንም ኢትዮጵያውያን የፖለቲከኛ እስረኞችን ባስቸኳይ መፍታት
2. ያለ ሕግ አግባብና በኢሰብአዊ አያያዝ በባርነት ጥላ ስር ውለው ያሉ ወገኖቻችንን እና በማንአለብኝ እብሪት በትግራይ ግፈኞች የተወሰደውን የአማራ መሬት የሆነውን የወልቃይት ጠገዴ: ሁመራ: አላማጣና: ኮረም ወደ ቀደመ ባለቤታቸው የአማራ ይዞታ ከተገቢው ካስ ጋር እንዲመለሱ ማድረግ
3. በሃገራችንና በህዝባችን ላይ የተጣለውን የህገ አራዊት የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ማንሳት:
4. በትግራዪች የበላይነት የሚዘወረው የኢኮኖሚ ፤ ወታደራዊና ፤ የደህንነት መዋቅር ሁሉንም የሃገሪቷን ሕዝቦች ሊወክል በሚችል ደረጃ ተከልሶ እንዲዋቀር ተጨባጭ እርምጃን መውሰድ
5. ሁሉንም የተቃዋሚ ፓርቲወች የሚሳተፉበት ህዝባዊ ውይይት እና መግባባትን መፍጠር ሕዝባችን በጽናትና በቁርጠኝነት ልጆቹን እየገበረ ሲያካሂድ የቆየውን የለውጥ የሰላምና የዲሞክራሲ ትግል በጥገናዊ ለውጥና በተስፋ የፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ሳይዛናጋ የሚካሄደውን የለውጥ ሂደት በንቃት በመከታተል በትግሉ እየተቀዳጀ ያለውን ድል እንዳይነጠቅ በተጠንቀቅ ከመቼውም ግዜ በላይ ነቅቶ መጠበቅ ይኖርበታል።
አዲሱም የሃገሪቷ መሪ ሆነው የተመረጡት ዶ/ር አብይ አህመድ ከአገዛዙ በተቃራኒ ሲያራምዱ የቆዩትን ሕዝባዊነት በበለጠ አጎልብተው በተስፋና በድጋፍ ከጎናቸው የቆመውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ከሚያሳዝንና የሃገሪቱን ሰላማዊ የለውጥ ተስፋ ከሚያጨልም ድርጊት ተቆጥበው ከሕዝብ ጎን እንዲቆሙ እና በመጭው የስልጣን ጊዜዎት መሰረታዊ ለውጦችን በአፋጣኛ እንዲፈጽሙ እናሳስባለን።
ድል ለሕዝባችን!!!
እውነተኛ አማራ እንኳን ተነጋግሮ ተያይቶ መግባባት አለበት !!!
አንድ አማራ ንቅናቄ
Oneamhara1@gmail.com
www.oneamhara.org
“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።
Leave a Reply