• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የትግላችን መነሻና መዳረሻ ምንድነው?

March 31, 2018 07:41 am by Editor Leave a Comment

ብቅ ብቅ ባለ ሣር የተሳበ በሬ፡አፏን ከከፈተች መሬት ይተርፍ ይሆን!

ለምን ሕዝባዊ ትግል አስፈለገ?መስዋዕትነቱስ የሚከፈለው ምንስ ለመቀዳጀት ይሆን?

ህይወት፤ ዕውቀት፤ጊዜና ገንዘብለሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ነገሮች ናቸው። የሰው ልጅ እነዚህን መሠረታዊ ሀብቶቹን አሳልፎ መስጠት ካለበት በአንጻሩ ብልጫ ያለው ካልሆነም ተመጣጣኝ የሆነ ምላሽ መሻት ይገባዋል።

ብሶት ብዙ ጊዜ የሚፈጥረው ትግል፤ በአግባቡ ካልተደራጀና ከታች ወደ ላይ ከላይ ወደ ታች በሚንቀሳቀስ አካሄድ ካልተመራ፣ትግሉ ያልተቀነባበረና ግብታዊነት የሰፈነበት ይሆናል።በንቃት የተደራጀ ከሆነ ቀጣዩን ትግል መልክ ለማስያዝ ጠንካራ ድርሻ ይኖረዋል። በዚህ መልክ ትግሉ ከተመራ የሚከፈለው መሰዋዕትነት በዉጤት የጎመራ ይሆናል።

እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባ ዐብይ ጉዳይ  በተበታተነ መልክ ለሚደረግ ትግል የሚከፈለውመሰዋዕትነት በራሱ ብቃት የሌለው ባዶነው ማለት ሳይሆን፤ለተከታዩ ትግል አስተዋጾ እንዲኖረው በማድረግ በኩል ከፍተኛዉን ሚና መጫወት የሚገባቸዉ አለሁልህ፣መሪህ ነን ፣የሚሉት የፓለቲካ ተዋኒያን የሚጠበቅባቸዉን ማድረግ የተሳናቸዉ መሆኑንነዉ።እንደውም አንዳንዴ አመራር ሰጭ ድርጅቶች ሲታዩ ሌላውን መምራት ቀርቶ እራሳቸውን ለመምራት መሪ የሚያሻቸው ይመስላሉ።

ይህን ለማለት የገፋፋኝ ዐላማን፤ጽኑ እምነትንና ራዕይን ሰንቆ አመራር መሰጠት የሚችል ድርጅት እና የዚሁ ድርጅት አካል የሆኑት የፖለቲካ ተዋንያን ሀላፊነታቸውን ለመወጣት ያላቸዉ ብቃትና ዝግጁነት ጥያቄ ዉስጥ በመግባቱ ነዉ። ይህም ሆኖ፣

የኢትዮጵያ ህዝብ  የሚደረሰበትን እንግልት፤ ግፍና ስቃይ በተናጠልም ሆነ በቡድን እየተቃወመ በሀገሬ ባይተዋርና ሁለተኛ ዜጋ ሆኜ መታየትን አልፈቅድም በማለት ህዝባዊ መስዋዕትነት በመክፈል ላይ ነዉ።

የህዝቡን ትግል እናደራጃለን የሚሉ ድርጅቶች፤ተሞክሮአቸዉ የሚያሳየዉ አብዛኞቹ እንደ ስልት በጋራና በህብረት ትግል  (ሸንጎ፤ ጥምረት፤ የሲያትሉ ትብብር….) የሚያራምዱትም፣ ሆነ በራሳቸዉ የቆሙት ፣ህብረብሔራዊ አጀንዳ ቀርፀዉ ተስማሚ በሆነ ርዮተዓለም ዙርያ ተሰባስበዉ ሲጓዙ አይታይም። እነዚህ በተቃዋሚ ጎራ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች በምን በምን የጋራ መርሃ ግብር አላማናአቋም ነዉ የተሳሰራችሁ? የሚለዉን ጥያቄ ሳያድበሰብሱ መመለስ ይገባቸዋል ።

የኢሕአዴግን ህገ መንስት የተቀበሉና ያልተቀበሉ፣የዘርና ጎሳ ፓለቲካ የተቀበሉና ያልተቀበሉ፣ኢትዮጵያነባር ሀገር ናት፤ የሚሉና እንዲሁም የመቶ ሃምሳ አመት ዕድሜ ዉጤት ናት የሚሉት ፤ይህንን ቅይጥና ዥንጉርጉር አቋማቸው በወንፊት ሳይበጠር በጋራ ሊጓዙ ያበቃቸዉ ሚስጢር ምድር ነዉ?ይህ ጥበብ ወይስ ታክቲክ ተብሎ ሊወሰድ ይችል ይሆን?ሚስጥሩ ሲገለጥ “ልከክልህ እከክልኝ” ወይም አንዳንዶች እንደሚሉት መሞዳሞድ ከሆነስ?

የበግ ለምድ ከለበሱት ዉስጥቓሚዉ እረኛ እዉነተኞችን መለየት ከተሳነዉ የእረኛዉ መፍዘዝ ወይስ ሁሉም አስመሳይ ለምድ የለበሱ በመሆናቸዉ ነዉ?ስልቻም ቀልቀሎ…!ይባል የለታዲያ።

ይህ የመሪ ድርጀት እጦት ሳይበግረዉህዝባችን በየአካባቢው ካለፉት አመታት ጀመሮ እየደረሰበት ያለውን ጥቃት ለመከላከል  በቄሮዎች በፋኖዎችናበጎበዝ አለቆች እየተመራ ከአደባባይ ሰልፍ እስከ ሽምቅ ውጊያ ድረስ ለመዝለቅ ተገዷል። አንዳንዶች ይህንን ሐቅ ከመካድም አልፈዉየሕዝባዊ አመፁን ውጤት እነሱ የፈጠሩት አስመሰለው ከማቅረብ አልቦዘኑም። ከታሪክና ከህዝብ ተሰውሮ መኖር አይቻልምና ህዝባችን በትግሉ ማዕበል ውስጥ በመገኘቱ እውነቱን  በግልጽ ያውቀዋል።  እንዚህ ዋሾዎች ግን ያደቆነ ሠይጣን ሳያቀስ አይለቅም እንዲሉ  የድሉ ቀን ሲመጣ ቆዳቸውን ለውጠው፤ መልካቸውን ቀይረው መምጣታቸው አይቀሬ ነውና፤ ዐመተ ፍዳቸውን እና ዐመተኩነኔያቸው በየፈርጁ ሊከተብ ይገባል። የክህደት ታዋቂነት ከሃዲ ያስብል እንደሆነ እንጂ ሀቀኛ የሚያሰኝ አይደለም።

ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ የፖለቲካ ትግላችን አቅጣጫ ነው።

ግባችንደሞክራሲያዊትኢትዮጵያን መገንባት እንደሆነ ብዙዎቻችን በጽንሰ ሐሳቡ ብንግባባም፤ ይህንን ግብ እዉን ለማድረግ ምን ዐይነት አካሄድ መጛዝ አለብን? የሚለው ጥያቄ ግን ትኩረት አግኝቶ የተመለሰ አይመሰልም።

ይህ ጉዳይ ምላሽ ያለማግኘቱ “በሬ ሆይ በሬ ሆይ ሳሩን አየህና ገደሉን ሣታይ” እንዲሉ የሚፈጠሩ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች እያማለሉን የዘነጋነው ወይንም ሆን ብለን ያለፍነው ወይንም ሸፋፍነን በማለፍ የፍርድ ቀን ለመጠበቅ በማሰብከሆነ ውጤቱ የከፋ ይሆናል።

የአገራችንና የሕዝባችን ዋናችግርና አደጋ ኢሕአዴግ የሚከተለው የፖለቲካ መሰመርና ፖሊሲ ነው። ይህ ጎሳን፤ ቋንቋንና ዘርን መሰረት ያደረገና ሀገሪቱንም በክልል የሸነሸነ አገዛዝ ለችግሮቻችን ሁሉ መሰረታዊ ምክንያት ሆኗል። ሕገ መንግስቱም የዚሁ እኩይ የአገዛዝ ውጤት በመሆኑ፤ ከመቅድሙ አንስቶ ‘ብሄር ብሄረሰብ ህዝቦች …” በሚል አባዜ ተጠምዶ ሕዝባችን ከኢትዮጵያዊነት ይልቅ ወደ ጎሰኝነት  እንዲያመዝን ቢያስገድድም ሙከራው ዘለቄታ አልኖረውም። ውሸትና ንጋት እያደር ይገለጥ የለ!

የነገይቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት የዛሬው ትግላችን የነባሯ እትዮጵያ ታሪክ በትውልድ ቅብብሎሽ የዳበረ እሴትና አብሮነትን ማዕከል ያደረገ መሆን አለበት። በኢትዮጵያዊነት የሚገለፀዉን ሕብረ-ብሄራዊነት አጀንዳ ለማስፈፀም ካልተባበረና ካልተነሳ በስተቀር የመሰዋዕትነታችን ውጤት አሁንም ፍሬ አልባ ከመሆን አያልፍም። ይህን ሐቅ መቀበል ሊከብድ ይችላል። መድሐኒትስ ይመር የለ! ስለዚህ መፍትሄው እውነትን ተናገሮ የመሸበት ማደር እንዲሉ ለዕውነት መሰዋዕትነት መክፈል ነው።

ዛሬ በምድር ላይ ያለው እንቅስቃሴ ቤተመንግስትን ለመንጠቅ በቀጥታ ያነጣጠረ መሆኑ መልካም  ቢሆንም፤ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያኖች ሕልም ግን በ4 ኪሎው ቤተ መንግስት የሚረካ ሣይሆን የዕርካታ ምንጫችን መሠረት “አንድ ሕዝብ ኢትዮጵያውያን አንድ አገር ኢትዮጵያ “ሁላችንም የአንድ አገር ዜጋ በሚል የተግባባና የተቀናጀ ትግል ዙሪያ ፀንቶ መቆም ነው። ከዚህኛው ምንጭ ዳግም የነጻነት ጥማት አይገጥመንምና።

አማራው ለኦሮሞው፤ ኦሮሞው ለትግራዩ፤ ደቡብ ለሰሜን፤ ምእራቡ ለምስራቁ ወዘተ…፤ ወንድማማች ነን መባባሉ ብቻ ዋስትና አይሆነንም።

ወያኔ ተወገደም አልተወገደም ከእንግዲህ “እኛን (ኦሮሚያን) ሊገዛ አይችልም” የሚለዉ አባባል በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የተመሰረተችዉን ኢትዮጵያና ሕዝቧን ይገልፃልን?? ምሳሌ (ከኔ)–አንድ ኢትዮጵያዊነት ፍልስፍናን መሠረት ያደረገ ግዙፍ ተራራ ከመሀል ስፍራ ላይ ቆሟል። በሌላኞው ጠርዝ ደግሞ በጀዋመ (የፈጠራስም)ና ጓደኞቹ በዘር በቋንቋ ማንነትና በክልል አስተዳደር ላይ የተገነባ አስተሳሰብ (ፍልስፍና) አለ። የእነ ጀዋመ አስተሳሰብ ሳይሆን፣ ግዙፍ ተራራ ከሆነ ወደነ ጀዋመ የመጣ ይህ ታክቲክ ወይስ ኢትዮጵያዊነትን ለድርድር ማቅረብ?

እዚህ ላይ ጆሮ ያለዉ ይስማ፣ ግን በአእምሮዉ ያስተዉል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢሕዴግና በዘረኞች ተክዷል።ይህ ሀቅ እንጂ ወዳጅነትን ለማብዛት ተብሎ የሚደሰኰር ፕሮፓጋንዳ አይደለም የታክቲክ ዉጤትም አይደለም።

ይህን ስንረዳ ብቻ ነዉ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመወዳጀት የዘይት ሀብት ላይ ተደግፎ ከመታገል ይልቅ የተጎሳቀለዉንና ሳያጣ ያጣ በሆነዉ ኩሩ ሕዝብ ጉልበት፣ላብና ደም ስንተማመን ነዉ በጋራ ወደፊት መትመም የምንችለዉ።

ማጠቃለያ–

መስዋዕትነታችን ዋጋ እንዲኖረውና ትግላችን በነባሯ ኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የተዋቀረ፤ ሕብረ ብሔራዊ አጀንዳ ያነገበ፤ ሉዐላዊነቷ የተከበረ፤ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን  ማቀዳጀት የሚችል የሀሣብ ፣የርዕዮት-ዐለም ፤የተግባር አቅም ያለዉሊሆንይገባል። አካሄዱም ከብሄር ተኮር (ጎሰኛነት) አደረጃጀትና ርዕዮት-ዓለም የፀዳ መሆን አለበት።

ጎሰኝነት የቱን ያህል ህዝቡን ለማነሳሳት የጠቀመ ቢመስልም ውጤቱ ግን አንድነት ሣይሆን ልዩነት ነው። የዘር ማንነት የክልል ፖለቲካ አደረጃጀትን ማዕከል ባደረግ ትግል የቤተመንግስትን ሥልጣን ለመንጠቅ ይቻል ይሆናል፤ግን ፋይዳው ለአንድነት ለዘላቂ ዕድገትና ብልጽግና ዳግም ነፃነትን እንዳንጠማ የተከፈለውን መስዋዕትነት አይከፍልምና እያስተዋልን መጓዝ ይበጀናል። አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ የሚለው አገላለጽ እንዳይመሰክርብን እንጠንቀቅ!!!

ከእዉነቱ ፈረደ

ኢትዮጵያ ለዘለዐለም ትኑር!

አሁንም ለወደፊትምኢትዮጵያዊነት ያሸንፋል!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule