• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሲመቱት ይጠብቃል

March 22, 2018 07:37 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የሚገባውን እንደዜጋ በነፃነት የመኖር መብት ለመጎናፀፍ ያደረገው ጥረት ሁሉ በአምባገነኖቹ እየተዳጠ አሁን ላለበት ዝቅተኛ ኑሮና ለከት ያጣ ግፍ ተዳርጓል። የግፉ ፅዋ ሞልቶ መፍሰስ በመጀመሩም ከአስከፊው ስርዓት ጨርሶ ለመላቀቅ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት እልህ አስጨራሹን ትግል ተያይዞታል። የአሁኑ ትግል ካለፉት በብዙ መልኩ የተለየ ነው። ህዝባዊ አመፁ ሰከን ያለና ህዝቡን ከዳር ዳር ያሳተፈ ለአምባገነኖቹ ጨርሶ ያልተመቸ፣ ግፈኛውን አገዛዝ ቀስ በቀስ እየደማ እንዲሞት የሚያደርግ ነው።

ፈረንጆች ሚስማር ሲመቱት እያደር ይጠብቃል እንዲሉ፤ ባለመዶሻው ወያኔ የህብረተሰቡ አንጓ የሆኑትን ራስ ራሳቸውን መታሁ ሲል የበለጠ ማህበራዊ ትስስሩንና የትግሉን ሂደት ሲያጠብቁት እናያለን።

አማራውን በጠላትነት በፕሮግራሙ ነድፎ ከሌላው ህብረተሰብ ጋር በማቃቃር ግፍ ሲፍፅምና ሲያስፈፅም፣ ይህ ለምን ይሆናል ያሉትን ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን በግፍ ቢገድልም ዛሬ አማራው ይህንን ግፍ ተቀምጦ የማያይ፣ አስፈታነው ሲሉት ነጥቆ የሚታጠቅ፣ በገደሉት ቁጥር የሚገድል፣ አጠፋነው ባሉ ቁጥር ጉሮሮአቸው ላይ የሚሰነቀር አጥንት ሆንኗል።

ኦሮሞውን ለስልጣን አጃቢነት ለመጠቀም ኦነግን ከተገለገሉበት በኋላ የወረወሩ ወያኔዎች መሬቱንና ሃብቱን በመቀራመት ልጆቹን በመግደልና በማሰር የከመሩበትን እዳ ዛሬ እነሱ እንዲከፍሉት እያስገደዳቸው ነው። ኦሮሞው ሺዎች ሞተውበት፣ ሚሊዮን ተፈናቅሎና ተሰድዶ ቄሮና ልሂቃኑ በሰከነ ሁኔታ የስርዓቱን ስስ ብልት እየመታ እንዳይነሳ ከማደባየቱም በላይ በወያኔ ሲቀነቀን የነበረው “አገር ሊያፈርሱ ነው” የሚል ቅጥፈት ከንቱ ሆኖ የኢትዮጵያ ባለቤትነቱን እያሳያቸው ነው።

ከህዝብ በተዘረፈ ገንዘብና በተባባሪዎች ደባ አንዳርጋቸው ፅጌ ታፍኖ ቢታሰርም ትግሉን ሺ ጊዜ አሳደገው፣ ብዙ ሺ አንዳርጋቸዎችን አፈራ፣ አንዳርጋቸው ነፃነት ለሚሹ የፅናት ተምሳሌት የሆነውን ያህል ለወያኔ መንፈሱ እንቅልፍ የሚነሳ ቅዠት ነው።

ፖለቲከኞች የዴሞክራሲ ስርዓትን ለማስፈን ህዝባቸው መሃል ስለተንቀሳቀሱ ብቻ ተገድለዋል፣ ታስረዋል፣ ተሰድደዋል። ታስረው የወጡት አንዱዓለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ፣ መረራ ጉዲና፣ አበበ ቀስቶ፣ ሃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ማሙሸት አማረ፣ ስማቸውን ዘርዝረን የማንጨርሳቸው ኢትዮጵያውያን አስረን፣ ሞራላቸውን ገድለን ለቀቅናቸው ሲሉ የበለጠ የበሰሉ፣ ለየነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ የሚሆኑ መሪዎች ሆነው ወጡ።

በነፃ ሚድያው ጎራ የህዝቡ ድምፅ የሆኑትን ጋዜጠኞች ማሰርና ማሰደድ ለወያኔ ምንም እንዳልበጀው እስክንድር፣ ተመስገን፣ ውቭሸት፣ወዘተ በህዝባቸውና በዓለም ያገኙትን ክብርና የነሱን ፅናት ለተመለከተ፣ ርዕዮት፣ ሲሳይ፣ መሳይና ሌሎችም በርካታ በዓለም የተሰራጩ ጋዜጠኞች በሙያቸው ህዝባቸውን በማገልገል ለለውጡ የሚያደርጉት አስተዋፆ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልሄደ አሳይቷል።

በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ስርዓቱ አመራሮቹ ላይ ወኪሎቹን ቢያስቀምጥም የሙስሊሙ ያላሳለሰ ትግል፣ የመሪዎቹ ፅናት፣ በኦርቶዶክስ ገዳማትና መነኮሳት የሚፈፀመው ግፍ ስርዓቱን ጨርሶ ከምዕመኑ የሚነጥል፣ ህዝባዊ ትግሉንም የሚያጎለብት እየሆነ ነው የሄደው።

ህወሃት በአገልጋይነት ያቋቋማቸው ድርጅቶች እንኳ ከሚሞት ስርዓት ጋር ላለመሞት ብለው ብቻ ሳይሆን ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚበጀው ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት መሆኑን በማረጋገጥ ክውስጡ ሰንገው ይዘውታል። በምርኮኞችና የኢትዮጵያን ህዝብ እስከአጥንቱ ግጠው በበሉ አደግዳጊዎቹ ሊያፍናቸው ቢሞክር ህዝባቸው ከጎናቸው ከመሆኑም በላይ እነሱ የታገሉለትን ዓላማ ዳር ሳያደርስ እንደማያርፍ በተግባር እያሳየ ነው።

ወያኔ እየዛለ በሄደ ክንዱ መታሁ ባለ ቁጥር እየጠበቀ የሄደው ህዝባዊ ትግል በአምባገነኖች የሬሳ ሳጥን ላይ የመጨረሻዋን ቢስማር ለመምታት ተቃርቧል። ከዚህ ጋር መታሰብ ያለበት ቀጣዩ እርምጃ የተገኙ ድሎች እንዳይነጠቁ ህዝቡ በዘላቂነት የሚጠብቅበትን መንገድ መነጋገርና ስርዓቱን ከአሁኑ ማበጀት መጀመር ላይ ማተኮር ያስፈልጋል። ህዝቡ የማይመቸውን ስርዓት ማፍረስ ላይ ያተኮረውን ያህል የሚፈልገውን አዲስ ስርዓት መገንባት የሚጀመረው ከአሁኑ በመሆኑ በሁሉም መስክ ህዝባዊ መሰረቶችን መጣል ላይም ሃሳብ መቀያየርና የተግባር እንቅስቃሴም መጀመር ያለበት ወቅት ላይ ነን።

ከአንተነህ መርዕድ (amerid2000@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule