• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሲመቱት ይጠብቃል

March 22, 2018 07:37 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የሚገባውን እንደዜጋ በነፃነት የመኖር መብት ለመጎናፀፍ ያደረገው ጥረት ሁሉ በአምባገነኖቹ እየተዳጠ አሁን ላለበት ዝቅተኛ ኑሮና ለከት ያጣ ግፍ ተዳርጓል። የግፉ ፅዋ ሞልቶ መፍሰስ በመጀመሩም ከአስከፊው ስርዓት ጨርሶ ለመላቀቅ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት እልህ አስጨራሹን ትግል ተያይዞታል። የአሁኑ ትግል ካለፉት በብዙ መልኩ የተለየ ነው። ህዝባዊ አመፁ ሰከን ያለና ህዝቡን ከዳር ዳር ያሳተፈ ለአምባገነኖቹ ጨርሶ ያልተመቸ፣ ግፈኛውን አገዛዝ ቀስ በቀስ እየደማ እንዲሞት የሚያደርግ ነው።

ፈረንጆች ሚስማር ሲመቱት እያደር ይጠብቃል እንዲሉ፤ ባለመዶሻው ወያኔ የህብረተሰቡ አንጓ የሆኑትን ራስ ራሳቸውን መታሁ ሲል የበለጠ ማህበራዊ ትስስሩንና የትግሉን ሂደት ሲያጠብቁት እናያለን።

አማራውን በጠላትነት በፕሮግራሙ ነድፎ ከሌላው ህብረተሰብ ጋር በማቃቃር ግፍ ሲፍፅምና ሲያስፈፅም፣ ይህ ለምን ይሆናል ያሉትን ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን በግፍ ቢገድልም ዛሬ አማራው ይህንን ግፍ ተቀምጦ የማያይ፣ አስፈታነው ሲሉት ነጥቆ የሚታጠቅ፣ በገደሉት ቁጥር የሚገድል፣ አጠፋነው ባሉ ቁጥር ጉሮሮአቸው ላይ የሚሰነቀር አጥንት ሆንኗል።

ኦሮሞውን ለስልጣን አጃቢነት ለመጠቀም ኦነግን ከተገለገሉበት በኋላ የወረወሩ ወያኔዎች መሬቱንና ሃብቱን በመቀራመት ልጆቹን በመግደልና በማሰር የከመሩበትን እዳ ዛሬ እነሱ እንዲከፍሉት እያስገደዳቸው ነው። ኦሮሞው ሺዎች ሞተውበት፣ ሚሊዮን ተፈናቅሎና ተሰድዶ ቄሮና ልሂቃኑ በሰከነ ሁኔታ የስርዓቱን ስስ ብልት እየመታ እንዳይነሳ ከማደባየቱም በላይ በወያኔ ሲቀነቀን የነበረው “አገር ሊያፈርሱ ነው” የሚል ቅጥፈት ከንቱ ሆኖ የኢትዮጵያ ባለቤትነቱን እያሳያቸው ነው።

ከህዝብ በተዘረፈ ገንዘብና በተባባሪዎች ደባ አንዳርጋቸው ፅጌ ታፍኖ ቢታሰርም ትግሉን ሺ ጊዜ አሳደገው፣ ብዙ ሺ አንዳርጋቸዎችን አፈራ፣ አንዳርጋቸው ነፃነት ለሚሹ የፅናት ተምሳሌት የሆነውን ያህል ለወያኔ መንፈሱ እንቅልፍ የሚነሳ ቅዠት ነው።

ፖለቲከኞች የዴሞክራሲ ስርዓትን ለማስፈን ህዝባቸው መሃል ስለተንቀሳቀሱ ብቻ ተገድለዋል፣ ታስረዋል፣ ተሰድደዋል። ታስረው የወጡት አንዱዓለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ፣ መረራ ጉዲና፣ አበበ ቀስቶ፣ ሃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ማሙሸት አማረ፣ ስማቸውን ዘርዝረን የማንጨርሳቸው ኢትዮጵያውያን አስረን፣ ሞራላቸውን ገድለን ለቀቅናቸው ሲሉ የበለጠ የበሰሉ፣ ለየነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ የሚሆኑ መሪዎች ሆነው ወጡ።

በነፃ ሚድያው ጎራ የህዝቡ ድምፅ የሆኑትን ጋዜጠኞች ማሰርና ማሰደድ ለወያኔ ምንም እንዳልበጀው እስክንድር፣ ተመስገን፣ ውቭሸት፣ወዘተ በህዝባቸውና በዓለም ያገኙትን ክብርና የነሱን ፅናት ለተመለከተ፣ ርዕዮት፣ ሲሳይ፣ መሳይና ሌሎችም በርካታ በዓለም የተሰራጩ ጋዜጠኞች በሙያቸው ህዝባቸውን በማገልገል ለለውጡ የሚያደርጉት አስተዋፆ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልሄደ አሳይቷል።

በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ስርዓቱ አመራሮቹ ላይ ወኪሎቹን ቢያስቀምጥም የሙስሊሙ ያላሳለሰ ትግል፣ የመሪዎቹ ፅናት፣ በኦርቶዶክስ ገዳማትና መነኮሳት የሚፈፀመው ግፍ ስርዓቱን ጨርሶ ከምዕመኑ የሚነጥል፣ ህዝባዊ ትግሉንም የሚያጎለብት እየሆነ ነው የሄደው።

ህወሃት በአገልጋይነት ያቋቋማቸው ድርጅቶች እንኳ ከሚሞት ስርዓት ጋር ላለመሞት ብለው ብቻ ሳይሆን ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚበጀው ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት መሆኑን በማረጋገጥ ክውስጡ ሰንገው ይዘውታል። በምርኮኞችና የኢትዮጵያን ህዝብ እስከአጥንቱ ግጠው በበሉ አደግዳጊዎቹ ሊያፍናቸው ቢሞክር ህዝባቸው ከጎናቸው ከመሆኑም በላይ እነሱ የታገሉለትን ዓላማ ዳር ሳያደርስ እንደማያርፍ በተግባር እያሳየ ነው።

ወያኔ እየዛለ በሄደ ክንዱ መታሁ ባለ ቁጥር እየጠበቀ የሄደው ህዝባዊ ትግል በአምባገነኖች የሬሳ ሳጥን ላይ የመጨረሻዋን ቢስማር ለመምታት ተቃርቧል። ከዚህ ጋር መታሰብ ያለበት ቀጣዩ እርምጃ የተገኙ ድሎች እንዳይነጠቁ ህዝቡ በዘላቂነት የሚጠብቅበትን መንገድ መነጋገርና ስርዓቱን ከአሁኑ ማበጀት መጀመር ላይ ማተኮር ያስፈልጋል። ህዝቡ የማይመቸውን ስርዓት ማፍረስ ላይ ያተኮረውን ያህል የሚፈልገውን አዲስ ስርዓት መገንባት የሚጀመረው ከአሁኑ በመሆኑ በሁሉም መስክ ህዝባዊ መሰረቶችን መጣል ላይም ሃሳብ መቀያየርና የተግባር እንቅስቃሴም መጀመር ያለበት ወቅት ላይ ነን።

ከአንተነህ መርዕድ (amerid2000@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule