• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሲመቱት ይጠብቃል

March 22, 2018 07:37 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የሚገባውን እንደዜጋ በነፃነት የመኖር መብት ለመጎናፀፍ ያደረገው ጥረት ሁሉ በአምባገነኖቹ እየተዳጠ አሁን ላለበት ዝቅተኛ ኑሮና ለከት ያጣ ግፍ ተዳርጓል። የግፉ ፅዋ ሞልቶ መፍሰስ በመጀመሩም ከአስከፊው ስርዓት ጨርሶ ለመላቀቅ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት እልህ አስጨራሹን ትግል ተያይዞታል። የአሁኑ ትግል ካለፉት በብዙ መልኩ የተለየ ነው። ህዝባዊ አመፁ ሰከን ያለና ህዝቡን ከዳር ዳር ያሳተፈ ለአምባገነኖቹ ጨርሶ ያልተመቸ፣ ግፈኛውን አገዛዝ ቀስ በቀስ እየደማ እንዲሞት የሚያደርግ ነው።

ፈረንጆች ሚስማር ሲመቱት እያደር ይጠብቃል እንዲሉ፤ ባለመዶሻው ወያኔ የህብረተሰቡ አንጓ የሆኑትን ራስ ራሳቸውን መታሁ ሲል የበለጠ ማህበራዊ ትስስሩንና የትግሉን ሂደት ሲያጠብቁት እናያለን።

አማራውን በጠላትነት በፕሮግራሙ ነድፎ ከሌላው ህብረተሰብ ጋር በማቃቃር ግፍ ሲፍፅምና ሲያስፈፅም፣ ይህ ለምን ይሆናል ያሉትን ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን በግፍ ቢገድልም ዛሬ አማራው ይህንን ግፍ ተቀምጦ የማያይ፣ አስፈታነው ሲሉት ነጥቆ የሚታጠቅ፣ በገደሉት ቁጥር የሚገድል፣ አጠፋነው ባሉ ቁጥር ጉሮሮአቸው ላይ የሚሰነቀር አጥንት ሆንኗል።

ኦሮሞውን ለስልጣን አጃቢነት ለመጠቀም ኦነግን ከተገለገሉበት በኋላ የወረወሩ ወያኔዎች መሬቱንና ሃብቱን በመቀራመት ልጆቹን በመግደልና በማሰር የከመሩበትን እዳ ዛሬ እነሱ እንዲከፍሉት እያስገደዳቸው ነው። ኦሮሞው ሺዎች ሞተውበት፣ ሚሊዮን ተፈናቅሎና ተሰድዶ ቄሮና ልሂቃኑ በሰከነ ሁኔታ የስርዓቱን ስስ ብልት እየመታ እንዳይነሳ ከማደባየቱም በላይ በወያኔ ሲቀነቀን የነበረው “አገር ሊያፈርሱ ነው” የሚል ቅጥፈት ከንቱ ሆኖ የኢትዮጵያ ባለቤትነቱን እያሳያቸው ነው።

ከህዝብ በተዘረፈ ገንዘብና በተባባሪዎች ደባ አንዳርጋቸው ፅጌ ታፍኖ ቢታሰርም ትግሉን ሺ ጊዜ አሳደገው፣ ብዙ ሺ አንዳርጋቸዎችን አፈራ፣ አንዳርጋቸው ነፃነት ለሚሹ የፅናት ተምሳሌት የሆነውን ያህል ለወያኔ መንፈሱ እንቅልፍ የሚነሳ ቅዠት ነው።

ፖለቲከኞች የዴሞክራሲ ስርዓትን ለማስፈን ህዝባቸው መሃል ስለተንቀሳቀሱ ብቻ ተገድለዋል፣ ታስረዋል፣ ተሰድደዋል። ታስረው የወጡት አንዱዓለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ፣ መረራ ጉዲና፣ አበበ ቀስቶ፣ ሃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ማሙሸት አማረ፣ ስማቸውን ዘርዝረን የማንጨርሳቸው ኢትዮጵያውያን አስረን፣ ሞራላቸውን ገድለን ለቀቅናቸው ሲሉ የበለጠ የበሰሉ፣ ለየነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ የሚሆኑ መሪዎች ሆነው ወጡ።

በነፃ ሚድያው ጎራ የህዝቡ ድምፅ የሆኑትን ጋዜጠኞች ማሰርና ማሰደድ ለወያኔ ምንም እንዳልበጀው እስክንድር፣ ተመስገን፣ ውቭሸት፣ወዘተ በህዝባቸውና በዓለም ያገኙትን ክብርና የነሱን ፅናት ለተመለከተ፣ ርዕዮት፣ ሲሳይ፣ መሳይና ሌሎችም በርካታ በዓለም የተሰራጩ ጋዜጠኞች በሙያቸው ህዝባቸውን በማገልገል ለለውጡ የሚያደርጉት አስተዋፆ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልሄደ አሳይቷል።

በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ስርዓቱ አመራሮቹ ላይ ወኪሎቹን ቢያስቀምጥም የሙስሊሙ ያላሳለሰ ትግል፣ የመሪዎቹ ፅናት፣ በኦርቶዶክስ ገዳማትና መነኮሳት የሚፈፀመው ግፍ ስርዓቱን ጨርሶ ከምዕመኑ የሚነጥል፣ ህዝባዊ ትግሉንም የሚያጎለብት እየሆነ ነው የሄደው።

ህወሃት በአገልጋይነት ያቋቋማቸው ድርጅቶች እንኳ ከሚሞት ስርዓት ጋር ላለመሞት ብለው ብቻ ሳይሆን ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚበጀው ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት መሆኑን በማረጋገጥ ክውስጡ ሰንገው ይዘውታል። በምርኮኞችና የኢትዮጵያን ህዝብ እስከአጥንቱ ግጠው በበሉ አደግዳጊዎቹ ሊያፍናቸው ቢሞክር ህዝባቸው ከጎናቸው ከመሆኑም በላይ እነሱ የታገሉለትን ዓላማ ዳር ሳያደርስ እንደማያርፍ በተግባር እያሳየ ነው።

ወያኔ እየዛለ በሄደ ክንዱ መታሁ ባለ ቁጥር እየጠበቀ የሄደው ህዝባዊ ትግል በአምባገነኖች የሬሳ ሳጥን ላይ የመጨረሻዋን ቢስማር ለመምታት ተቃርቧል። ከዚህ ጋር መታሰብ ያለበት ቀጣዩ እርምጃ የተገኙ ድሎች እንዳይነጠቁ ህዝቡ በዘላቂነት የሚጠብቅበትን መንገድ መነጋገርና ስርዓቱን ከአሁኑ ማበጀት መጀመር ላይ ማተኮር ያስፈልጋል። ህዝቡ የማይመቸውን ስርዓት ማፍረስ ላይ ያተኮረውን ያህል የሚፈልገውን አዲስ ስርዓት መገንባት የሚጀመረው ከአሁኑ በመሆኑ በሁሉም መስክ ህዝባዊ መሰረቶችን መጣል ላይም ሃሳብ መቀያየርና የተግባር እንቅስቃሴም መጀመር ያለበት ወቅት ላይ ነን።

ከአንተነህ መርዕድ (amerid2000@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule