• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሲመቱት ይጠብቃል

March 22, 2018 07:37 am by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ ለበርካታ ዓመታት የሚገባውን እንደዜጋ በነፃነት የመኖር መብት ለመጎናፀፍ ያደረገው ጥረት ሁሉ በአምባገነኖቹ እየተዳጠ አሁን ላለበት ዝቅተኛ ኑሮና ለከት ያጣ ግፍ ተዳርጓል። የግፉ ፅዋ ሞልቶ መፍሰስ በመጀመሩም ከአስከፊው ስርዓት ጨርሶ ለመላቀቅ በተለይ ባለፉት ሶስት ዓመታት እልህ አስጨራሹን ትግል ተያይዞታል። የአሁኑ ትግል ካለፉት በብዙ መልኩ የተለየ ነው። ህዝባዊ አመፁ ሰከን ያለና ህዝቡን ከዳር ዳር ያሳተፈ ለአምባገነኖቹ ጨርሶ ያልተመቸ፣ ግፈኛውን አገዛዝ ቀስ በቀስ እየደማ እንዲሞት የሚያደርግ ነው።

ፈረንጆች ሚስማር ሲመቱት እያደር ይጠብቃል እንዲሉ፤ ባለመዶሻው ወያኔ የህብረተሰቡ አንጓ የሆኑትን ራስ ራሳቸውን መታሁ ሲል የበለጠ ማህበራዊ ትስስሩንና የትግሉን ሂደት ሲያጠብቁት እናያለን።

አማራውን በጠላትነት በፕሮግራሙ ነድፎ ከሌላው ህብረተሰብ ጋር በማቃቃር ግፍ ሲፍፅምና ሲያስፈፅም፣ ይህ ለምን ይሆናል ያሉትን ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን በግፍ ቢገድልም ዛሬ አማራው ይህንን ግፍ ተቀምጦ የማያይ፣ አስፈታነው ሲሉት ነጥቆ የሚታጠቅ፣ በገደሉት ቁጥር የሚገድል፣ አጠፋነው ባሉ ቁጥር ጉሮሮአቸው ላይ የሚሰነቀር አጥንት ሆንኗል።

ኦሮሞውን ለስልጣን አጃቢነት ለመጠቀም ኦነግን ከተገለገሉበት በኋላ የወረወሩ ወያኔዎች መሬቱንና ሃብቱን በመቀራመት ልጆቹን በመግደልና በማሰር የከመሩበትን እዳ ዛሬ እነሱ እንዲከፍሉት እያስገደዳቸው ነው። ኦሮሞው ሺዎች ሞተውበት፣ ሚሊዮን ተፈናቅሎና ተሰድዶ ቄሮና ልሂቃኑ በሰከነ ሁኔታ የስርዓቱን ስስ ብልት እየመታ እንዳይነሳ ከማደባየቱም በላይ በወያኔ ሲቀነቀን የነበረው “አገር ሊያፈርሱ ነው” የሚል ቅጥፈት ከንቱ ሆኖ የኢትዮጵያ ባለቤትነቱን እያሳያቸው ነው።

ከህዝብ በተዘረፈ ገንዘብና በተባባሪዎች ደባ አንዳርጋቸው ፅጌ ታፍኖ ቢታሰርም ትግሉን ሺ ጊዜ አሳደገው፣ ብዙ ሺ አንዳርጋቸዎችን አፈራ፣ አንዳርጋቸው ነፃነት ለሚሹ የፅናት ተምሳሌት የሆነውን ያህል ለወያኔ መንፈሱ እንቅልፍ የሚነሳ ቅዠት ነው።

ፖለቲከኞች የዴሞክራሲ ስርዓትን ለማስፈን ህዝባቸው መሃል ስለተንቀሳቀሱ ብቻ ተገድለዋል፣ ታስረዋል፣ ተሰድደዋል። ታስረው የወጡት አንዱዓለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ፣ መረራ ጉዲና፣ አበበ ቀስቶ፣ ሃብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ማሙሸት አማረ፣ ስማቸውን ዘርዝረን የማንጨርሳቸው ኢትዮጵያውያን አስረን፣ ሞራላቸውን ገድለን ለቀቅናቸው ሲሉ የበለጠ የበሰሉ፣ ለየነገዋ ኢትዮጵያ ተስፋ የሚሆኑ መሪዎች ሆነው ወጡ።

በነፃ ሚድያው ጎራ የህዝቡ ድምፅ የሆኑትን ጋዜጠኞች ማሰርና ማሰደድ ለወያኔ ምንም እንዳልበጀው እስክንድር፣ ተመስገን፣ ውቭሸት፣ወዘተ በህዝባቸውና በዓለም ያገኙትን ክብርና የነሱን ፅናት ለተመለከተ፣ ርዕዮት፣ ሲሳይ፣ መሳይና ሌሎችም በርካታ በዓለም የተሰራጩ ጋዜጠኞች በሙያቸው ህዝባቸውን በማገልገል ለለውጡ የሚያደርጉት አስተዋፆ እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ እንዳልሄደ አሳይቷል።

በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ስርዓቱ አመራሮቹ ላይ ወኪሎቹን ቢያስቀምጥም የሙስሊሙ ያላሳለሰ ትግል፣ የመሪዎቹ ፅናት፣ በኦርቶዶክስ ገዳማትና መነኮሳት የሚፈፀመው ግፍ ስርዓቱን ጨርሶ ከምዕመኑ የሚነጥል፣ ህዝባዊ ትግሉንም የሚያጎለብት እየሆነ ነው የሄደው።

ህወሃት በአገልጋይነት ያቋቋማቸው ድርጅቶች እንኳ ከሚሞት ስርዓት ጋር ላለመሞት ብለው ብቻ ሳይሆን ለአገራቸውና ለህዝባቸው የሚበጀው ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን መገንባት መሆኑን በማረጋገጥ ክውስጡ ሰንገው ይዘውታል። በምርኮኞችና የኢትዮጵያን ህዝብ እስከአጥንቱ ግጠው በበሉ አደግዳጊዎቹ ሊያፍናቸው ቢሞክር ህዝባቸው ከጎናቸው ከመሆኑም በላይ እነሱ የታገሉለትን ዓላማ ዳር ሳያደርስ እንደማያርፍ በተግባር እያሳየ ነው።

ወያኔ እየዛለ በሄደ ክንዱ መታሁ ባለ ቁጥር እየጠበቀ የሄደው ህዝባዊ ትግል በአምባገነኖች የሬሳ ሳጥን ላይ የመጨረሻዋን ቢስማር ለመምታት ተቃርቧል። ከዚህ ጋር መታሰብ ያለበት ቀጣዩ እርምጃ የተገኙ ድሎች እንዳይነጠቁ ህዝቡ በዘላቂነት የሚጠብቅበትን መንገድ መነጋገርና ስርዓቱን ከአሁኑ ማበጀት መጀመር ላይ ማተኮር ያስፈልጋል። ህዝቡ የማይመቸውን ስርዓት ማፍረስ ላይ ያተኮረውን ያህል የሚፈልገውን አዲስ ስርዓት መገንባት የሚጀመረው ከአሁኑ በመሆኑ በሁሉም መስክ ህዝባዊ መሰረቶችን መጣል ላይም ሃሳብ መቀያየርና የተግባር እንቅስቃሴም መጀመር ያለበት ወቅት ላይ ነን።

ከአንተነህ መርዕድ (amerid2000@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule