• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘብ ቆመናል ክቡር የኢትዮጵያ ልጅ ዶ/ር አብይ አህመድ

April 1, 2018 06:39 am by Editor 1 Comment

ሁላችንም ካለንበት አጣብቂኝ ውስጥ መውጫ መንገድ አጥተን ተፋጠን ሰንብተናል። ስንነካከስ እንዳንጠፋፋ በሚያስፈራበት መልኩ ሁላችንም ግብ ግብ ስንገጥም እዚህ ደረስን። መንግስት በጉልበቱ ሲገፋበት፥ ሕዝብ በአመፁ ሲዘልቅበት፥ አማራጭ ኃይል በሁሉ አቀፍ ትግሉ ሲዘምትበት፥ አካሄዱ ሁሉ ሲያስፈራ የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን ያሰኝ ነበር። ሕዝቡ ሁሉ በሁሉም አቅጣጫ ወደ አምላኩ ከመጮህ አልተቆጠበም። በአራቱም አቅጣጫ አንድነቷን እና ብልጽግናዋን በማይወዱ የተከበበች ሀገር ሆና ሳለ፥ ከውስጥ ደግሞ በነውጥ ስትናጥ ተስፋዋ እየመነመነ ጫፍ ደርሶ ነበር። ምን አልባት ታዲያ የማታ ማታ ፈጣሪዋ ኢትዮጵያን ከምጥ ሊገላግላት፣ ውጥረቷን አርግቦ ሰላምን ሊሰጣት አስቦ ይሆን ዶ/ር አብይ እርስዎን ወደ አመራር ያመጣዎት? ካለንበት አጣብቂኝ ለመውጣት ረዥም መንገድ መሄድ እንዳለብን እሙን ነው። ዶ/ር አብይ ለኢትዮጵያ ዘብ በመቆምና እኛም ለእርሳቸው ዘብ በመቆም ይህን የተስፋ ጭላንጭል ጠላት እንዳያጨናግፍ ሁላችንም የየበኩላችንን ድርሻ መወጣት ይገባናል። አሁን ከፊታችን የተደቀነው ወሳኝ ሰዓት እኛ ተመልካች ሆነን፥ ዶ/ር አብይ ደግሞ በፊታቸው ያለውን ፈተና ያልፉ እንደሆነ ለማየትና ብያኔ ለመስጠት በጥርጥር ዓይን የምንመለከታቸው አይደለም። ወይንም እኛ ሁላችን እሳቸውን የምናዋክብበት ጊዜ አይደለም፤ ነገር ግን እኛም ሆንን እሳቸው የመፍትሄው አካል ከመሆን እንዳንጎድል የምንጠነቀቅበት ጊዜ ከምን ጊዜውም በላይ አሁን ነው።

በአንደኛ ደረጃ፥ ህዝብ ካንዣበበት አደጋ አምልጦ በሰላምና በመረጋጋት እንዲኖር ዶ/ር አብይ ራስዎን ከአጣብቂኝ መውጫ አድርገው ለሕዝብ የተሰጡ ይሆኑ ዘንድ የተሰጠዎትን የሕዝብ ፍቅርና አመኔታ አነሳስተዎት ለኢትዮጵያ ዘብ ይቆማሉ ብዬ አምናለሁ። ከዚህ በፊት በተለያዩ መድረኮች ያደርጉ የነበረውን ንግግርዎትንና ስብዕናዎን፣ አምላክ ወደ ብርሃን አውጥቶ በሕዝቡ ልብ ውስጥ እርስዎን አስቀምጧል። ሕዝቡ ትልቅ ተስፋም እንዲኖረው አድርጓል። እርስዎ ታማኝነትዎን ለመንግስት ዕድሜ ቅጠላ ሳይሆን ሰሚ ላጣው ሕዝብ እንዲሆን ማድረግ ተገቢ ነው። ለጠ/ሚ ስልጣንም ያበቃዎት በቀዳሚነት የሕዝብ ትግል ነውና። በመንግስት ዘንድ የሕዝብ ጆሮና ዓይን በመሆን የሕዝብ ጠበቃ እንዲሆኑና የሚመሩትን መንግስት ወደ አዲሲቷ ኢትዮጵያ አዋላጅነት እንዲያሻግሩ ታሪካዊ ጥሪያዎን ይወጡ ዘንድ ተልዕኮዎን ለአንዲትም ደቂቃ መዘንጋት የለብዎትም። ይህንንም ሃላፊነትዎን እንዲወጡ ፋታ ባገኘሁ ይሉ ይሆናል። ግን ፋታ እንዲሰጥዎት የሚያደርጉት እርስዎ ራስዎ በሚያደርጉት ተግባር ነው። በማስተዋል በመመላለስ ሁለት ነገሮችን ቢያደርጉ ፋታ የሚያገኙ ይመስለኛል።

በመጀመሪያ የሕዝብን ጥያቄ በየደረጃው ለመመለስ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ መንቀሳቀስን ቸል የማይሉት ነገር ሆኖ ሲገኝ ነው። በሁለተኛ ደረጃ የምንሄድበትን አዲስ አቅጣጫና ራዕይ እየነገሩንና አድራሻችንን እያሳዩን፥ አንድ ልብ ኖሮን እንደ አንድ ቤተሰብ የምንሄድበትን አካሄድ ለማስጨበጥ የሚተጉ ሆነው ሲገኙ ነው። አባቶች ደማቸውን አፍሰው በመሞት ኢትዮጵያን አቆይተው ዛሬ ለዚህች እናት ኢትዮጵያ ጠ/ሚ ለመሆን ታድለዋል። በተራዎ እርስዎ ራስዎ ለኢትዮጵያ በመኖር ኢትዮጵያን የሁሉ በእኩልነት የመኖሪያ እና የማረፊያ ሀገር እንድትሆን የበኩሉዎን ታሪካዊ ድርሻ መወጣት ይጠበቅብዎታል። ሁሉም መልካም ምኞቱንና በጎ ፍቃዱን እንደለገሰዎት በማወቅ ለተሰጠዎት ለዚህ ታላቅ ፀጋ ታማኝ እንዲሆኑ ማስተዋል ይብዛልዎት። በሁሉ ነገር መልካም እንዲሆንልዎት የመላው ኢትዮጵያዊ ፀሎትና ሰላማዊ ትግል እንደማይለይዎት ጽኑ እምነቴ ነው።

በሁለተኛ ደረጃ፥ ኢሕአዴግ ራሱን ለማትረፍ ከዶ/ር አብይ የበለጠ መውጫ አያገኝምና ለዶ/ር አብይ ዘብ በመቆም ህልውናውን በሀቅ ምርጫ ለማስቀጠል ራሱን ካለው የጊዜው የሕዝብ ጥያቄ ጋር ማጣጣም ይኖርበታል።  የኢትዮጵያ ሕዝብ በቅንነት አገልጋይ ለሆነ ሁሉ የሃይማኖት የጎሳና የፖለቲካ ፓርቲ አባልነቱ ማንነት ውሳኔውን ሳያዛባ በአስተሳሰቡ ምንነት ላይ ብቻ ተደግፎ ፍቅሩን እንደሚለግስ በዶ/ር አብይ ምርጫ ምክንያት የታየው ደስታ ያረጋግጣል። ይህም የኢትዮጵያ ሕዝብን ቅንነትና ታላቅ ስብዕና ያሳያል። እስካሁን መንግስት የሄደበት አካሄድ ስልጣንን በጉልበት እንጂ በእውነተኛ ምርጫ አላገኝም ብሎ ያመነ ይመስል ከዲሞክራሲ የተፋታ ነበር።

ታዲያ ዛሬ በእነ ክቡር አቶ ለማና ክቡር አቶ ገዱ ሕዝብን የማዳመጥና የማገልገል አስተሳሰብ ራሱን አጥምቆ ቢንቀሳቀስ፥ በእውነተኛ ምርጫ ለስልጣን የመታደል ዕድል ሊያገኝ እንደሚችል ጭላንጭል እየታየ ነው። የትኛውም በጦር የመጣ መንግስት እኔ እስከማውቀው ድረስ እንዲህ ያለ የመሸጋገሪያ ድልድይ ከራሱ አብራክ በወጣው ልጅ ዕድል ሲያገኝ አላየሁም ደግሞም አልሰማሁም። በጎም ሆነ ክፉ እያደረገ ለ27 ዓመታት እንደፈለገው ገዝቶ ሲያበቃ፥ እንደገና በዲሞክራሲ በመዳኘት በምርጫ ስልጣኑን ቢያጣ እንኳን እንደ ኢሕአዴግ ህልውናውን ከመጥፋት አስመልጦ ማስቀጠል የሚችልበትን ዕድል አግኝቷል። ታዲያ ለዚህ ምክንያት የሆኑት ዶ/ር አብይን በሙሉ ስልጣን የመመራት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ የኢሕአዴግ ምክር ቤት አባላት በመረባረብ የውስጥ እንቅፋት የሚሆነውን ሁሉ በማሳመን ሕዝብን ማክበር ይኖርባቸዋል።

በሦስተኛ ደረጃ፥ ተቃዋሚው ሃይል ለኢትዮጵያ አማራጭ ሃይል ለመሆን ዶ/ር አብይ ሁነኛ መውጫ ሊሆኑ ብቃት ያላቸው ይመስላሉና ለዶ/ር አብይ ዘብ በመቆም ለሰላሙ ትግል ሃይሉን አጠናክሮና አቀናጅቶ መቅረብ ይኖርበታል። ተቃዋሚው እውነተኛ ምርጫ እንዲዳኘው የሚያስችል የዲሞክራሲ ምህዳር ቢኖርለት የአመፅ ናፍቆት የለውም። የዲሞክራሲው ምህዳር እንዲሰፋና እንዲንሰራፋ መድረኩ ክፍት ከሆነ፥ በውጭም ሆነ በውስጥ ያሉት ተቃዋሚዎች አማራጭ ሃይል ለመሆንም ሆነ ለመተባበር ዕድል ፈንታ ይሰጣቸዋል። ለዚህም ነው ተቃዋሚ ሃይሎች ዶ/ር አብይን ለዲሞክራሲ ጉዞ ከአጣብቂኝ መውጫ ይሆኑ ዘንድ ደጀን በመሆን እውነት ራሷ ይህንን የዲሞክራሲ አካሄድ የሚቃወሙትን እንድትሞግትና እንድትረታ ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ይበልጥ መቀናጀት የሚያስፈልጋቸው።

ለማንኛውም የዛሬ ሁለት ዓመት ሊመጣ ያለውን ምርጫ ከቁጥር በማስገባት እስከዚያው ድረስ ዶ/ር አብይ ለምርጫው ፍትሀዊነት ሁሉን እያሳተፉ የለውጥ ዋዜማ ሽታ እስካመጡ ድረስ በትዕግስትና በመረዳት ፋታ መስጠት የግድ ነው። አሁን ዶ/ር አብይን በተመለከተ በሁሉም አማራጭ ሃይሎች ዘንድ የሚታየው በጎ ፍቃድና የእምነት ተስፋ እጅግ የሚያበረታታቸው ይመስለኛል። ይህም መልሶ ለሕዝብ እንዲኖሩ ግፊት እያደረገ የሕዝብ እውነተኛ አገልጋይ እንዲሆኑ ጉልበት ይሆናቸዋል።

ላለፉት 44 ዓመታት በወጀብ ስትናወጥ የነበረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ደግሞ በአዲስ መንፈስ መሪዋና ሕዝቡ በፍቅር እጅና ጓንት ሆነው አዲሲቷ ኢትዮጵያ እንድትወለድና ሀገራችንም ለመጀመሪያ ጊዜ እፎይ የምትልበት ዘመን ይህ ጊዜ ይሁንልን። ይህ መለኮታዊ ዕድል አያምልጠን። ልባችን ለዚህ ውልደት ዘብ ለመቆም ይጨክን!

የኢትዮጵያ አምላክ ኢትዮጵያን አሰበ።

ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ!

ዶ/ር ዘላለም እሸቴ – ኢሜል፡ ethioStudy@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Lemma says

    April 7, 2018 03:16 pm at 3:16 pm

    Dr.Zelemem, yihin kemeselew wib hasabiwo gar becher yinuru.

    Ethioipiawinet shall prevail.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule