የሀገር መከላከያ ሠራዊትና የአማራ ክልል የጸጥታ ኀይል በማይጠብሪ ግንባር ከፍተኛ ድል እያስመዘገበ መሆኑን የ54ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል የሺበር አዳነ ተናገሩ። በማይጠብሪ ግንባር ለዳግም ወረራ የተነሳው አሸባሪውና ተስፋፊው የትህነግ ቡድን በሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ በአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻና ፋኖ እየተደመሰሰ መሆኑን የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን በግንባር ተገኝቶ ተመልክቷል። በማይጠብሪ ግንባር ያነጋገርናቸው የ54ኛ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ኮሎኔል የሺበር አዳነ እንደገለጹት ሽብርተኛው ትህነግ ከፍተኛ ኪሳራ ውስጥ ገብቷል። የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ጠላትን ለማሸነፍ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት አድርጎ መግባቱ እየተመዘገበ ላለው ድል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ኮሎኔል የሺበር አስታውቀዋል። ኮሎኔሉ ሽብርተኛው ትህነግ ከዓመታት በፊት የቀየሰውን የጦርነት … [Read more...] about የማይጠብሪው ድል
operation dismantle tplf
በአምቦ ከተማ ጥይቶችን በአምቡላንስ ሲያጓጉዙ የተገኙ ተያዙ
በአምቦ ከተማ 1 ሺህ 377 ተተኳሽ ጥይቶች በህገ ወጥ መንገድ በተሽከርካሪ ጭነው ሲያጓጉዙ የተገኙ አራት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ። ግለሰቦቹ ጥይቶቹን በመንግስት አምቡላንስ ተሽከርካሪ ጭነው ሲያጓጉዙ እንደተገኙ የከተማዋ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሲሳይ ሂርጳ ገልጸዋል። ከከተማዋ ወጣ ብሎ በሚገኘው አዋሮ ቆራ አካባቢ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ትናንት ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ተኩል አካባቢ ነው ግለሰቦቹን ከነጥይቶቹ መቆጣጠር የተቻለው ብለዋል። ኮማንደር ሲሳይ እንዳመለከቱት፤ ግለሰቦቹ ጥይቶቹን በሴቶች "ታይት" አልባሳት ጠቅልለው በማዳበሪያ ውስጥ መድሃኒት አስመስለው በመጫን ከቡራዩ ከተማ ወደ አምቦ ለማሳለፍ ሲሞክሩ ነው የተደረሰባቸው። በዚህም አሽከርካሪው፣ ፋርማሲስት እና ሁለት የጥይቱ ተቀባዮች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳዩ እየተጣራ … [Read more...] about በአምቦ ከተማ ጥይቶችን በአምቡላንስ ሲያጓጉዙ የተገኙ ተያዙ
ዘመቻ: “እጃችሁን ከኢትዮጵያ ላይ አንሱ – #Handsoffethiopia”
ባለፉት 24 ሰዓታት “እጃችሁን ከኢትዮጵያ ላይ አንሱ - #Handsoffethiopia” በሚል መሪ ቃል በተካሄደ የትዊተር ዓለም አቀፍ ዘመቻ በርካታ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች የነቃ ተሳትፎ ማድረጋቸው ተገለፀ። 100 ሺህ ገደማ የትዊተር መልዕክት በተሰራጨበት ዘመቻ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እንዲከበር የሚጠይቁ እና አሸባሪው ህወሓት አገር ለማፍረስ እየሰራ ያለውን ሴራና ግፍ የሚያወግዙ መልዕክቶች ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እና መገናኛ ብዙሃን ጭምር ተላልፈዋል። በትዊተር ዘመቻው በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት እየተንቀሳቀሱ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሚጠይቀው መልዕክት ዐቢይ አጀንዳ ነበር። የትዊተር ዘማቾቹ በተለይም ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡትን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጄፍሪ ፊልትማን እየጠቀሱ፣ … [Read more...] about ዘመቻ: “እጃችሁን ከኢትዮጵያ ላይ አንሱ – #Handsoffethiopia”
ወንድማማቾቹ የኢትዮጵያ ዘማቾች
ወጣት አለኸኝ ይመኑ እና ወጣት ግርማ ብሩ ከአንድ ማህጸን የተወለዱ ወንድማማቾች ናቸው። ውልደትና እድገታቸው ደግሞ በአዳማ አቅራቢያ በሚገኘው ልዩ ስሙ ቆቃ በተባለው አካባቢ ነው። ምንም እንኳን የእናት አንጀት ለልጆቿ ምን ያህል እንደሚራራ ቢተወቅም አገር ጥሪ ባቀረበች ጊዜ ግን ከሰንደቅ ዓላማ የሚበልጥ የለምና ኢትዮጵያን ከጠላት እንዲታደጉ እናታቸው መርቀው በደስታ ለውትድርና እንደላኳቸው ይናገራሉ።ቤተሰብና የአካባቢው ሰዎችም ልጆቻቸው ለአገር መከታ ይሆኑ ዘንድ በምርቃትና በደስታ ሸኝተዋቸዋል። (ኢብኮ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ወንድማማቾቹ የኢትዮጵያ ዘማቾች
“ሸኔ ኦሮምኛ የሚናገር አሸባሪ ህወሓት ነው”
አሸባሪው ህወሓትን ለማጥፋት የሚደረገው ትግል በአሸባሪው ሸኔ ላይም ተግባራዊ ሊደረግ እንደሚገባ የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደአ አሳሰቡ። አቶ ታዬ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ አሸባሪው ህወሓትም ሆነ ሸኔ ለሀገር እና ለህዝብ ጠንቅ በመሆናቸው አሸባሪው ህወሓትን ለማጥፋት የሚደረገው ትግል ሁሉ በአሸባሪው ሸኔ ላይም በተመሳሳይ መልኩ ሊተገበር ይገባዋል። የኦሮሞ ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድሞቹ ጋር በመሆን ኢትዮጵያን ለመጠበቅ፣ ሉዐላዊነቷን ለማስከበር፣ ብልጽግናዋን እውን ለማድረግ መረባረብ ይገባዋል። የቡድኖቹ በጋራ ለመንቀሳቀስ መስማማት ‹‹በግልጽ አብረን ስንሰራ ነበር፣ ኦሮሞን ስናሰቃይ፣ ኢትዮጵያ ላይ ወንጀል ስንፈጽም የነበረው በጋራ ነው፣ ወንጀሎቹ ሁለታችንንም እኩል ይመለከቱናል የሚል መልዕክት አለው›› … [Read more...] about “ሸኔ ኦሮምኛ የሚናገር አሸባሪ ህወሓት ነው”
በጋምቤላና ቤንሻንጉል የትህነግ ተላላኪዎች እርምጃ ተወሰደባቸው
በጋምቤላ ከተማ በአሸባሪዎቹ ህወሃት እና ሸኔ ተላላኪነት የተጠረጠሩ ሶስት ግለሰቦችን ከጦር መሳሪያና ሌሎች ቁሳቀሶች ጋር በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ቱት ኮር ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በቁጥጥር ከዋሉት ግለሰቦች መካከል ሁለቱ የቀድሞውን የሀገር መከላከያ የደንብ ልብስና ጫማ እንዲሁም የሕክምናና ሌሎች ቁሳቁስ ይዘው ከጋምቤላ ከተማ ወደ ጫካ ሲንቀሳቀሱ ተደርሶባቸው ነው። ቀሪው ተጠርጣሪ ደግሞ ከህዝብ በደረሰ ጥቆማ በቤቱ በተደረገ ፍተሻ አንድ ዘመናዊ የጦር ሜዳ መነጽርና አንድ ሽጉጥ ተገኝቶበት እንደሆነ አመልክተዋል። ተጠርጣሪው ካሁን በፊትም ከአሸባሪው ህወሃት ጋር ግንኙነት እንዳለው ተጠርጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በተጠርጣሪዎቹ ላይ እየተደረገ ያለው ተጨማሪ ምርመራ ሲጠናቀቅ ጉዳያቸው ወደ … [Read more...] about በጋምቤላና ቤንሻንጉል የትህነግ ተላላኪዎች እርምጃ ተወሰደባቸው
የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎቶች ላልተወሰነ ጊዜ ታገደ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ከአርብ ነሐሴ 7 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለመሬት አስተዳደር ተቋማት፣ ለመሠረተ ልማት ቅንጅት እና ግንባታ ፈቃድ ባለስልጣን እንዲሁም ለ11ዱም ክፍለ ከተሞች ባስተላለፈው ሰርኩላር፣ የመሬት እና መሬት ነክ አገልግሎቶች ላልተወሰነ ጊዜ ሙሉ በሙሉ እንዳይሰጡ ውሳኔ አስተላልፏል። ካቢኔው ዕግዱን ያስተላለፈው በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ትኩረታቸውን በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲያደርጉ ለማስቻል ሲሆን አንዳንድ ስግብግብ ግለሰቦች ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታውን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም በአቋራጭ ለመክበር በመሬትና መሬት ነክ አገልግሎቶች ላይ ትኩረት በማድረግ በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ በመገንዘቡም ጭምር ነው ተብሏል። በዚህም ምክንያት ማንኛውም የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ የታገደ ሲሆን ስድስቱም … [Read more...] about የመሬትና መሬት ነክ አገልግሎቶች ላልተወሰነ ጊዜ ታገደ
“ምዕራቦች በምዕራብ —– የትንታጎች ድል”
ሽብርተኛው የህወሀት ሽብርተኛ ቡድን አገራችንን ለመበታተንና ህዝባችንን አንገት ለማስደፋት የከፈተብንን ጦርነት ለመመከት በማይፀብሪ ግንባር የተሰማሩት የምዕራብ ዕዝ ፣ የአማራ ልዩ ሀይል ፣ ህዝባዊ ሚሊሻ ፣ ፋኖ እና የክተት ጥሪውን ተቀብለው የተሰለፉ ሀይሎች አንፀባራቂ ጀግንነት በመፈፀም ላይ ይገኛሉ። ጁንታው ባለፉት ቀናት የሰነዘረውን ማጥቃት በመመከትና ወደ መልሶ ማጥቃት በመሸጋገር በተወሰደው እርምጃ 222 የጠላት ሀይል ተደምስሷል። 01 ዲሽቃ፣ 04 መትረየስ፣ 01 ስናይፐር፣ 04 ተተካይ ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 31 ኋላቀር መሳሪያ፣ 25 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ፣ 4 ሺ የብሬን ጥይት፣ 3ሺ800 የብሬን ጥይት፣ 100 የዲሽቃ ጥይት በመማረክ በጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረስ ችሏል። የምዕራብ ትንታጎቹ በግንባሩ ከተሰማራው ሀይል ጋር በመሆን … [Read more...] about “ምዕራቦች በምዕራብ —– የትንታጎች ድል”
ትውስታ ዘ ዳንሻ – ታላቁ ጥቁር!
አምስተኛ መካናይዝድ ክፍለጦር ወታደራዊ ካምፕ ውስጥ እንደ ወትሮው ከዋርድያዋች ውጭ ሁሉም ተኝቷል። አንድ ታላቅ ፣ ጥቀር የሌሊት ልብሱን እንደ ለበሰ መፅሃፍ ያነባል ድንገት የቶክስ ድምፅ ሰማ በአካባቢው ሁሌም የቶክስ ድምፅ መስማት የተለመደ ቢሆንም ወታደር ነውና ምልልስ ካለ ብሎ ለማዳመጥ ሞከረ ከሁለት አቅጣጫ መሆኑን ተረዳ። ስልኩን አነሳ ወደተለያየ ቦታ ደወለ ሁሉም አይሰራም ስልኩን አየው ኔትወርክ የለውም አሁን ችግር እንዳለ ተራዳ ካለበት ክፍል ግድግዳ እየታከከ ወደ በሩ ተጠጋና በሩን ሲከፍተው የተመታ ጓዱ ከነክላሹ በጀርባው ወደቀ ወዲያው የቶክስ ሩምታ ወደ በሩ አቅጣጫ ተከፈተበት እንደምንም ከወደቀው ጓዱ ካላሹን ተቀብሎ እየተኮሰ በቅርብ ቀን ወደተሰራች የብሎኬት ግቢ ዘሎ ገባ። በግቢው ውስጥ አንደ ገባ የራሱ ጓድ የሆነች ሴት ወታደር በብሎኬት አጥር ቀዳዳ … [Read more...] about ትውስታ ዘ ዳንሻ – ታላቁ ጥቁር!
ጥቁር ውሃ ላይ አስጨርሶ፣ እንደገና የፈረጠጠው ጄኔራል ከበደ ፈቃዱ ማን ነው?
የህወሃቱ ታጋይ ጄ/ል ከበደ በ1988 ዓም የ31ኛ ክ/ጦር 3ኛ ብርጌድ ፓራ ኮማንዶ፣ የ1ኛ ሻለቃ አዛዥ ሆኖ ሰርቷል። በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት በ31ኛ ክ/ጦር ምክትል ብርጌድ አዛዥ ሆኖ አገልግሏል። በ1992 ዓም 35ኛ ክ/ጦር ስትፈጠር የ35ኛ ክ/ጦር 3ኛ ብርጌድ አዛዥ ሆኖ ተሹሟል። በ1997 ዓም ኮር የሚባለው አጀረጃጀት ፈርሶ ዕዝ የሚባል አደረጃጀት ሲቋቋም፣ ግለሰብ የ35ኛ ክ/ጦር ም/አዛዥ ቀጥሎም የ33ኛ ክ/ጦር ዋና አዛዥ ሆኖ እስከ 2006 ዓ/ም ሠርቷል። በ2006 ዓ/ም እነ ጄኔራል አበባው ታደሰን ለማስወጣት በተደረገው ግምገማ፣ ግለሰቡ የአበባው አሽከር ነህ ተብሎ ተፈርጇል። ይህን ተከትሎም ከክፍለ ጦር አዛዥነቱ ተነስቶ፣ የዕዙ ማሰልጠኛ ት/ት ቤት አዛዥ ሆኖ ተመድቧል። የጡረታው ጊዜ ሲደርስ “ተጠቅሞ ይውጣ” ተባለና … [Read more...] about ጥቁር ውሃ ላይ አስጨርሶ፣ እንደገና የፈረጠጠው ጄኔራል ከበደ ፈቃዱ ማን ነው?