• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢትዮጵያን ለማፍረስ መስከረም 2013 በትህነግ የተዘጋጀው ሰነድ

September 26, 2021 11:13 am by Editor 1 Comment

“የትግል ልዩ ምዕራፍ እድገቶች እና የምከታችን ቀጣይ ስትራቴጂዎች፣ ስልቶች እና አቅጣጫዎች” በሚል ርዕስ ኢትዮጵያን በረቀቀ ስልት ለማፈራረስ ካልተቻለም የትህነግን ጡንቻ በማሳበጥ የመደራደር ዐቅሙን ለማጎልበት እንዲረዳ የወጣ ባለ 86 ገጽ ሰነድ እዚህ ላይ ይገኛል።

“የትግል ልዩ ምዕራፍ እድገቶች እና የምከታችን ቀጣይ ስትራቴጂዎች፣ ስልቶች እና አቅጣጫዎች” Download

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    September 27, 2021 09:48 am at 9:48 am

    ወያኔዎች የክፋታቸው ጥግ ሰማይ ጠቀስም ቢሆን የሚደነቁ ናቸው። ይህ ሁሉ ሰነድና ዝግጅት ሲደረግ አንድም ሰው ሚስጢራቸውን አለማውጣቱ በራሱ የሚያስገርም ነው። በእርግጥ የኢሳያስ የስለላ መረብ ደርሶበት ለዶ/ር ደብረጽዪን በፊት ለፊት ተው ይህ ለጦርነት መዘጋጀታችሁ አያዋጣችሁም እንዳለው ተረድተናል። ይሁን እንጂ የሰሜን እዝ አፍንጫ ስር ነዳጅና የጦር መሳሪያ ሲያከማችሁ፤ ከማህል ሃገር የነበሩ በጡረታና በሌላም መልክ የተሰናበቱ ታጋዪችን ሲሰበስቡ አንድም የወገን ሰው አለመንቃቱ የቱን ያህል የወያኔ አሰራር የሰሜን እዝ ጦርን የራሱ ተላላኪና አራሽ ገበሬ አድርጎት እንደነበር በግልጽ ያሳያል።
    አሁን እንሆ ወያኔ የነደፈው የተባለነውን የተንኮል ጥራዝ አንብቦ ለተረዳ ከስልጣን ከተባረሩ በህዋላ ያዘጋጅት ሳይሆን ገና ቀደም ብሎ የነደፉት ለመሆኑ አመላካች ነገሮች ብዙ ናቸው። በእርግጥም ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ጊዜው አሁን ነው ማለታቸው የቱን ያህል የልብ ልብ እንደተሰማቸውና እኛ ብቻ የምስራቅ አፍሪቃ የወታደራዊ ሃይል የበላይ ነን ብለው እንደሚያምኑ በግልጽ ያሳያል። ቁም ነገሩ ትግራይ ለትግራይ በትግራይ ይበሉ እንጂ ለራሳቸው ስልጣን መራዘም የተነደፈ የፓለቲካ ሴራ ለመሆኑ የአለምን እይታና የፓከቲካ አሰላለፍ በተለይም የአፍሪቃ ሃገሮችን ድጋፍ ሰጭነትና ያለዚያም ኢትዮጵያን በመናዳችሁ አይናችሁን ላፈር መባሉን በግልጽ ያላካተተ በጅሎች ለጅሎች የተነደፈ ሰነድ እንደሆነ ልብ ያለው ያስተውላል። ግን ይህ ሁሉ እብደት መንግስት ነኝ በሚለው የዶ/ር አብይ በኩል የሚሰነዘርበትን የአልሞት ባይ ተጋዳይ ፍልሚያ ልብ ብሎ የመዘነው አይመስልም። አይ ወያኔ ሁሌ ጦርነት ከእኔ በላይ አዋቂ የለም ብሎ መደንፋት። ተራራ ያንቀጠቀጠው ትውልድ በተራሮች መካከል ተወሽቆ ሲቀጠቀጥ። አታድርስ ነው። ከዚህ ባሻገር ሰነድ ስለ ኤርትራና ኢሳያስ ዘባርቆ የዶ/ር አብይና የኢሳያስን ጥምረት ነካክቶ በጎን የሱዳን ድጋፍን አምኖ የተቀበለ የሙት ድርጅት የፓለቲካ ሰነድ ነው።
    ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲኦል ድረስ እንጓዛለን እያለ የሚዝተው ጌታቸው ረዳ ሴኩቱሬ በመብረቃዊ ጥቃት ሁሉን ተቆጣጠርነው ብሎ እንደ ደነፋው አይነት የንፋስ ወሬ ነው። ባይገባው ነው እንጂ ጌታቸው ረዳ አሁንም የቆመበት ሥፍራ ሲኦል ነው። የስንቶችን ደም አፍሶ፤ ስንቶችን አስለቅሶና ዘርፎ ለመኖር ያወጣው ሰነድ ይኸው ህዝባችን እያየው ነው። የሚገርመው ግን የትግራይ ልጆች ከእውነት የራቀ ዝምታና በአንድ በኩል በዘርና በቋንቋ ብቻ መሰለፍ ነው። ለትግራይ ህዝብ የሚያስብና ህዝቤ ተራበብኝ የሚል ድርጅት የእርዳታ እህል እንዲያደርሱ የተላኩ ካሚዎኖችን አስቀርቶ ሾፌሮቹ ትግሉን ተቀላቅለዋል ብሎ ወሬ ያናፍሳል? ይህ እብደት አደለም የሚል ማንም የትግራይ ተወላጅ ራሱ ያበደ ብቻ ነው። ግን ወያኔ መንግስት ከሆነ በህዋላ የተወለድ የትግራይ ልጆች ወያኔ በትግራይ ህዝብ ላይ ያደረሰውን ያለፈ ገመና አያውቁም። የአሁኑን መከራ ግን እየተጋቱት ነው። ያኔ ታጋይ የነበሩትም በዘርና በቋንቋ ስለ ሰከረው ከአብሮ ከእብዶች ጋር እየተመሙ ነው። ወያኔ የትግራይን ህዝብ የራሱ መነገጃ ካደረገው ዘመናት ተቆጥረዋል። አሁን ረሃብ ያጠናወታቸው ስጋቸው ተሸብሽቦ አጥንታቸው ገጦ የሚታይ ፎቶ ለዓለም ቢለቀቅ ደስታውን አይችለውም። ያኔም በትግራይ ህዝብ ላይ የነገድበት በዚህ አይነት ሁኔታ ነው። ወደፊቱም የወያኔ ወረት የትግራይ ህዝብ ነው። የትግራይ ህዝብ መከራና ችግር ግን ለእነ ጌታቸው ረዳ ጭራሽ አይታያቸውም። እስቲ አመራር ላይ ካሉት መካከል ልጆቻቸው፤ ዘመዶቻቸው በጦር ሜዳ ላይ አሉ የምትሉ ካላችሁ ንገሩን? የስዬ አብርሃ ልጆች ትግራይ ውስጥ ናቸው? የጻድቃን ቤተሰቦች ይዋጋሉ። የዶ/ር ደብረጽዪን ዘመድና አዝማድ ውጊያ ሜዳ ላይ ናቸው? አይደሉም። የትግራይን ህዝብ በውሸት እያደነቆሩ ለዘመናት ሲያስገድሉትና አሁንም በእሳት የሚማግድት እነዚህ የሙታን ስብስቦች ናቸው። የትግራይ ህዝብ ሁሉን መዝኖ በመነሳት ከምድረገጽ ወያኔን እስካላጠፋ ድረስ መከራው ይቀጥላል።
    ያው መግቢያው ላይ እንዳልኩት ግን ወያኔ አስገራሚ ድርጅት ነው። ከ 250 ሺ በላይ ህዝብ በሰውርና በሚስጢር ያስታጠቀው ወያኔ የዶ/ር አብይን መንግስት ነኝ ባይነት ከመፈተን አልፎ አፋርና አማራ ክልል ድረስ ዘልቆ በመግባት ማበራየቱ በራሱ የመንግስት አይነት አቋምና መዋቅር በትግራይ መሬት መስርቶ እንደነበር ያሳያል። ተጨፈጨፉ፤ ተቆርጦ የቀረው ተለቀመ፤ እንደ ድቄት ተበተኑ፤ ለወሬ ነጋሪ የቀረ የለም ኸረ ምን የማይባል ነገር አለ የተባሉት ወያኔዎች የትግራይ ክልልን ባንዲራ የተቀቡ ታንኮች፤ የአየር መቃወሚያዎች፤ መድፎችና ዲሽቃዎች ይዘው የወሎን፤ የአፋርንና የአማራን ህዝብ ያለምንም ርህራሄ ሲገድሉና ሲዘርፉ አዲስ አበባ ላይ ተቀምጦ አካኪ ዘራፍ የሚለው የአብይ መንግስት የአህያ ባል ከጅብ አያስጥል አይነት ነው። ወያኔ ገና ብዙ ገመና የሚያደርስ ድርቡሽ ድርጅት ለመሆኑ አሁን በላሊበላና በሌሎች አካባቢዎች የሚያደርሱትና በማድረስ ላይ ያሉትን ጸረ ሰው፤ ጸረ እንስሳና ጸረ ሰብል የሆነ ተግባር ለትውልድ የሚረሳ አይሆንም። ስለሆነም የወያኔን የዘመናት ሴራ ጠንቅቆ ለሚረዳ ሰው ቀድሞም በህዝብ ላይ ያደረሱት አሁንም የሚያደርሱት ወደፊትም የሚያደርሱት ግፍና ዝርፊያ አብሯቸው የኖረ የፓለቲካ ባህሪያቸው እንጂ ከስልጣን ከተባረሩ በህዋላ የተከሰተላቸው እይታ አይደለም። ይህ በትህነግ ተዘጋጀ የተባለውም ሰነድ የሚያሳየው የክፋታችውን ጥግ ነው። ግን መቼ ይሆን ነገርን መርምረን፤ ሰውን በሰውነቱ ተቀብለን፤ እይታችን ሰፍቶ፤ ከዘርና ከክልል ፓለቲካ ርቀን እውነትን በማየት ለህዝባችን ተደራሽ የምንሆነው? ያ ቀን ይመጣ ይሆን ወይስ እድሜ ልካችን አማራ፤ ኦሮሞ፤ ትግሬ ገለ መሌ በማለት የደንበር ገተር የዘር ፓለቲካችን ይቀጥላል? ቆይቶ ማየት ነው። ለአሁን ይብቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule