የሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩና ሁሉን ዓቀፍ መንግሥት በኢትዮጵያ እንዲቋቋም ለማስቻል በአሜሪካ የእንደራሴዎች ምክርቤት የተዘጋጀው ረቂቅ ሕግ ያለአንዳች ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ኤፕሪል 10፤2018ዓም ጸድቋል። ህወሓት እጅግ ከፍተኛ የውትወታ ገንዘብ ያፈሰሰበትና በርካታ የፖለቲካ ሥራ የሠራበት ረቂቅ በምክርቤቱ በሚገኙ 108 እንደራሴዎች ስፖንሰር ያደረጉት ሲሆን የሁለቱም ማለትም የዴሞክራትና የሪፑብሊካን እንደራሴዎች በጣምራነት የደገፉት ረቂቅ ነበር። በዋሽንግቶን ዲሲ በ“አምባሳደርነት” ሹመት የኢህአዴግ ተወካይ ሆኖ የተቀመጠው ካሣ ተክለብርሃን ለምክርቤቱ ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ ደብዳቤ ልኮ እንደነበር H.R. 128 ለኢትዮጵያ በፌስቡክ ገጹ ላይ ባተመው የደብዳቤው ፎቶ አስታውቋል። በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኅብረት ያደረጉት እንቅስቃሴ አንዱ የድሉ አካል እንደሆነ … [Read more...] about H.R. 128 ያለ ተቃውሞ አልፏል!
Middle Column
A charismatic young leader tries to calm ethnic tension in Ethiopia
"The price of power may have been private assurances that aspects of the security establishment would be left untouched" Intelligence Expert at Georgetown University. IN ITS three decades of existence, the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) has gone through only two leaders. Neither came to power through a competitive vote. So it was with a sense of novelty that Ethiopians awaited the outcome of a secret ballot held on March 27th to determine the new chairman of … [Read more...] about A charismatic young leader tries to calm ethnic tension in Ethiopia
“መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው” ጠ/ሚ/ር ዓብይ አህመድ
"መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው፤" እየተባለ ጆሮዋችን ሲደነቁርባት በነበረ አገር አዲሱ ጠቅላይ ሚ/ር ዓብይ አህመድ “መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው” በማለት ለኢትዮጵያ የሚመጥን ንግግር ኣድርገዋል። ይህንን አስመልክቶ ሪፖርተር ያጠናቀረው ዘገባ አንዲህ ይነበባል። "ኢትዮጵያውያን ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ደግሞ ኢትዮጵያ ነን" ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሰኞ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. በፓርላማ ሲሰየሙ ባደረጉት ንግግር፣ በሕዝብ ዘንድ ትኩረትን ከሳቡት ጉዳዮች መካከል የቤተሰብ ጉዳይ አንዱ ነው። የሰባት ዓመት ልጅ እያሉ ሩቅ፣ ጥልቅና ረቂቅ ራዕይ በውስጣቸው የተከሉትን፣ ያሳደጓቸውንና ለፍሬ ያበቋቸውን ወላጅ እናት ለማመሥገን እንዲፈቀድላቸው ሲጠይቁ ብዙዎች ልባቸው ተነክቷል። እናታቸው … [Read more...] about “መጪው ጊዜ በኢትዮጵያችን የፍቅርና የይቅርታ ጊዜ ነው” ጠ/ሚ/ር ዓብይ አህመድ
“(ዓብይ) ብዙ ቃል የገባቸውን ጉዳዮች ፈጽሟል”
ማክሰኞ መጋቢት 18 ቀን 2010 ዓ.ም. ምሽት እኩለ ሌሊት እየተቃረበ እያለ የተሰማው ሰበር ዜና በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ያነጋገረ ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከኢሕአዴግ ሊቀመንበርነታቸውና ከጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው ለመልቀቅ መወሰናቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ፣ ተተኪያቸው ማን ይሆን የሚለው በመላ አገሪቱ ዋነኛ መነጋገሪያ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በተለይ ማክሰኞ መጋቢት 11 ቀን 2010 ዓ.ም. ተተኪውን የግንባሩን ሊቀመንበር ለመምረጥ ስብሰባ የተቀመጠው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ለአንድ ሳምንት በመቆየቱ፣ በርካቶች በመላ ምቶችና በሴራ ንድፈ ሐሳቦች እንዲጨናነቁ አድርጓቸዋል፡፡ የአገሪቱ ፖለቲካ ለትንተና እስከሚያስቸግር ድረስ የተለያዩ መረጃዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች በመሰማታቸው፣ የተተኪው ማንነት ብዙዎችን ቢያሳስብ አይገርምም … [Read more...] about “(ዓብይ) ብዙ ቃል የገባቸውን ጉዳዮች ፈጽሟል”
የHR 128 እና የማግኒትስኪ ሕግ ትሥሥር፤ የህወሓት ፍርሃቻ!
ተጨማሪ መረጃ፤ ያለፈው ሳምንት መገባደጃ አካባቢ የኮሎራዶ 6ኛው ወረዳ እንደራሴ ማይክ ኮፍማን በድረገጻቸው እንዳስታወቁት HR 128 በኤፕሪል ወር ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክርቤት ድምጽ ይቀርባል ብለዋል። ጉዳዩን ከሚከታተሉ በርካታ ወገኖች መካከል የቅርብ መረጃ ያላቸው አቶ ኦባንግ ሜቶ የቀጠሮው ቀን ኤፕሪል 9 (ሚያዚያ 1) መሆኑን በፌስቡክ ገጻቸው በለቀቁት መረጃ አስታውቀዋል። ይህ ረቂቅ ጸድቆ በሕግ እንዲወጣ ከፍተኛ ሥራ እየሠራ የሚገኘውን የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግብረኃይል ፌስቡክ ገጽ በመሄድ ለረቂቅ ሕጉ እንዴት ድጋፍ መስጠት እንደሚቻል የበለጠ መረጃ ማግኘት ይቻላል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ባለፈው “ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ” የሚለውን ዘገባ በድጋሚ አቅርበናል። ይህ ዘገባ ህወሓት ለምን ረቂቅ ሕጉን እንደፈራውና እጅግ በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ ለማጨናገፍ … [Read more...] about የHR 128 እና የማግኒትስኪ ሕግ ትሥሥር፤ የህወሓት ፍርሃቻ!
“የክርስቲያን አገር በሆነችው ሙስሊሞች ሊነግሡባት ነው” ህወሓት ለአሜሪካ እንደራሴዎች
የአስራ ሰባት ታዋቂ ኦሮሞ ሙስሊሞችን ስም ለማስረጃነት አቅርቧል ከዝርዝሩ ውስጥ የዶ/ር አቢይ አህመድ ስም ይገኝበታል ህወሓት ከፊቱ የተጋረጠበትን የፖለቲካ ቀውስና ቀውሱን ተከትሎ ከጌቶቹ የተነሳበትን ተቃውሞና ግፊት አቅጣጫ ለማስቀየር ሃይማኖትን የተንተራሰ ስልት ተግባራዊ ማድረጉ ተሰማ። የሚካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ አገሪቱን ለእስልምና አክራሪ አሳልፎ ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ህወሓት በወኪሉ በኩል ስም ዘርዝሮ አቅርቧል። የጎልጉል ዲፕሎማት የመረጃ አቀባዮች ከዋሽንግቶን ዲሲ እንዳስታወቁት ህወሓት አሁን የተነሳበትን ዙሪያ ገጠም ተቃውሞ ከእስልምና አክራሪነት ጋር በማቆራኘት የአስራ ሰባት ኦሮሞ ሙስሊም ታዋቂ ፖለቲከኞችን፣ የመብት ተሟጋቾችን፣ ወዘተ ስም ዘርዝሮ ነው ያቀረበው። ዙሪያው ገደል የሆነበት ህወሓት የስም ዝርዝሩን ባቀረበ ጊዜ ራሱን የክርስቲያን መንግሥት አድርጎ … [Read more...] about “የክርስቲያን አገር በሆነችው ሙስሊሞች ሊነግሡባት ነው” ህወሓት ለአሜሪካ እንደራሴዎች
“እምቢተኛውን” ኦህዴድ በመርዝ ወይስ በመሰንጠቅ?
“ስንደመር እናሸንፋለን፣ አንድ ካልሆን እንጠፋለን” የለማ መገርሳ ተማጽንዖ!! ኦህዴድ በድንገት ያካሄደውን “ስትራቴጂክ” የተባለ የአመራር ሽግሽግ አስመልክቶ ለማ መገርሳ በሰጠው መግለጫ በተደጋጋሚ “አንድ ካልሆንን እንጠፋለን፤ ስንደመር እናሸንፋለን” ማለቱን በማስታወስ ህወሓት ኦህዴድን ለመበተን እየሠራ መሆኑን በተደጋጋሚ ለጎልጉል መረጃ የሚሰጡት የኢህአዴግ ሰዎች ተናገሩ። ወታደራዊ አገዛዙ በትሩን በኦህዴድ አመራሮች ላይ እያሳረፈ ነው። የጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የአዲስ አበባ ዘጋቢ የመረጃ ሰዎቹን ዋቢ በማድረግ እንደገለጸው የኦህዴድ መፍጠን ህወሓትን አበሳጭቷል። በድንገት ኦህዴድ ሽግሽግ ከማድረጉ በፊት የህወሓት ቅርብና ታማኝ የሚባሉ የሥራ አስፈጻሚ አባላትን አባርሯል፤ አግዷል። እንዲሁም ዝቅ በማድረግ አቅም አልባ አድርጓቸዋል። የማጽዳቱ ሥራ ጅምር እንደሆነና ወደፊትም … [Read more...] about “እምቢተኛውን” ኦህዴድ በመርዝ ወይስ በመሰንጠቅ?
ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ
ከዚህ በፊት በአሜሪካ ምክርቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በረቂቅ ሕግነት ከቀረቡት መካከል ህወሓት/ኢህአዴግ HR 128 እጅግ ፈርቶታል። ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን - ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል። ይህንን ረቂቅ … [Read more...] about ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ
የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ እና የህወሓቶች አሻጥር (የሰነድ ማስረጃ)
ጥቅምት 03/2010 ዓ.ም በተለያዩ የኦሮሚያ አከባቢዎች የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዶ ነበር። በወቅቱ “ይህን የተቃውሞ ሰልፍ ማን ነው የሚያስተባብረው?” የሚለው ጥያቄ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በውጪ የሚገኙ የኦሮሞ ልሂቃን የተቃውሞ ሰልፉን እንዳልጠሩ ሲገልፁ ነበር። በተመሳሳይ አዲሱ የኦህዴድ አመራር በጉዳዩ ዘሪያ እጁ እንደሌለበት መግለፁ ይታወሳል። በእርግጥ ሰልፈኞች ከወትሮ በተለየ መልኩ የኦነግን ባንዲራ ይዘው ታይተዋል። በአንፃሩ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ደግሞ ምንም ዓይነት አመፅና ሁከት እንዳይቀሰቀስ ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ሲያደርግ ነበር። እኔ በግሌ ከታች የሚታየውን ፎቶ ሳነሳ ፖሊሶች ስልኬን ቀምተውኝ የነበረ ሲሆን ማንነቴን ከአጣሩ በኋላ ነው የመለሱልኝ። በሌላ እንደ ዳኒኤል ብርሃኔ ያሉ ቀንደኛ የህወሓት ደጋፊዎች “የተቃውሞ ሰልፉ እየተመራ ያለው ከተጠበቀው በላይ ትልቅ … [Read more...] about የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ እና የህወሓቶች አሻጥር (የሰነድ ማስረጃ)
ወርቅነህ አሜሪካኖችን “ምረጡኝ፤ አስመርጡኝ” ያለበት የጠ/ሚ ምርጫ ተውኔት ይፋ ሆነ
እነ ለማ የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው - ወርቅነህ ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ለአሜሪካኖች “እኔ እንድመረጥ ድጋፍና ጫና ብታደርጉ የናንተን ፍላጎት ለማሳካት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነኝ” በማለት አሜሪካኖችን ሲወተውት እንደነበር ታወቀ። እርሱን እንዲመርጡ ድጋፍ ለመጠየቅ መነሻ አድርጎ ያቀረበው ሃሳብ “እነ ለማ ‹ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ› ቢሉም የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው፤ ከአማራው ጠቅላይ ሚኒስትር ቢመደብ ወደ አማራ ማድላቱ አይቀርም፤ ከሁለቱም ያልሆነ እንደእኔ ያለ ሰው መመረጥ አለበት” የሚል ነው። በግልጽ በማይነገር የጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህንን ያለው ሰሞኑን በአሜሪካ ቆይታው ከፖሊሲ አውጪዎችና የዓለምአቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ጋር ተገኝቶ ስለወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታና መፍትሄ ማብራሪያ ሲሰጥ ነው። … [Read more...] about ወርቅነህ አሜሪካኖችን “ምረጡኝ፤ አስመርጡኝ” ያለበት የጠ/ሚ ምርጫ ተውኔት ይፋ ሆነ










