• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እምቢተኛውን” ኦህዴድ በመርዝ ወይስ በመሰንጠቅ?

March 1, 2018 08:45 pm by Editor 5 Comments

  • “ስንደመር እናሸንፋለን፣ አንድ ካልሆን እንጠፋለን” የለማ መገርሳ ተማጽንዖ!!

ኦህዴድ በድንገት ያካሄደውን “ስትራቴጂክ” የተባለ የአመራር ሽግሽግ አስመልክቶ ለማ መገርሳ በሰጠው መግለጫ በተደጋጋሚ “አንድ ካልሆንን እንጠፋለን፤ ስንደመር እናሸንፋለን” ማለቱን በማስታወስ ህወሓት ኦህዴድን ለመበተን እየሠራ መሆኑን በተደጋጋሚ ለጎልጉል መረጃ የሚሰጡት የኢህአዴግ ሰዎች ተናገሩ። ወታደራዊ አገዛዙ በትሩን በኦህዴድ አመራሮች ላይ እያሳረፈ ነው።

የጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የአዲስ አበባ ዘጋቢ የመረጃ ሰዎቹን ዋቢ በማድረግ እንደገለጸው የኦህዴድ መፍጠን ህወሓትን አበሳጭቷል። በድንገት ኦህዴድ ሽግሽግ ከማድረጉ በፊት የህወሓት ቅርብና ታማኝ የሚባሉ የሥራ አስፈጻሚ አባላትን አባርሯል፤ አግዷል። እንዲሁም ዝቅ በማድረግ አቅም አልባ አድርጓቸዋል።

የማጽዳቱ ሥራ ጅምር እንደሆነና ወደፊትም በተለያዩ መዋቅሮች ማሻሻል በማድረግ ኦህዴድን በአዲስ የመሥራት ዕቅድ እንዳለ ለማ መገርሣ በቃለ ምልልሱ አመልክቷል። ይህንን አካሄድ ለጥንቃቄ ሲባል የሚደረግ መሆኑንን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ይናገራሉ።

ህወሓት እንዴት ተቀናቃኝ ፓርቲዎችን እንደሚበላ ጠንቅቀው የሚያውቁትና ተሳታፊ የነበሩት የኦህዴድ አዲስ አመራሮች ከቅርብ ጊዜ በኋላ እየያዙ የመጡት አቋም የራስ ምታት የሆነበት ህወሓት፣ ቢነቃበትም አመራሩን በኃይል ለማንበርከክና ድርጅቱን ለመበተን እየሠራ መሆኑ ተሰምቷል። እንቅስቃሴውን የሚረዱት የአሁኖቹ የኦህዴድ አመራሮች ግን “የወሰድነው እርምጃ ሁሉ ህዝባችንን ተማምነን ነው፤ በህዝባችን እንመካለን” በሚል በራሳቸው መገናኛ “እኛም አውቀናል…” አይነት ምላሽ መስጠታቸውን ጉዳዩን የሚከታተሉ ይገልጻሉ።

ለጎልጉል ዘጋቢ መረጃ የሰጡት ክፍሎች እንዳሉት ህወሓት በአስቸኳይ አዋጅ ስም ወታደራዊ አስተዳደሩን በመጠቀም በኦሮሚያ የመካከለኛ አመራሮች ላይ በትሩን ማሳረፍ መጀመሩን የታሰሩትን ስም በመጥቀስ ዘርዝረዋል። በተጨማሪም ገጠር ድረስ በመግባት በፈረሰው መዋቅር ላይ ህወሓት አመራር መስጠት ጀምሯል። የዓይን ምስክሮች እንደሚሉት ጠብመንጃ አንጋቾች አስተዳደሩን ሙሉ በሙሉ የተረከቡበት ደረጃ ደርሰዋል። አዲስ አመራርም ማደራጀት ጀምረዋል። በአንጻሩ ግን አዳዲስ አመራሮችን ማደራጀት መጀመሩ ካሁን በኋላ ኦሮሚያ ላይ እንደማይሠራ ተጠቁሟል።

ከወራት በፊት በ“ጥልቅ ተሃድሶ” ስም ከኦሮሚያ ከሁለት ሺህ በላይ አባላቱን ያገደውና ያባረረው ኦህዴድ ከ3000 በላይ ሚሊሺያ እንደመለመለ የኮማንድ ፖስቱ ፀሐፊ ሲራጅ ፈርጌሳ ባወጀበት ወቅት ሁሉም ሰላም፣ ሁሉም አማን እንደሆነ አመልክቶ ነበር።

በስልጤ ዞን በነፍስ ማጥፋት የሚወነጀለው ሲራጅ፤ ይህንን ባለ በቀናት ልዩነት ውስጥ ኦህዴድ መክዳቱን ያረጋገጠ ክልል-ዓቀፍ ተቃውሞ አገረሸ። እነ ሲራጅ ህወሓትን ለማስደሰት በህጻናት፣ በታዳጊዎችና በአዛውንቶች ደም የተነከረው እጃቸው ሳይጠግግ ዳግም በደም መጨማለቅ ጀምረዋል። በነቀምት፣ በደንቢ ዶሎና በባሌ ደም እያፈሰሱ ነው። ይህንን የተቃወሙ የኦህዴድ የአካባቢው አመራሮች ታስረዋል። የት እንደተወሰዱም አይታወቅም።

የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት የኦህዴድ ከፍተኛ አመራሮች ጉዳዩን በመቃወም የታሰሩት እንዲፈቱ ጠይቀዋል። በዚህ መሰሉ ውጥንቅጡ የወጣ አካሄድ የሚዳክረው ህወሓት የኦህዴድና የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች ላይ ጫና ለመፍጠር የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ተቀምጧል። የጎልጉል መረጃ አቀባዮች እንደሚሉት ነገ (አርብ) የሚደረገው የኢህአዴግ ሸንጎ (“ፓርላማ)” ፍትጊያ እንደሚኖርው ያሰጋው ህወሓት አቻ ፓርቲዎቹ ለድርጅታቸው መርህና ቃል ለገቡለት ዲሲፒሊን እንዲገዙ መወትወቱ የተፈራውን እንደማያስቀረው ነው።

ለጀርመን ድምጽ ቃለ ምልልስ የሰጡ የፓርላማ አባሎች እንዳሉት ጉዳዩ የመደገፍና የመቃወም ሳይሆን በቂ ማብራሪያ እንደሚጠይቁ፣ ማብራሪያው የሚያሳምን ሊሆን እንደሚገባው፣ ይህ ሳይሆን ድጋፍ ለመስጠት እንደሚቸገሩ አመልክተዋል። በሌላ አነጋገር “ማመን መቻል” አለብን ሲሉ ተደምጠዋል።

የጎልጉል ዘጋቢ ያነጋገራቸው የድርጅት ሰዎች አርብ የሚደረገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የማጸደቅ ስብሰባ በቀጥታ ለህዝብ እንዲተላለፍ ኦህዴድ ጠይቋል። ይህም በህወሃት በኩል ተቃውሞ ቢያስነሳም መጨረሻው ግን ምን እንደሆነ ገና አልታወቀም።

እዚህ ድረስ የተካረሩት ህወሓትና ኦህዴድ መጨረሻቸው ምን እንደሚሆን ለመገመት ቢያስቸግርም፣ ኦህዴድ ዶ/ር መረራ ከሚመሩት የኦሮሞ ሕዝብ ኮንግሬስ (ኦህኮ) ጋር በማንኛውም ጉዳይ ድርድር ለማድረግ፣ ለመወያየትና ስምምነት ለመፈጠር ሙሉ በሙሉ ፈቃደኛ መሆኑንና በቅርቡ ወደ ተግባር እንደሚገባ በከፍተኛ አመራሩ አማካይነት አመልክቷል።

ህወሃት “አሸባሪ” ብሎ ሲያሰቃያቸው ከነበሩት አካላት ጋር በሁሉም ጉዳዮች ለመደራደር በሩን መበርገዱን ይፋ ያደረገው ኦህዴድ የፓርላማ አባላቱን በማስተባበር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተግባራዊ እንዳይሆን አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት እንዲከፍልም ማሳሰቢያ እየቀረበለት ነው። የኦሮሞ አክቲቪስቶች፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ለመላው የፓርላማ አባላት እንዲያስቡበት እየመከሩና እያስጠነቀቁም ነው። በተለይም የጉዳዩ ዋና ባለቤት “ቄሮ” የኦሮሚያ ወኪሎችን (“የፓርላማ አባላትን”) ክፉኛ አስጠንቅቋል።

አዋጁ በድምጽ ብልጫ እንዳያልፍ የአማራ ክልል ወኪሎችም ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቦላቸዋል። እጅን ማውጣት “አፋችንን ለጉሙን፣ ግደሉን፣ እሰሩን ማለት ፍጹም ከህዝብ ጋር መቆራረጥ ነው” ሲሉም ስለወደፊቱ እንዲያስቡ ምክር አዘል ማሳሰቢያ አክለዋል።

ህወሓትና በህዝብ ጫና የተወጠረው ኦህዴድ፣ አቋሙን ወደ ህዝብ ያጋደለው ኦህዴድ፣ ስልታዊ አካሄድ መከተሉን ያወጀው ኦህዴድ፣ መጨረሻው ምን ይሆን? በኢህአዴግ የድርጅት መርህ መሠረት በድምጽ ብላጫ በማዕከላዊ ኮሚቴ የሚወሰነውን ውሳኔ ማስፈጸም የየድርጅቶቹ እና በድርጅቶቹ ጥላ ሥር የተመረጡ የፓርላማ አባላትና ምድብተኛ ባለስልጣኖች ግዴታ ነው። እናም ኦህዴድ የሞት መንገድ መሆኑንን በሚገነዘበው መንገድ “ለመርህ” ብቻ ሲል ከተቃቃረው ህወሓት ጋር አብሮ ይቀጥላል ወይስ በግልጽ ኢህአዴግን በመሰናበት ወደ ህዝብ ይቀላቀላል (ራሱን ይችላል)?

የጎልጉል ዘጋቢ እንደሚለው ህወሓት የነከሰውን ጥርስ  መቼም ሰላማያላቅቀው ኦህዴድ ዙሩን ማክረር እንደሚጠበቅበት አምነው የመጣውን ለመቀበል የተዘጋጁ አሉ። በተመሳሳይ ደግሞ ሁኔታው ሂደት በመሆኑ ከማክረር በስልት መሥራቱ እንደሚበጅ የሚናገሩም አሉ። ይህ ክፍተት ድርጅቱን ለመሰነጠቅ ለታሰበው ሤራ የሚያመች ደረጃ ላይ ነው ብለው ግን አያምኑም። ከዚህ በላይ የሚያሰጋው ግን የኃይል ጉዳይ እንዳይነሳ ነው። አቶ አለማየሁ አቶምሳን በአጭሩ ያስቀረው መርዝም አለ!!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column, opdo, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    March 2, 2018 07:15 pm at 7:15 pm

    በሰንጠቅ??? ሚኖ ባኪህ?? ጋብሬል ሲንጢቅ!! ያርጋል!

    Reply
    • Petros says

      March 4, 2018 12:04 am at 12:04 am

      idiot!

      Reply
    • ወንድወሰን says

      March 5, 2018 11:51 pm at 11:51 pm

      ሀለቃ በትኔ፣
      እውነተኛ ቀለምሽ እየተንጠባጠበ ነው!

      Reply
  2. Eyerus says

    March 2, 2018 08:03 pm at 8:03 pm

    እኔን የሚገርመኝ
    ክፉዎች በክፋታቸው
    የተለያየ ስልት እያወጡ
    የመግደል ሥራቸውን
    በወታደራዊ ኃይል
    የበለጠ ለመቀጠል ሲዘጋጁ!

    ኦሆዴዶች ሕዝባቸውን ለማትረፍ
    የተለያየ ስልት እየነደፉ ሳለ
    የመሪዎችን ስም ማጠልሸት
    ዋሾዎች ሥራቸውን ጀመሩ በሃሰት!

    ብአዴን ምን ነካው
    የመረጠው ዝም ማለት?
    የደመቀ ባህሪ ተጋባበት?
    ወይስ እንዳይናገር የጠ/ሚኒስቴርነት ጉርሻ ቃል ተገባለ?
    አሁንም ምርጫቸው ከሆነ አሻንጉሊነት?
    ይብላኝላቸው ስልጣኑ በሕዝብ እጅ የገባ እለት

    ሕዋት ትግራይ እናንተስ መቸ ይሆን አደብ የምትገዙት?
    እየሆነ ካለው ሁኔታስ መቼ ይሆን የምትማሩት?
    ሁልጊዜ ያለእኛ ስለማይሆን ተውን እንቀጥለበት?
    እያላችሁን ነው እኮ በምድሪቱ ላይ እኛ ብቻ እንንገሥበት!
    ተወስኗልና እኛ ለመግደል ሌላው ለመሞት!

    የትግራይ ሕዝብ ሚናስ በዚህ የሞት የሽረት ወቅት ምን ሊሆን ይገባው ነበር?
    ዝምታ ወይስ የልጆቹን አውሬነት መቃዎም??? ምርጫ ሊኖርህ ይገባል እኮ ! ኧረ መቐለ፣ ማይጨው፣ እንደርታ፣ አገው፣ አጋሜ ወዘተ አስተውል??

    Reply
  3. አለም says

    March 2, 2018 10:04 pm at 10:04 pm

    ጎልጉል፣
    ጉዳዩ ያለው የኦሮሞና የአማራ ቄሮ ጋ ነው። ሕዝብ ተነስቷል፤ ትግሉ እየተጧጧፈ ነው። ህወሓት ያንን ማብረድ እንደማይቻለው አውቆታል። መቀጠል ያለበትና መቋረጥ የለለበት ለዚህ ነው። መሪ የሚወጣውና እነ ለማ ብርታት የሚያገኙት ከኋላቸው ሕዝብ ሲነሳ ብቻ ነው። ህወሓት ለማወናበድ ይሞክራል፤ ትግሉ ከቀጠለ ግን ተስፋ የለውም። በነገራችን ላይ ውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ሌላ ወሬና ውዥንብር ትቶ ውስጥ ባሉት ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ ለዓለም ማስታወቅ ይኖርበታል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule