• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወርቅነህ አሜሪካኖችን “ምረጡኝ፤ አስመርጡኝ” ያለበት የጠ/ሚ ምርጫ ተውኔት ይፋ ሆነ

February 21, 2018 11:16 pm by Editor Leave a Comment

  • እነ ለማ የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው – ወርቅነህ

ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ለአሜሪካኖች “እኔ እንድመረጥ ድጋፍና ጫና ብታደርጉ የናንተን ፍላጎት ለማሳካት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነኝ” በማለት አሜሪካኖችን ሲወተውት እንደነበር ታወቀ። እርሱን እንዲመርጡ ድጋፍ ለመጠየቅ መነሻ አድርጎ ያቀረበው ሃሳብ “እነ ለማ ‹ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ› ቢሉም የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው፤ ከአማራው ጠቅላይ ሚኒስትር ቢመደብ ወደ አማራ ማድላቱ አይቀርም፤ ከሁለቱም ያልሆነ እንደእኔ ያለ ሰው መመረጥ አለበት” የሚል ነው።

በግልጽ በማይነገር የጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህንን ያለው ሰሞኑን በአሜሪካ ቆይታው ከፖሊሲ አውጪዎችና የዓለምአቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ጋር ተገኝቶ ስለወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታና መፍትሄ ማብራሪያ ሲሰጥ ነው። ወርቅነህ በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደር ከሆኑት ኒኪ ሄይሊ እንዲሁም ከሌሎች የአሜሪካ ፖሊሲ አማካሪዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሃላፊዎችና በፖለቲካው መስመር ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር መገናኘቱ በይፋ የተዘገበ ነው።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የጎልጉል የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ወርቅነህ “ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ምረጡኝ፣ አስመርጡኝ፣ እኔ ነኝ መካከለኛ ሰው … አሜሪካ የምትፈልገውን ጥቅም ሁሉ አስከብራለሁ” በማለት በገሃድ ሲናገር ለሰሚዎቹ አስገራሚ ከመሆን አልፎ አስደንጋጭም ነበር። እጅግ ውድ የሆነውን ሮሌክስ ሰዓቱን እያሻሸ የአስመርጡኝ ዘመቻውን ለማካሄድ የሞክረው ወርቅነህ “እኛ ማንም እንዲመረጥ የምናደርገው ነገር የለም” ተብሎ ከተማመነባቸው ጌቶቹ ሲነገረው በትኩሱ አልቦት ነበር።

“ኦሮሞ ነኝ እያለ ነገር ግን ኦህዴድን ወክሎ ይህንን መናገሩ አስገራሚ ነው” ያሉት የመረጃ አቀባይ “እኔ ነኝ መካከለኛው ሰው” በሚለው ንግግሩ ትግሬ መሆኑንንም ማረጋገጫ እንደሰጠ የገባው አይመስልም። ይህ ለሥልጣን ምን ያህል ፍላጎት እንዳለው የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን ገና ካሁኑ እንዴት ጭፍን አምባገነን እንደሆነ ጠቋሚ ነው ብለዋል። አያይዘውም “ይህ ጥሩ የዲክታተር ምሳሌ ነው” ሲሉም ተሳልቀውበታል።

በኦህዴድ እየማለ፣ ኦህዴድን የጽንፍ ፖለቲካ አራማጅ አድርጎ ሲሸቅጥ የነበረው ወርቅነህ ይህንን እንዲያደርግ ከህወሃት ፈቃድ ስለማግኘቱ የታወቀ ነገር የለም። ይሁን እንጂ አንዳንድ የህወሃት የማህበራዊ ገጽ አራጋቢዎችና ተላላኪዎች ወርቅነህ እንዲመራ ምኞታቸውን፣ ማስታወቂያቸውን፣ ተልዕኳቸውን በስፋት እያሰሙ ነው። በነካ እጃቸው ኒኪ ሄሊን “የትራምፕ ውሽማ/ዕቁባት” በማለት ሲሳደቡ፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካንን አምባሳደር “ጂኦግራፊ ተማር በሉት” የሚል ስድብ ሲያሰራጩ ቆይተዋል።

“ከሻሸመኔ ድንገት ተስፈንጥሮ ፖሊስ የሆነው ወርቅነህ ስሙን የቀየረ፣ ብሄሩ ኦሮሞ ያልሆነ በሚል ተቃውሞ ያልተለየው፣ የበርካታ ንጹሃን ደም እጁ ላይ ያለበት የህወሃት ኮማንዶ ነው። በኦሮሞ ስም የተለያዩ ሃላፊነቶች ላይ ሲደንስና ደም ሲያፈስ ኖሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለመሆን በቃ፣ ይህንን ያህል የሚነግድበትን ድርጅት ‘ጽንፈኛ’ ሲል ቆመረበት” በማለት ለጎልጉል መረጃ ያቀበሉ እንዳሉት እነ ለማ መገርሳም ሆኑ ድርጅቱ ይህንን አንስተው ማብራሪያ ቢጠይቁ ወይም በመጠየቅ ተጨባጭ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ ድጋፍ ሊያደርጉ ዝግጁ ናቸው።

ራሱን “ብልጣ ብልጥ” አድርጎ የወሰደው ሮሌክስ አድራጊው “ሸበላው”ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”፤ በአቀራረቡ ሲሳቅበትና የማጣፊያ መልስ ሲሰጠው ጉዳዩን “ክፍተቱን የመሙላት ነው” ሲል እራሱን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ መገደዱን፣ እሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሆን የኦሮሞ ጉዳይ ምላሽ እንደሚያገኝ፣ ሰላም እንደሚፈጠርና አሜሪካም የምትፈልገው ጥቅሟ ያለአንዳች ገደብ እንደሚከበር ያለእፍረት በገሃድ ደስኩሯል። እንዲህ ዓይነቱን ድፍረት የሰጠው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ከመለስ ሞት በኋላ በዓለምአቀፍ ግንኙነት ላይ የኢትዮጵያ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ቀንሷል” በማለት በቅርቡ በአገር ውስጥ በሰጠው መግለጫ ላይ ራሱን “አዲሱ መለስ” አድርጎ ለማቅረብ ከመሞከሩ ጋር የሚያገናኙትም አሉ።

በ“ትንታኔው” ሲደመሙ የነበሩት አድማጮች ወርቅነህ በዲፕሎማሲው መስክ በገሃድ የሚጠየቁና ከመጋረጃ በስተኋላ የሚደረጉ ጉዳዮችን በቅጡ ያልተረዳ እንጭጭ መሆኑን ከመታዘብ አልፈው የአስተሳሰቡን ኮሳሳነት በውል ለመረዳት አጋጣሚ ሆኖላቸዋል። በምክትል ሊቀመንበርነት የሚመራውን ኦህዴድ “ጽንፈኛ” ብሎ ከፈረጀ በኋላ ራሱን ክፍተት መሙያ ማድረጉ በአሜሪካውያኑ ዘንድ ከማስገረሙም በላይ አስቂኝ ተውኔት ሆኖ መሰንበቱ ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

(የመግቢያ ፎቶ፤ በስተግራ ካሣ ተክለብርሃን ቀጥሎ ወርቃማ ሰዓቱ የሚታየው ወርቅነህ ከርሱ ቀጥሎ (ተሸፍኗል) በአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል ዳይሬክተር ፒተር ፓም፤ የአትላንቲክ ካውንስል በጠራው ስብሰባ ላይ ወርቅነህ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ፊት ስለ ህወሓት “ቅዱስነት” ሲናገር፤ በቀኝ በኩል ያለው ወርቅነህ “ኧረ ባካችሁ ምረጡኝ ወይም አስመርጡኝ” በሚል መልኩ የአሜሪካዋን አምባሳደር ኒኪ ሄይሊን ሲለምን)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, opdo, prime minister, tplf, workineh

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule