• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወርቅነህ አሜሪካኖችን “ምረጡኝ፤ አስመርጡኝ” ያለበት የጠ/ሚ ምርጫ ተውኔት ይፋ ሆነ

February 21, 2018 11:16 pm by Editor Leave a Comment

  • እነ ለማ የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው – ወርቅነህ

ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ለአሜሪካኖች “እኔ እንድመረጥ ድጋፍና ጫና ብታደርጉ የናንተን ፍላጎት ለማሳካት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነኝ” በማለት አሜሪካኖችን ሲወተውት እንደነበር ታወቀ። እርሱን እንዲመርጡ ድጋፍ ለመጠየቅ መነሻ አድርጎ ያቀረበው ሃሳብ “እነ ለማ ‹ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ› ቢሉም የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው፤ ከአማራው ጠቅላይ ሚኒስትር ቢመደብ ወደ አማራ ማድላቱ አይቀርም፤ ከሁለቱም ያልሆነ እንደእኔ ያለ ሰው መመረጥ አለበት” የሚል ነው።

በግልጽ በማይነገር የጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህንን ያለው ሰሞኑን በአሜሪካ ቆይታው ከፖሊሲ አውጪዎችና የዓለምአቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ጋር ተገኝቶ ስለወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታና መፍትሄ ማብራሪያ ሲሰጥ ነው። ወርቅነህ በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደር ከሆኑት ኒኪ ሄይሊ እንዲሁም ከሌሎች የአሜሪካ ፖሊሲ አማካሪዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሃላፊዎችና በፖለቲካው መስመር ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር መገናኘቱ በይፋ የተዘገበ ነው።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የጎልጉል የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ወርቅነህ “ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ምረጡኝ፣ አስመርጡኝ፣ እኔ ነኝ መካከለኛ ሰው … አሜሪካ የምትፈልገውን ጥቅም ሁሉ አስከብራለሁ” በማለት በገሃድ ሲናገር ለሰሚዎቹ አስገራሚ ከመሆን አልፎ አስደንጋጭም ነበር። እጅግ ውድ የሆነውን ሮሌክስ ሰዓቱን እያሻሸ የአስመርጡኝ ዘመቻውን ለማካሄድ የሞክረው ወርቅነህ “እኛ ማንም እንዲመረጥ የምናደርገው ነገር የለም” ተብሎ ከተማመነባቸው ጌቶቹ ሲነገረው በትኩሱ አልቦት ነበር።

“ኦሮሞ ነኝ እያለ ነገር ግን ኦህዴድን ወክሎ ይህንን መናገሩ አስገራሚ ነው” ያሉት የመረጃ አቀባይ “እኔ ነኝ መካከለኛው ሰው” በሚለው ንግግሩ ትግሬ መሆኑንንም ማረጋገጫ እንደሰጠ የገባው አይመስልም። ይህ ለሥልጣን ምን ያህል ፍላጎት እንዳለው የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን ገና ካሁኑ እንዴት ጭፍን አምባገነን እንደሆነ ጠቋሚ ነው ብለዋል። አያይዘውም “ይህ ጥሩ የዲክታተር ምሳሌ ነው” ሲሉም ተሳልቀውበታል።

በኦህዴድ እየማለ፣ ኦህዴድን የጽንፍ ፖለቲካ አራማጅ አድርጎ ሲሸቅጥ የነበረው ወርቅነህ ይህንን እንዲያደርግ ከህወሃት ፈቃድ ስለማግኘቱ የታወቀ ነገር የለም። ይሁን እንጂ አንዳንድ የህወሃት የማህበራዊ ገጽ አራጋቢዎችና ተላላኪዎች ወርቅነህ እንዲመራ ምኞታቸውን፣ ማስታወቂያቸውን፣ ተልዕኳቸውን በስፋት እያሰሙ ነው። በነካ እጃቸው ኒኪ ሄሊን “የትራምፕ ውሽማ/ዕቁባት” በማለት ሲሳደቡ፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካንን አምባሳደር “ጂኦግራፊ ተማር በሉት” የሚል ስድብ ሲያሰራጩ ቆይተዋል።

“ከሻሸመኔ ድንገት ተስፈንጥሮ ፖሊስ የሆነው ወርቅነህ ስሙን የቀየረ፣ ብሄሩ ኦሮሞ ያልሆነ በሚል ተቃውሞ ያልተለየው፣ የበርካታ ንጹሃን ደም እጁ ላይ ያለበት የህወሃት ኮማንዶ ነው። በኦሮሞ ስም የተለያዩ ሃላፊነቶች ላይ ሲደንስና ደም ሲያፈስ ኖሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለመሆን በቃ፣ ይህንን ያህል የሚነግድበትን ድርጅት ‘ጽንፈኛ’ ሲል ቆመረበት” በማለት ለጎልጉል መረጃ ያቀበሉ እንዳሉት እነ ለማ መገርሳም ሆኑ ድርጅቱ ይህንን አንስተው ማብራሪያ ቢጠይቁ ወይም በመጠየቅ ተጨባጭ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ ድጋፍ ሊያደርጉ ዝግጁ ናቸው።

ራሱን “ብልጣ ብልጥ” አድርጎ የወሰደው ሮሌክስ አድራጊው “ሸበላው”ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”፤ በአቀራረቡ ሲሳቅበትና የማጣፊያ መልስ ሲሰጠው ጉዳዩን “ክፍተቱን የመሙላት ነው” ሲል እራሱን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ መገደዱን፣ እሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሆን የኦሮሞ ጉዳይ ምላሽ እንደሚያገኝ፣ ሰላም እንደሚፈጠርና አሜሪካም የምትፈልገው ጥቅሟ ያለአንዳች ገደብ እንደሚከበር ያለእፍረት በገሃድ ደስኩሯል። እንዲህ ዓይነቱን ድፍረት የሰጠው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ከመለስ ሞት በኋላ በዓለምአቀፍ ግንኙነት ላይ የኢትዮጵያ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ቀንሷል” በማለት በቅርቡ በአገር ውስጥ በሰጠው መግለጫ ላይ ራሱን “አዲሱ መለስ” አድርጎ ለማቅረብ ከመሞከሩ ጋር የሚያገናኙትም አሉ።

በ“ትንታኔው” ሲደመሙ የነበሩት አድማጮች ወርቅነህ በዲፕሎማሲው መስክ በገሃድ የሚጠየቁና ከመጋረጃ በስተኋላ የሚደረጉ ጉዳዮችን በቅጡ ያልተረዳ እንጭጭ መሆኑን ከመታዘብ አልፈው የአስተሳሰቡን ኮሳሳነት በውል ለመረዳት አጋጣሚ ሆኖላቸዋል። በምክትል ሊቀመንበርነት የሚመራውን ኦህዴድ “ጽንፈኛ” ብሎ ከፈረጀ በኋላ ራሱን ክፍተት መሙያ ማድረጉ በአሜሪካውያኑ ዘንድ ከማስገረሙም በላይ አስቂኝ ተውኔት ሆኖ መሰንበቱ ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

(የመግቢያ ፎቶ፤ በስተግራ ካሣ ተክለብርሃን ቀጥሎ ወርቃማ ሰዓቱ የሚታየው ወርቅነህ ከርሱ ቀጥሎ (ተሸፍኗል) በአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል ዳይሬክተር ፒተር ፓም፤ የአትላንቲክ ካውንስል በጠራው ስብሰባ ላይ ወርቅነህ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ፊት ስለ ህወሓት “ቅዱስነት” ሲናገር፤ በቀኝ በኩል ያለው ወርቅነህ “ኧረ ባካችሁ ምረጡኝ ወይም አስመርጡኝ” በሚል መልኩ የአሜሪካዋን አምባሳደር ኒኪ ሄይሊን ሲለምን)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, opdo, prime minister, tplf, workineh

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule