• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወርቅነህ አሜሪካኖችን “ምረጡኝ፤ አስመርጡኝ” ያለበት የጠ/ሚ ምርጫ ተውኔት ይፋ ሆነ

February 21, 2018 11:16 pm by Editor Leave a Comment

  • እነ ለማ የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው – ወርቅነህ

ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ለአሜሪካኖች “እኔ እንድመረጥ ድጋፍና ጫና ብታደርጉ የናንተን ፍላጎት ለማሳካት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነኝ” በማለት አሜሪካኖችን ሲወተውት እንደነበር ታወቀ። እርሱን እንዲመርጡ ድጋፍ ለመጠየቅ መነሻ አድርጎ ያቀረበው ሃሳብ “እነ ለማ ‹ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ› ቢሉም የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው፤ ከአማራው ጠቅላይ ሚኒስትር ቢመደብ ወደ አማራ ማድላቱ አይቀርም፤ ከሁለቱም ያልሆነ እንደእኔ ያለ ሰው መመረጥ አለበት” የሚል ነው።

በግልጽ በማይነገር የጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህንን ያለው ሰሞኑን በአሜሪካ ቆይታው ከፖሊሲ አውጪዎችና የዓለምአቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ጋር ተገኝቶ ስለወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታና መፍትሄ ማብራሪያ ሲሰጥ ነው። ወርቅነህ በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደር ከሆኑት ኒኪ ሄይሊ እንዲሁም ከሌሎች የአሜሪካ ፖሊሲ አማካሪዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሃላፊዎችና በፖለቲካው መስመር ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር መገናኘቱ በይፋ የተዘገበ ነው።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የጎልጉል የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ወርቅነህ “ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ምረጡኝ፣ አስመርጡኝ፣ እኔ ነኝ መካከለኛ ሰው … አሜሪካ የምትፈልገውን ጥቅም ሁሉ አስከብራለሁ” በማለት በገሃድ ሲናገር ለሰሚዎቹ አስገራሚ ከመሆን አልፎ አስደንጋጭም ነበር። እጅግ ውድ የሆነውን ሮሌክስ ሰዓቱን እያሻሸ የአስመርጡኝ ዘመቻውን ለማካሄድ የሞክረው ወርቅነህ “እኛ ማንም እንዲመረጥ የምናደርገው ነገር የለም” ተብሎ ከተማመነባቸው ጌቶቹ ሲነገረው በትኩሱ አልቦት ነበር።

“ኦሮሞ ነኝ እያለ ነገር ግን ኦህዴድን ወክሎ ይህንን መናገሩ አስገራሚ ነው” ያሉት የመረጃ አቀባይ “እኔ ነኝ መካከለኛው ሰው” በሚለው ንግግሩ ትግሬ መሆኑንንም ማረጋገጫ እንደሰጠ የገባው አይመስልም። ይህ ለሥልጣን ምን ያህል ፍላጎት እንዳለው የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን ገና ካሁኑ እንዴት ጭፍን አምባገነን እንደሆነ ጠቋሚ ነው ብለዋል። አያይዘውም “ይህ ጥሩ የዲክታተር ምሳሌ ነው” ሲሉም ተሳልቀውበታል።

በኦህዴድ እየማለ፣ ኦህዴድን የጽንፍ ፖለቲካ አራማጅ አድርጎ ሲሸቅጥ የነበረው ወርቅነህ ይህንን እንዲያደርግ ከህወሃት ፈቃድ ስለማግኘቱ የታወቀ ነገር የለም። ይሁን እንጂ አንዳንድ የህወሃት የማህበራዊ ገጽ አራጋቢዎችና ተላላኪዎች ወርቅነህ እንዲመራ ምኞታቸውን፣ ማስታወቂያቸውን፣ ተልዕኳቸውን በስፋት እያሰሙ ነው። በነካ እጃቸው ኒኪ ሄሊን “የትራምፕ ውሽማ/ዕቁባት” በማለት ሲሳደቡ፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካንን አምባሳደር “ጂኦግራፊ ተማር በሉት” የሚል ስድብ ሲያሰራጩ ቆይተዋል።

“ከሻሸመኔ ድንገት ተስፈንጥሮ ፖሊስ የሆነው ወርቅነህ ስሙን የቀየረ፣ ብሄሩ ኦሮሞ ያልሆነ በሚል ተቃውሞ ያልተለየው፣ የበርካታ ንጹሃን ደም እጁ ላይ ያለበት የህወሃት ኮማንዶ ነው። በኦሮሞ ስም የተለያዩ ሃላፊነቶች ላይ ሲደንስና ደም ሲያፈስ ኖሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለመሆን በቃ፣ ይህንን ያህል የሚነግድበትን ድርጅት ‘ጽንፈኛ’ ሲል ቆመረበት” በማለት ለጎልጉል መረጃ ያቀበሉ እንዳሉት እነ ለማ መገርሳም ሆኑ ድርጅቱ ይህንን አንስተው ማብራሪያ ቢጠይቁ ወይም በመጠየቅ ተጨባጭ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ ድጋፍ ሊያደርጉ ዝግጁ ናቸው።

ራሱን “ብልጣ ብልጥ” አድርጎ የወሰደው ሮሌክስ አድራጊው “ሸበላው”ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”፤ በአቀራረቡ ሲሳቅበትና የማጣፊያ መልስ ሲሰጠው ጉዳዩን “ክፍተቱን የመሙላት ነው” ሲል እራሱን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ መገደዱን፣ እሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሆን የኦሮሞ ጉዳይ ምላሽ እንደሚያገኝ፣ ሰላም እንደሚፈጠርና አሜሪካም የምትፈልገው ጥቅሟ ያለአንዳች ገደብ እንደሚከበር ያለእፍረት በገሃድ ደስኩሯል። እንዲህ ዓይነቱን ድፍረት የሰጠው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ከመለስ ሞት በኋላ በዓለምአቀፍ ግንኙነት ላይ የኢትዮጵያ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ቀንሷል” በማለት በቅርቡ በአገር ውስጥ በሰጠው መግለጫ ላይ ራሱን “አዲሱ መለስ” አድርጎ ለማቅረብ ከመሞከሩ ጋር የሚያገናኙትም አሉ።

በ“ትንታኔው” ሲደመሙ የነበሩት አድማጮች ወርቅነህ በዲፕሎማሲው መስክ በገሃድ የሚጠየቁና ከመጋረጃ በስተኋላ የሚደረጉ ጉዳዮችን በቅጡ ያልተረዳ እንጭጭ መሆኑን ከመታዘብ አልፈው የአስተሳሰቡን ኮሳሳነት በውል ለመረዳት አጋጣሚ ሆኖላቸዋል። በምክትል ሊቀመንበርነት የሚመራውን ኦህዴድ “ጽንፈኛ” ብሎ ከፈረጀ በኋላ ራሱን ክፍተት መሙያ ማድረጉ በአሜሪካውያኑ ዘንድ ከማስገረሙም በላይ አስቂኝ ተውኔት ሆኖ መሰንበቱ ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

(የመግቢያ ፎቶ፤ በስተግራ ካሣ ተክለብርሃን ቀጥሎ ወርቃማ ሰዓቱ የሚታየው ወርቅነህ ከርሱ ቀጥሎ (ተሸፍኗል) በአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል ዳይሬክተር ፒተር ፓም፤ የአትላንቲክ ካውንስል በጠራው ስብሰባ ላይ ወርቅነህ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ፊት ስለ ህወሓት “ቅዱስነት” ሲናገር፤ በቀኝ በኩል ያለው ወርቅነህ “ኧረ ባካችሁ ምረጡኝ ወይም አስመርጡኝ” በሚል መልኩ የአሜሪካዋን አምባሳደር ኒኪ ሄይሊን ሲለምን)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, opdo, prime minister, tplf, workineh

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule