• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወርቅነህ አሜሪካኖችን “ምረጡኝ፤ አስመርጡኝ” ያለበት የጠ/ሚ ምርጫ ተውኔት ይፋ ሆነ

February 21, 2018 11:16 pm by Editor Leave a Comment

  • እነ ለማ የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው – ወርቅነህ

ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ለአሜሪካኖች “እኔ እንድመረጥ ድጋፍና ጫና ብታደርጉ የናንተን ፍላጎት ለማሳካት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነኝ” በማለት አሜሪካኖችን ሲወተውት እንደነበር ታወቀ። እርሱን እንዲመርጡ ድጋፍ ለመጠየቅ መነሻ አድርጎ ያቀረበው ሃሳብ “እነ ለማ ‹ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ› ቢሉም የሚያራምዱት የጽንፍ ፖለቲካ ነው፤ ከአማራው ጠቅላይ ሚኒስትር ቢመደብ ወደ አማራ ማድላቱ አይቀርም፤ ከሁለቱም ያልሆነ እንደእኔ ያለ ሰው መመረጥ አለበት” የሚል ነው።

በግልጽ በማይነገር የጄኔራልነት ማዕረግ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ይህንን ያለው ሰሞኑን በአሜሪካ ቆይታው ከፖሊሲ አውጪዎችና የዓለምአቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ጋር ተገኝቶ ስለወቅታዊ የአገሪቱ ሁኔታና መፍትሄ ማብራሪያ ሲሰጥ ነው። ወርቅነህ በተባበሩት መንግሥታት የአሜሪካ አምባሳደር ከሆኑት ኒኪ ሄይሊ እንዲሁም ከሌሎች የአሜሪካ ፖሊሲ አማካሪዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሃላፊዎችና በፖለቲካው መስመር ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር መገናኘቱ በይፋ የተዘገበ ነው።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የጎልጉል የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ወርቅነህ “ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ምረጡኝ፣ አስመርጡኝ፣ እኔ ነኝ መካከለኛ ሰው … አሜሪካ የምትፈልገውን ጥቅም ሁሉ አስከብራለሁ” በማለት በገሃድ ሲናገር ለሰሚዎቹ አስገራሚ ከመሆን አልፎ አስደንጋጭም ነበር። እጅግ ውድ የሆነውን ሮሌክስ ሰዓቱን እያሻሸ የአስመርጡኝ ዘመቻውን ለማካሄድ የሞክረው ወርቅነህ “እኛ ማንም እንዲመረጥ የምናደርገው ነገር የለም” ተብሎ ከተማመነባቸው ጌቶቹ ሲነገረው በትኩሱ አልቦት ነበር።

“ኦሮሞ ነኝ እያለ ነገር ግን ኦህዴድን ወክሎ ይህንን መናገሩ አስገራሚ ነው” ያሉት የመረጃ አቀባይ “እኔ ነኝ መካከለኛው ሰው” በሚለው ንግግሩ ትግሬ መሆኑንንም ማረጋገጫ እንደሰጠ የገባው አይመስልም። ይህ ለሥልጣን ምን ያህል ፍላጎት እንዳለው የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን ገና ካሁኑ እንዴት ጭፍን አምባገነን እንደሆነ ጠቋሚ ነው ብለዋል። አያይዘውም “ይህ ጥሩ የዲክታተር ምሳሌ ነው” ሲሉም ተሳልቀውበታል።

በኦህዴድ እየማለ፣ ኦህዴድን የጽንፍ ፖለቲካ አራማጅ አድርጎ ሲሸቅጥ የነበረው ወርቅነህ ይህንን እንዲያደርግ ከህወሃት ፈቃድ ስለማግኘቱ የታወቀ ነገር የለም። ይሁን እንጂ አንዳንድ የህወሃት የማህበራዊ ገጽ አራጋቢዎችና ተላላኪዎች ወርቅነህ እንዲመራ ምኞታቸውን፣ ማስታወቂያቸውን፣ ተልዕኳቸውን በስፋት እያሰሙ ነው። በነካ እጃቸው ኒኪ ሄሊን “የትራምፕ ውሽማ/ዕቁባት” በማለት ሲሳደቡ፤ በኢትዮጵያ የአሜሪካንን አምባሳደር “ጂኦግራፊ ተማር በሉት” የሚል ስድብ ሲያሰራጩ ቆይተዋል።

“ከሻሸመኔ ድንገት ተስፈንጥሮ ፖሊስ የሆነው ወርቅነህ ስሙን የቀየረ፣ ብሄሩ ኦሮሞ ያልሆነ በሚል ተቃውሞ ያልተለየው፣ የበርካታ ንጹሃን ደም እጁ ላይ ያለበት የህወሃት ኮማንዶ ነው። በኦሮሞ ስም የተለያዩ ሃላፊነቶች ላይ ሲደንስና ደም ሲያፈስ ኖሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለመሆን በቃ፣ ይህንን ያህል የሚነግድበትን ድርጅት ‘ጽንፈኛ’ ሲል ቆመረበት” በማለት ለጎልጉል መረጃ ያቀበሉ እንዳሉት እነ ለማ መገርሳም ሆኑ ድርጅቱ ይህንን አንስተው ማብራሪያ ቢጠይቁ ወይም በመጠየቅ ተጨባጭ መረጃ ማግኘት ከፈለጉ ድጋፍ ሊያደርጉ ዝግጁ ናቸው።

ራሱን “ብልጣ ብልጥ” አድርጎ የወሰደው ሮሌክስ አድራጊው “ሸበላው”ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”፤ በአቀራረቡ ሲሳቅበትና የማጣፊያ መልስ ሲሰጠው ጉዳዩን “ክፍተቱን የመሙላት ነው” ሲል እራሱን ብቸኛ አማራጭ ለማድረግ መገደዱን፣ እሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሆን የኦሮሞ ጉዳይ ምላሽ እንደሚያገኝ፣ ሰላም እንደሚፈጠርና አሜሪካም የምትፈልገው ጥቅሟ ያለአንዳች ገደብ እንደሚከበር ያለእፍረት በገሃድ ደስኩሯል። እንዲህ ዓይነቱን ድፍረት የሰጠው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ “ከመለስ ሞት በኋላ በዓለምአቀፍ ግንኙነት ላይ የኢትዮጵያ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ቀንሷል” በማለት በቅርቡ በአገር ውስጥ በሰጠው መግለጫ ላይ ራሱን “አዲሱ መለስ” አድርጎ ለማቅረብ ከመሞከሩ ጋር የሚያገናኙትም አሉ።

በ“ትንታኔው” ሲደመሙ የነበሩት አድማጮች ወርቅነህ በዲፕሎማሲው መስክ በገሃድ የሚጠየቁና ከመጋረጃ በስተኋላ የሚደረጉ ጉዳዮችን በቅጡ ያልተረዳ እንጭጭ መሆኑን ከመታዘብ አልፈው የአስተሳሰቡን ኮሳሳነት በውል ለመረዳት አጋጣሚ ሆኖላቸዋል። በምክትል ሊቀመንበርነት የሚመራውን ኦህዴድ “ጽንፈኛ” ብሎ ከፈረጀ በኋላ ራሱን ክፍተት መሙያ ማድረጉ በአሜሪካውያኑ ዘንድ ከማስገረሙም በላይ አስቂኝ ተውኔት ሆኖ መሰንበቱ ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

(የመግቢያ ፎቶ፤ በስተግራ ካሣ ተክለብርሃን ቀጥሎ ወርቃማ ሰዓቱ የሚታየው ወርቅነህ ከርሱ ቀጥሎ (ተሸፍኗል) በአትላንቲክ ካውንስል የአፍሪካ ማዕከል ዳይሬክተር ፒተር ፓም፤ የአትላንቲክ ካውንስል በጠራው ስብሰባ ላይ ወርቅነህ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ፊት ስለ ህወሓት “ቅዱስነት” ሲናገር፤ በቀኝ በኩል ያለው ወርቅነህ “ኧረ ባካችሁ ምረጡኝ ወይም አስመርጡኝ” በሚል መልኩ የአሜሪካዋን አምባሳደር ኒኪ ሄይሊን ሲለምን)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: News Tagged With: eprdf, Full Width Top, Middle Column, opdo, prime minister, tplf, workineh

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule