• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

H.R. 128 ያለ ተቃውሞ አልፏል!

April 10, 2018 11:08 pm by Editor 2 Comments

የሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩና ሁሉን ዓቀፍ መንግሥት በኢትዮጵያ እንዲቋቋም ለማስቻል በአሜሪካ የእንደራሴዎች ምክርቤት የተዘጋጀው ረቂቅ ሕግ ያለአንዳች ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ኤፕሪል 10፤2018ዓም ጸድቋል።

ህወሓት እጅግ ከፍተኛ የውትወታ ገንዘብ ያፈሰሰበትና በርካታ የፖለቲካ ሥራ የሠራበት ረቂቅ በምክርቤቱ በሚገኙ 108 እንደራሴዎች ስፖንሰር ያደረጉት ሲሆን የሁለቱም ማለትም የዴሞክራትና የሪፑብሊካን እንደራሴዎች በጣምራነት የደገፉት ረቂቅ ነበር።

በዋሽንግቶን ዲሲ በ“አምባሳደርነት” ሹመት የኢህአዴግ ተወካይ ሆኖ የተቀመጠው ካሣ ተክለብርሃን ለምክርቤቱ ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ ደብዳቤ ልኮ እንደነበር H.R. 128 ለኢትዮጵያ በፌስቡክ ገጹ ላይ ባተመው የደብዳቤው ፎቶ አስታውቋል።

በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኅብረት ያደረጉት እንቅስቃሴ አንዱ የድሉ አካል እንደሆነ ተነግሯል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከዚህ በፊት ይህንኑ የህወሓት ውትወታ አስመልክቶ ሲዘግብ፤ “ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ በርካታ ሙከራዎችን ህወሓት ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን – ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል።ይህንን ረቂቅ ህግ ገና ከጅምሩ የፈራው ህወሓት ለወትዋቾች (ሎቢይስቶች) በጀት መድቦ መንቀሳቀስ ከጀመረ አንድ ዓመት አልፎታል። በዋሽንግቶን ዲሲ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ተጠሪ የነበረው ግርማ ብሩ SGR Government Relations ከተባለ የወትዋቾች ድርጅት ጋር በተፈራረመው ሰነድ ላይ በግልጽ እንደተመለከተው ለዚህ የውትወታ ሥራ ድርጅቱ (SGR) በወር 150ሺህ ዶላር፤ በጥቅሉ 1.8 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሎት ረቂቅ ሕጉን የማክሸፍ ዘመቻ እንዲሠራ ስምምነት ተደርጓል” በማለት በመረጃ የተደገፈ ሪፖርት ማቅረቡ ይታወሳል።

ይህ በምክርቤቱ የፀደቀው ሕግ በኢትዮጵያ ያለውን ግድያ፣ ግፍ፣ እስራት፣ ሥቅየት፣ ወዘተ ከመዘርዘር ባሻገር አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን የህወሓት/ኢህአዴግን አገዛዝ የሚከተሉትን ተግባራት እንዲፈጽም ውሳኔ የተላለፈበት ነው፤

  • የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲያነሳ፤
  • የፀጥታ ኃይላት ከመጠን በላይ ኃይል መጠቀማቸውን እንዲያቆሙ፤
  • በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከመጠን በላይ ኃይል በመጠቀም የተፈጸሙ ግድያዎች እንዲመረመሩ፤
  • ሕገመንግሥታዊ መብቶቻቸውን በተግባር በማዋላቸው የታሰሩት የፖለቲካ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ ተቃዋሚዎች፣ … ከእሥር እንዲለቀቁ፤
  • በሰላም የመሰባሰብ መብት እንዲከበር እና የፕሬስ ነጻነት ዋስትና እንዲሰጠው፤
  • የልማት ስትራቴጂውን በተመለከተ ከዜጎች ጋር ግልጽ ውይይት እንዲካሄድ፤
  • የተባበሩት መንግሥታት ራፖርተር በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ነጻ ምርመራ እንዲያደርግ እንዲፈቀድ፤
  • በሕጋዊነት በተመዘገቡ የተቃዋሚ ድርጅቶች የሚቀርቡ አቤቱታዎችንና ቅሬታዎችን በማዳመጥ መፍትሔ እንዲያገኙ እንዲደረግ፤
  • ሕገመንግሥታዊ መብቶቻቸውን ተጠቅመው ሃሳባቸውን በነጻነት በገለጹ ዜጎች ላይ ግድያ፣ ስቅየት፣ ግፍ፣ ወዘተ የፈጸሙ በሕግ እንዲጠየቁ፤
  • ነሐሴ 28፤ 2008ዓም ቂሊንጦ እስርቤት ላይ በመተኮስና በእሣት በማቃጠል፤ መስከረም 22፤ 2009 በኢሬቻ በዓል ላይ የሞቱትን እንዲሁም በሶማሊያ ክልል ለዓመታት ሲካሄድ የቆየውን ግድያ አስመልክቶ ምርመራ ተደርጎ ሪፖርት እንዲቀርብ የሚጠይቅ ነው።

ህወሓት/ኢህአዴግ የሚከተለውንና በተግባር አውሎ እየተጠቀመባቸው ያሉትን የአፋኝ ሕግጋት ስብስብ እንዲሰረዙ፤ እነዚህም የጸረ-ሽብር ሕጉ፤ የመያዶች ሕግ፣ ወዘተ የሚጠቀልል ነው።

በመጨረሻም ሕጉ፤

  1. አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ዕርዳታ የውጭ ጉዳይ (ስቴት ዲፓርትመት) መልሶ እንዲያጤነው፤
  2. የአሜሪካ ዓለምአቀፍ የልማት ኤጀንሲ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን ስትራቴጂዎችን እንዲነድፍ፤
  3. ስቴት ዲፓርትመንት ከአሜሪካው ገንዘብ ሚ/ር መ/ቤት ጋር በጥምረት በመሆን በኢትዮጵያውያን ላይ ግድያ፣ ስቅየት፣ እንግልትና ግፍ የፈጸሙ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች በዓለምአቀፍ ደረጃ በሚታወቁ ሕግጋት መሠረት አስፈላጊው ማዕቀብ እንዲጣልባቸውና በኃላፊነት እንዲጠየቁ በግልጽ አስቀምጧል፤

እነዚህንና ሌሎች ጠቃሚ አንቀጾችን ያካተተው ረቂቅ ሲጸድቅ በምክርቤቱ አዳራሽ ተገኝተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን በጭብጨባና በዕልልታ ደስታቸውን ገልጸዋል።

ቀጣዩ ጉዞ ይህ በምክርቤት የጸደቀ ሰነድ ወደ ሕግ መወሰኛ ምክርቤት (ሴኔት) በመሄድ ድምጽ ይሰጥበትና ካለፈ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፊርማቸውን በማኖር በሕግ መልኩ ወጥቶ ተግባራዊ እንዲደረግ ይታወጃል።

ህወሓት ይህንን ተግባር የሚያስፈጽሙለት እንደነ ሴናተር ኢንሆፍ ያሉ “ወዳጆች” እንዳሉት ሲናገር ቢሰማም ሕጉ አስቀድሞ የበርካታ ሴናተሮች ድጋፍ እንዳገኘ ይነገራል። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት 25 ሴናተሮች (18 ከዴሞክራቲክ፤ 7 ከሪፑብሊካን) S.Res.168ን ስፖንሰር አድርገዋል። ኢትዮጵያውንም H.Res. 128 ከጸደቀበት ሰዓት ጀምሮ በሴኔቱ የውሳኔ አሠራር ላይ የተጽዕኖ ሥራቸውን ማካሄድ ጀምረዋል።

(መግቢያ ፎቶ፤ ረቂቅ ሕጉ ያለተቃውሞ ሲያልፍ ሊቀመንበሩ መዶሻቸውን በመምታት ሲያረጋግጡ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, hr 128, kassa, lobby, Middle Column, sgr, sr 168, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    April 11, 2018 10:55 pm at 10:55 pm

    በናንተ ቤት፤ ሁሉም ነገር ተሳክቷል!!! መንግስቲ ግንቦት ሰባት!!! ቂቂቂ!!!ጨበርባሪዎች!!

    Reply
  2. Bekele tessema says

    April 14, 2018 11:11 pm at 11:11 pm

    አገር ወዳድ በጣም ወዳችሁሃለን ሴኔቱ ውሣኔ እንዲሠጥ የነዚ በግፍ የተገደሉት ነጳነት ፈላጊ ኢትዮጵያውያን አምላክ ይርዳችሁ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule