• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

H.R. 128 ያለ ተቃውሞ አልፏል!

April 10, 2018 11:08 pm by Editor 2 Comments

የሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩና ሁሉን ዓቀፍ መንግሥት በኢትዮጵያ እንዲቋቋም ለማስቻል በአሜሪካ የእንደራሴዎች ምክርቤት የተዘጋጀው ረቂቅ ሕግ ያለአንዳች ተቃውሞ በሙሉ ድምፅ ኤፕሪል 10፤2018ዓም ጸድቋል።

ህወሓት እጅግ ከፍተኛ የውትወታ ገንዘብ ያፈሰሰበትና በርካታ የፖለቲካ ሥራ የሠራበት ረቂቅ በምክርቤቱ በሚገኙ 108 እንደራሴዎች ስፖንሰር ያደረጉት ሲሆን የሁለቱም ማለትም የዴሞክራትና የሪፑብሊካን እንደራሴዎች በጣምራነት የደገፉት ረቂቅ ነበር።

በዋሽንግቶን ዲሲ በ“አምባሳደርነት” ሹመት የኢህአዴግ ተወካይ ሆኖ የተቀመጠው ካሣ ተክለብርሃን ለምክርቤቱ ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ ደብዳቤ ልኮ እንደነበር H.R. 128 ለኢትዮጵያ በፌስቡክ ገጹ ላይ ባተመው የደብዳቤው ፎቶ አስታውቋል።

በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኅብረት ያደረጉት እንቅስቃሴ አንዱ የድሉ አካል እንደሆነ ተነግሯል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከዚህ በፊት ይህንኑ የህወሓት ውትወታ አስመልክቶ ሲዘግብ፤ “ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ በርካታ ሙከራዎችን ህወሓት ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን – ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል።ይህንን ረቂቅ ህግ ገና ከጅምሩ የፈራው ህወሓት ለወትዋቾች (ሎቢይስቶች) በጀት መድቦ መንቀሳቀስ ከጀመረ አንድ ዓመት አልፎታል። በዋሽንግቶን ዲሲ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ተጠሪ የነበረው ግርማ ብሩ SGR Government Relations ከተባለ የወትዋቾች ድርጅት ጋር በተፈራረመው ሰነድ ላይ በግልጽ እንደተመለከተው ለዚህ የውትወታ ሥራ ድርጅቱ (SGR) በወር 150ሺህ ዶላር፤ በጥቅሉ 1.8 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሎት ረቂቅ ሕጉን የማክሸፍ ዘመቻ እንዲሠራ ስምምነት ተደርጓል” በማለት በመረጃ የተደገፈ ሪፖርት ማቅረቡ ይታወሳል።

ይህ በምክርቤቱ የፀደቀው ሕግ በኢትዮጵያ ያለውን ግድያ፣ ግፍ፣ እስራት፣ ሥቅየት፣ ወዘተ ከመዘርዘር ባሻገር አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን የህወሓት/ኢህአዴግን አገዛዝ የሚከተሉትን ተግባራት እንዲፈጽም ውሳኔ የተላለፈበት ነው፤

  • የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲያነሳ፤
  • የፀጥታ ኃይላት ከመጠን በላይ ኃይል መጠቀማቸውን እንዲያቆሙ፤
  • በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ከመጠን በላይ ኃይል በመጠቀም የተፈጸሙ ግድያዎች እንዲመረመሩ፤
  • ሕገመንግሥታዊ መብቶቻቸውን በተግባር በማዋላቸው የታሰሩት የፖለቲካ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ ተቃዋሚዎች፣ … ከእሥር እንዲለቀቁ፤
  • በሰላም የመሰባሰብ መብት እንዲከበር እና የፕሬስ ነጻነት ዋስትና እንዲሰጠው፤
  • የልማት ስትራቴጂውን በተመለከተ ከዜጎች ጋር ግልጽ ውይይት እንዲካሄድ፤
  • የተባበሩት መንግሥታት ራፖርተር በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ነጻ ምርመራ እንዲያደርግ እንዲፈቀድ፤
  • በሕጋዊነት በተመዘገቡ የተቃዋሚ ድርጅቶች የሚቀርቡ አቤቱታዎችንና ቅሬታዎችን በማዳመጥ መፍትሔ እንዲያገኙ እንዲደረግ፤
  • ሕገመንግሥታዊ መብቶቻቸውን ተጠቅመው ሃሳባቸውን በነጻነት በገለጹ ዜጎች ላይ ግድያ፣ ስቅየት፣ ግፍ፣ ወዘተ የፈጸሙ በሕግ እንዲጠየቁ፤
  • ነሐሴ 28፤ 2008ዓም ቂሊንጦ እስርቤት ላይ በመተኮስና በእሣት በማቃጠል፤ መስከረም 22፤ 2009 በኢሬቻ በዓል ላይ የሞቱትን እንዲሁም በሶማሊያ ክልል ለዓመታት ሲካሄድ የቆየውን ግድያ አስመልክቶ ምርመራ ተደርጎ ሪፖርት እንዲቀርብ የሚጠይቅ ነው።

ህወሓት/ኢህአዴግ የሚከተለውንና በተግባር አውሎ እየተጠቀመባቸው ያሉትን የአፋኝ ሕግጋት ስብስብ እንዲሰረዙ፤ እነዚህም የጸረ-ሽብር ሕጉ፤ የመያዶች ሕግ፣ ወዘተ የሚጠቀልል ነው።

በመጨረሻም ሕጉ፤

  1. አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠውን ዕርዳታ የውጭ ጉዳይ (ስቴት ዲፓርትመት) መልሶ እንዲያጤነው፤
  2. የአሜሪካ ዓለምአቀፍ የልማት ኤጀንሲ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን ስትራቴጂዎችን እንዲነድፍ፤
  3. ስቴት ዲፓርትመንት ከአሜሪካው ገንዘብ ሚ/ር መ/ቤት ጋር በጥምረት በመሆን በኢትዮጵያውያን ላይ ግድያ፣ ስቅየት፣ እንግልትና ግፍ የፈጸሙ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች በዓለምአቀፍ ደረጃ በሚታወቁ ሕግጋት መሠረት አስፈላጊው ማዕቀብ እንዲጣልባቸውና በኃላፊነት እንዲጠየቁ በግልጽ አስቀምጧል፤

እነዚህንና ሌሎች ጠቃሚ አንቀጾችን ያካተተው ረቂቅ ሲጸድቅ በምክርቤቱ አዳራሽ ተገኝተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን በጭብጨባና በዕልልታ ደስታቸውን ገልጸዋል።

ቀጣዩ ጉዞ ይህ በምክርቤት የጸደቀ ሰነድ ወደ ሕግ መወሰኛ ምክርቤት (ሴኔት) በመሄድ ድምጽ ይሰጥበትና ካለፈ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ፊርማቸውን በማኖር በሕግ መልኩ ወጥቶ ተግባራዊ እንዲደረግ ይታወጃል።

ህወሓት ይህንን ተግባር የሚያስፈጽሙለት እንደነ ሴናተር ኢንሆፍ ያሉ “ወዳጆች” እንዳሉት ሲናገር ቢሰማም ሕጉ አስቀድሞ የበርካታ ሴናተሮች ድጋፍ እንዳገኘ ይነገራል። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት 25 ሴናተሮች (18 ከዴሞክራቲክ፤ 7 ከሪፑብሊካን) S.Res.168ን ስፖንሰር አድርገዋል። ኢትዮጵያውንም H.Res. 128 ከጸደቀበት ሰዓት ጀምሮ በሴኔቱ የውሳኔ አሠራር ላይ የተጽዕኖ ሥራቸውን ማካሄድ ጀምረዋል።

(መግቢያ ፎቶ፤ ረቂቅ ሕጉ ያለተቃውሞ ሲያልፍ ሊቀመንበሩ መዶሻቸውን በመምታት ሲያረጋግጡ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, hr 128, kassa, lobby, Middle Column, sgr, sr 168, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    April 11, 2018 10:55 pm at 10:55 pm

    በናንተ ቤት፤ ሁሉም ነገር ተሳክቷል!!! መንግስቲ ግንቦት ሰባት!!! ቂቂቂ!!!ጨበርባሪዎች!!

    Reply
  2. Bekele tessema says

    April 14, 2018 11:11 pm at 11:11 pm

    አገር ወዳድ በጣም ወዳችሁሃለን ሴኔቱ ውሣኔ እንዲሠጥ የነዚ በግፍ የተገደሉት ነጳነት ፈላጊ ኢትዮጵያውያን አምላክ ይርዳችሁ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule