• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲሱ የአሜሪካ ምክርቤት ረቂቅ ሕግ በህወሓት ባለሥልጣናትና ቤተሰቦች ላይ ጭንቀት ፈጥሯል

July 28, 2017 11:55 am by Editor Leave a Comment

ትላንት በአሜሪካ ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ የፀደቀው ረቂቅ ሕግ በህወሓት ባልሥልጣናትና ቤተሰቦቻቸው ላይ ከፍተኛ ሥጋት፥ ፍርሃትና ጭንቀት መፍጠሩ ተሰማ።

ረቂቅ ሕጉን ገና ከአወጣጡ ጀምሮ ሲከታተሉና ግብዓት ሲሰጡ የቆዩ ወገኖች እንደሚሉት ይህ ያሁኑ ረቂቅ ሕግ የህወሓት ሰዎች አንገት ላይ ገመዱን ያስገባ ነው። ኢትዮጵያውያንን በመግደል፥ በማሰቃየትና በማንኛውም መልኩ የሰብዓዊ መብቶቻቸውን በመርገጥ ስማቸው የሚገኝ የህወሓት ሹሞችና ተባባሪዎቻቸው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት ከገንዘብ ሚ/ር መ/ቤት ጋር በመተባበር በዓለምአቀፍ ሕግጋት በተደነገገው መሠረት ዕቀባ እንዲያደርግባቸው ረቂቅ ሕጉ ያዛል። ይህ ማለት በሌላ አነጋገር ህወሓት/ኢህአዴግ ለዚህ የአሜሪካ የለውጥ ዕቅድ የማይገዛ ከሆነ የህወሓት ሹሞችና ቤተሰቦቻቸው ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ማዕቀብ ይጣልባቸዋል፥ ሃብታቸው እንዳይነቃነቅ ይደረጋል። የአሜሪካንን ፈለግ የሚከተለውና ከህወሓት ጋር የላላ ወዳጅነት ያለው የአውሮጳ ኅብረትም ተመሳሳይ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ያሁኑ ረቂቅ ሕግ በአሜሪካ ምክርቤት በሚገኙት ሁለቱም ፓርቲዎች ሙሉ ድጋፍ ያገኘ በመሆኑ ሊታጠፍ እንደማይችልና የወትዋቾች (ሎቢይስቶች) ድለላ የማይበግረው እንደሆነ ተነግሯል።

የህወሃት/ኢህአዴግ ሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ከሒዝቦላና ሰሜን ኮሪያ ጉዳይ ጋር በሙሉ ድምጽ ውሳኔ አገኘ (July 27, 2017 08:43 pm)

የህወሃት/ኢህአዴግን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታና አጠቃላይ አስተዳድርን የሚወቅስ የህግ ረቂቅ ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መምሪያ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ፊት ቀርቦ በሙሉ ስምምነት አልፏል። ከውሳኔው በላይ የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሕዝብን ለመከራና ስቃይ ሲዳርግ የኖረው የኢህአዴግ አገዛዝ በአሻባሪነቱ ከሚወገዘው ሒዝቦላ እና ከሰሜን ኮሪያ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ጋር በእኩል ቀርቦ መታየቱ “የአሜሪካና ኢህአዴግ ወዳጅነት ወዴት?” አስብሏል፡፡

መለስ በG-20 ስብሰባ

በዕለቱ ዘጠን አጀንዳዎች ለውሳኔ የቀረቡ ሲሆን የኢትዮጵያን ጉዳይ ጨምሮ የአውሮጳ ህብረት ሒዝቦላን አሸባሪ ድርጅት በማለት እንዲጠራው፤ የሰሜን ኮሪያን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በተመለከተ ከዚህ በፊት የወጣው እንደገና እንዲተገበር፤ ኬኒያ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳታካሂድ፣ በቬኒዙዌላ ያለውን የሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ቀውስ የሚኮንን ረቂቅ ሕግ አቅርቦ ከማስወሰንና ከሌሎች አጀንዳዎች ጋር የቀረበ ነበር፡፡ (የስብሰባውን ሙሉ ውይይትና ውሳኔ ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ)

ለምዕራባዊ ጌቶቹ በተለማማጭነትና በታዛዥነት የሚታወቀው መለስ አለቆቹ ያሉትን በመፈጸም አስፈላጊ ሲሆንም ከተጠየቀው በላይ በመሄድ ለመወደድ ያደርግ የነበረውን የአሁኖቹ የህወሓት አመራሮች ሊከውኑት ያልተቻለ ተግባር ሆኖ በተደጋጋሚ የታየ ሆኗል፡፡ በምዕራባዊ አገራት ሎሌነቱን በገሃድ ያስመሰከረው መለስ አገር ውስጥ “አሜሪካ አትረዳንም፤ የሰጡን ኮንዶም ነው፤ ሶማሊያ በኮንዶም አንዋጋም” እያለ በጠብመንጃ የሚገዛው ሕዝብ ላይ ሲደነፋ ቢኖርም ሃቁ ግን ኢህአዴግ አልሻባብን እዋጋለሁ እያለ ሲምታታ የኖረበት ዘመን ማለቁ ነው፡፡

ለዓመታት የህወሓት ቀንደኛ ተቃዋሚ በመሆን የሰላ ትችቶችን በአደባባይ በማድረግ የሚታወቁት የኒው ጀርዚው እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ዛሬም ኢህአዴግን አብጠልጥለውታል፡፡ በኢትዮጵያ “እየደረሱ ያሉት የሰብዓዊ መብቶች ረገጣዎች ፈጽሞ ተቀባይነት የላቸውም” በማለት ኢህአዴግም ሆነ ሰሚዎቹ ሊክዱት በማይችሉበት ሁኔታ ማስረጃዎችን እየጠቀሱ ተናግረዋል፡፡

ከኦባማ አስተዳደር የሥልጣን ማብቃት ጋር ተያይዞ በወያኔነት ሲያገለግሉ የቆዩና በአሜሪካ ከፍተኛ የሥልጣን እርከኖች ላይ የነበሩ “ነጭ ወያኔዎች” መልቀቅ ህወሓትን እጅግ በርካታ ገንዘብ የሚያፈስበት የሎቢ (ውትወታ) “ፕሮጀክት” ውስጥ አስገብቶታል፡፡ ይህንኑ ውትወታ አልፎ “H. Res. 128, Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia.” በሚል ርዕስ በሙሉ ድምጽ የጸደቀው ረቂቅ ሕግ ለህወሓት ተጨማሪ ራስ ምታት ሆኖ እንሚቀጥልበት ይነገራል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ ኢህአዴግ አሜሪካንን በተደጋጋሚ የጉዞ ማዕቀቧን እንድታነሳ ጠይቆ ፈቃደኛ ሳትሆን መቅረቷ የተቃዋሚው ጎራ አለመተባበርና አለመዘጋጀት ነው እንጂ አሜሪካንን ከኢህአዴግ ጋር ለማቆራረጥ ጊዜው አሁን ነው የሚሉ ወገኖችን አመለካከት ያጎላ ሆኗል፡፡

በኦባማ አስተዳደር ማብቂያ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው የነበሩት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የዴሞክራሲ፣ የሠብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ በወቅቱ የተናገሩትን አስመልክቶ ጎልጉል ይህንን ዘግቦ ነበር፡፡

ማሊኖውስኪ ይህንን ነበር ያሉት፤ “በኢትዮጵያ እንዲመጣ የሚፈለገው ለውጥ ሥርዓቱን ለዝነተ ዓለም ለማፅናት በሚደረግ ትግል

ፎቶ: የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የUSAID በኢትዮጵያ ሃላፊ ጌይል ስሚዝ (በመኪናው ላይ የሚታየው ምህጻረ ቃል “ማረት” – ማኅበረ ረድኤት ትግራይ) – Photo: David Kahrmann USAID Ethiopia)

ወይንም ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በሚወሰድ እርምጃም ሊሆን አይገባም፤ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ሥልጣን ማስረከብ ደረጃ ሊደረስ ይችላል፡፡” ሲቀጥሉም “እንደ ወዳጅ መክረናል … ምክንያቱም … ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ነገር ቢፈጠር ሙሉ ምስራቅ አፍሪቃ ምን ሊከተል እንደሚችል ስለምናውቅ … ነው” ካሉ በኋላ አገሪቱን እሳት ላይ ተቀምጦ እንደሚንተከተክ ማሰሮ የመሰሉትና ማስሮው እንዳይገነፍል ብቸኛው አማራጭ ክዳኑን መክፈት እንደሆነ ያመለክቱት ቶም ማሊኖውስኪ፣ “ተስፋ አለን ይሰሙናል፣ መልካም ነገር እንጠብቃለን” ብለዋል፡፡ ይህንን ማስጠንቀቂ በማሳያነት የሚጠቅሱ ክፍሎች ተቃዋሚው ጎራና ኢህአዴግ ተያይዘው ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንዲገቡ አሜሪካ አሁን ላይ የደረሰችበት እምነት ነው። ለዚህም ይመስላል ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠችው ይላሉ። ሌሎች ግን አሜሪካ ምንም የምታመጣው ነገር የለም፤ ብታመጣ ኖሮ እስከዛሬ አትቆይም ነበር፤ ይህ ተራ የፖለቲካ ጫወታ ነው ሲሉ የአሜሪካንን አካሄድ ያጣጥላሉ፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ “በአሻባሪነት” ስም በሶማሊ የሚያደርገው ማስፈራሪያ ጊዜው ያለፈበት ይመስላል፡፡ የህወሃትና የአልሸባብ ግንኙነት እንዳለ ሆኖ አሸባሪነትን ለመዋጋት በሚል አርባ ምንጭ የሰው-አልባ አሮፕላን ማረፊያ (ድሮን ቤዝ) ማቋቋም ደርሳ የነበረችው አሜሪካ ፕሮጀክቷን ያጠናቀቀች ይመስላል፡፡ “ሶማሊያ ውስጥ … በኮንዶም አንዋጋም!” እያለ የሚያምታታ መለስ የሌለው ህወሃት/ኢህአዴግ ቁንጮውን ብቻ ሳይሆን ከበረሃ ጀምሮ ሲያግዙት የነበሩትን “ነጭ ወያኔዎችም” እያጣ ነው፡፡

ዛሬ በረቂቅ ህግነት በሙሉ ድምጽ ያለፈው አዋጅ ወደ እንደራሴዎች ምክርቤት ቀርቦ ድምጽ እንዲሰጥበት ይደረጋል፡፡ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ኮሚቴው በሙሉ ድምጽ ማጽደቁ ለእንደራሴዎቹ ምክርቤት የድጋፍ ድምጽ መስጠት በር ከፋች ነው ብለዋል፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ያቀናበረው የምስል ዘገባ ከዚህ በታች ይገኛል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule