• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃት/ኢህአዴግ ሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ከሒዝቦላና ሰሜን ኮሪያ ጉዳይ ጋር በሙሉ ድምጽ ውሳኔ አገኘ

July 27, 2017 08:43 pm by Editor Leave a Comment

የህወሃት/ኢህአዴግን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታና አጠቃላይ አስተዳድርን የሚወቅስ የህግ ረቂቅ ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መምሪያ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ፊት ቀርቦ በሙሉ ስምምነት አልፏል። ከውሳኔው በላይ የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሕዝብን ለመከራና ስቃይ ሲዳርግ የኖረው የኢህአዴግ አገዛዝ በአሻባሪነቱ ከሚወገዘው ሒዝቦላ እና ከሰሜን ኮሪያ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ጋር በእኩል ቀርቦ መታየቱ “የአሜሪካና ኢህአዴግ ወዳጅነት ወዴት?” አስብሏል፡፡

መለስ በG-20 ስብሰባ

በዕለቱ ዘጠን አጀንዳዎች ለውሳኔ የቀረቡ ሲሆን የኢትዮጵያን ጉዳይ ጨምሮ የአውሮጳ ህብረት ሒዝቦላን አሸባሪ ድርጅት በማለት እንዲጠራው፤ የሰሜን ኮሪያን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በተመለከተ ከዚህ በፊት የወጣው እንደገና እንዲተገበር፤ ኬኒያ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳታካሂድ፣ በቬኒዙዌላ ያለውን የሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ቀውስ የሚኮንን ረቂቅ ሕግ አቅርቦ ከማስወሰንና ከሌሎች አጀንዳዎች ጋር የቀረበ ነበር፡፡ (የስብሰባውን ሙሉ ውይይትና ውሳኔ ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ)

ለምዕራባዊ ጌቶቹ በተለማማጭነትና በታዛዥነት የሚታወቀው መለስ አለቆቹ ያሉትን በመፈጸም አስፈላጊ ሲሆንም ከተጠየቀው በላይ በመሄድ ለመወደድ ያደርግ የነበረውን የአሁኖቹ የህወሓት አመራሮች ሊከውኑት ያልተቻለ ተግባር ሆኖ በተደጋጋሚ የታየ ሆኗል፡፡ በምዕራባዊ አገራት ሎሌነቱን በገሃድ ያስመሰከረው መለስ አገር ውስጥ “አሜሪካ አትረዳንም፤ የሰጡን ኮንዶም ነው፤ ሶማሊያ በኮንዶም አንዋጋም” እያለ በጠብመንጃ የሚገዛው ሕዝብ ላይ ሲደነፋ ቢኖርም ሃቁ ግን ኢህአዴግ አልሻባብን እዋጋለሁ እያለ ሲምታታ የኖረበት ዘመን ማለቁ ነው፡፡

ለዓመታት የህወሓት ቀንደኛ ተቃዋሚ በመሆን የሰላ ትችቶችን በአደባባይ በማድረግ የሚታወቁት የኒው ጀርዚው እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ዛሬም ኢህአዴግን አብጠልጥለውታል፡፡ በኢትዮጵያ “እየደረሱ ያሉት የሰብዓዊ መብቶች ረገጣዎች ፈጽሞ ተቀባይነት የላቸውም” በማለት ኢህአዴግም ሆነ ሰሚዎቹ ሊክዱት በማይችሉበት ሁኔታ ማስረጃዎችን እየጠቀሱ ተናግረዋል፡፡

ከኦባማ አስተዳደር የሥልጣን ማብቃት ጋር ተያይዞ በወያኔነት ሲያገለግሉ የቆዩና በአሜሪካ ከፍተኛ የሥልጣን እርከኖች ላይ የነበሩ “ነጭ ወያኔዎች” መልቀቅ ህወሓትን እጅግ በርካታ ገንዘብ የሚያፈስበት የሎቢ (ውትወታ) “ፕሮጀክት” ውስጥ አስገብቶታል፡፡ ይህንኑ ውትወታ አልፎ “H. Res. 128, Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia.” በሚል ርዕስ በሙሉ ድምጽ የጸደቀው ረቂቅ ሕግ ለህወሓት ተጨማሪ ራስ ምታት ሆኖ እንሚቀጥልበት ይነገራል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ ኢህአዴግ አሜሪካንን በተደጋጋሚ የጉዞ ማዕቀቧን እንድታነሳ ጠይቆ ፈቃደኛ ሳትሆን መቅረቷ የተቃዋሚው ጎራ አለመተባበርና አለመዘጋጀት ነው እንጂ አሜሪካንን ከኢህአዴግ ጋር ለማቆራረጥ ጊዜው አሁን ነው የሚሉ ወገኖችን አመለካከት ያጎላ ሆኗል፡፡

በኦባማ አስተዳደር ማብቂያ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው የነበሩት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የዴሞክራሲ፣ የሠብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ በወቅቱ የተናገሩትን አስመልክቶ ጎልጉል ይህንን ዘግቦ ነበር፡፡

ማሊኖውስኪ ይህንን ነበር ያሉት፤ “በኢትዮጵያ እንዲመጣ የሚፈለገው ለውጥ ሥርዓቱን ለዝነተ ዓለም ለማፅናት በሚደረግ ትግል

ፎቶ: የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የUSAID በኢትዮጵያ ሃላፊ ጌይል ስሚዝ (በመኪናው ላይ የሚታየው ምህጻረ ቃል “ማረት” – ማኅበረ ረድኤት ትግራይ) – Photo: David Kahrmann USAID Ethiopia)

ወይንም ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በሚወሰድ እርምጃም ሊሆን አይገባም፤ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ሥልጣን ማስረከብ ደረጃ ሊደረስ ይችላል፡፡” ሲቀጥሉም “እንደ ወዳጅ መክረናል … ምክንያቱም … ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ነገር ቢፈጠር ሙሉ ምስራቅ አፍሪቃ ምን ሊከተል እንደሚችል ስለምናውቅ … ነው” ካሉ በኋላ አገሪቱን እሳት ላይ ተቀምጦ እንደሚንተከተክ ማሰሮ የመሰሉትና ማስሮው እንዳይገነፍል ብቸኛው አማራጭ ክዳኑን መክፈት እንደሆነ ያመለክቱት ቶም ማሊኖውስኪ፣ “ተስፋ አለን ይሰሙናል፣ መልካም ነገር እንጠብቃለን” ብለዋል፡፡ ይህንን ማስጠንቀቂ በማሳያነት የሚጠቅሱ ክፍሎች ተቃዋሚው ጎራና ኢህአዴግ ተያይዘው ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንዲገቡ አሜሪካ አሁን ላይ የደረሰችበት እምነት ነው። ለዚህም ይመስላል ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠችው ይላሉ። ሌሎች ግን አሜሪካ ምንም የምታመጣው ነገር የለም፤ ብታመጣ ኖሮ እስከዛሬ አትቆይም ነበር፤ ይህ ተራ የፖለቲካ ጫወታ ነው ሲሉ የአሜሪካንን አካሄድ ያጣጥላሉ፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ “በአሻባሪነት” ስም በሶማሊ የሚያደርገው ማስፈራሪያ ጊዜው ያለፈበት ይመስላል፡፡ የህወሃትና የአልሸባብ ግንኙነት እንዳለ ሆኖ አሸባሪነትን ለመዋጋት በሚል አርባ ምንጭ የሰው-አልባ አሮፕላን ማረፊያ (ድሮን ቤዝ) ማቋቋም ደርሳ የነበረችው አሜሪካ ፕሮጀክቷን ያጠናቀቀች ይመስላል፡፡ “ሶማሊያ ውስጥ … በኮንዶም አንዋጋም!” እያለ የሚያምታታ መለስ የሌለው ህወሃት/ኢህአዴግ ቁንጮውን ብቻ ሳይሆን ከበረሃ ጀምሮ ሲያግዙት የነበሩትን “ነጭ ወያኔዎችም” እያጣ ነው፡፡

ዛሬ በረቂቅ ህግነት በሙሉ ድምጽ ያለፈው አዋጅ ወደ እንደራሴዎች ምክርቤት ቀርቦ ድምጽ እንዲሰጥበት ይደረጋል፡፡ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ኮሚቴው በሙሉ ድምጽ ማጽደቁ ለእንደራሴዎቹ ምክርቤት የድጋፍ ድምጽ መስጠት በር ከፋች ነው ብለዋል፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ያቀናበረው የምስል ዘገባ ከዚህ በታች ይገኛል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule