• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የህወሃት/ኢህአዴግ ሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ከሒዝቦላና ሰሜን ኮሪያ ጉዳይ ጋር በሙሉ ድምጽ ውሳኔ አገኘ

July 27, 2017 08:43 pm by Editor Leave a Comment

የህወሃት/ኢህአዴግን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታና አጠቃላይ አስተዳድርን የሚወቅስ የህግ ረቂቅ ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መምሪያ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ፊት ቀርቦ በሙሉ ስምምነት አልፏል። ከውሳኔው በላይ የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሕዝብን ለመከራና ስቃይ ሲዳርግ የኖረው የኢህአዴግ አገዛዝ በአሻባሪነቱ ከሚወገዘው ሒዝቦላ እና ከሰሜን ኮሪያ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ጋር በእኩል ቀርቦ መታየቱ “የአሜሪካና ኢህአዴግ ወዳጅነት ወዴት?” አስብሏል፡፡

መለስ በG-20 ስብሰባ

በዕለቱ ዘጠን አጀንዳዎች ለውሳኔ የቀረቡ ሲሆን የኢትዮጵያን ጉዳይ ጨምሮ የአውሮጳ ህብረት ሒዝቦላን አሸባሪ ድርጅት በማለት እንዲጠራው፤ የሰሜን ኮሪያን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በተመለከተ ከዚህ በፊት የወጣው እንደገና እንዲተገበር፤ ኬኒያ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳታካሂድ፣ በቬኒዙዌላ ያለውን የሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ቀውስ የሚኮንን ረቂቅ ሕግ አቅርቦ ከማስወሰንና ከሌሎች አጀንዳዎች ጋር የቀረበ ነበር፡፡ (የስብሰባውን ሙሉ ውይይትና ውሳኔ ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ)

ለምዕራባዊ ጌቶቹ በተለማማጭነትና በታዛዥነት የሚታወቀው መለስ አለቆቹ ያሉትን በመፈጸም አስፈላጊ ሲሆንም ከተጠየቀው በላይ በመሄድ ለመወደድ ያደርግ የነበረውን የአሁኖቹ የህወሓት አመራሮች ሊከውኑት ያልተቻለ ተግባር ሆኖ በተደጋጋሚ የታየ ሆኗል፡፡ በምዕራባዊ አገራት ሎሌነቱን በገሃድ ያስመሰከረው መለስ አገር ውስጥ “አሜሪካ አትረዳንም፤ የሰጡን ኮንዶም ነው፤ ሶማሊያ በኮንዶም አንዋጋም” እያለ በጠብመንጃ የሚገዛው ሕዝብ ላይ ሲደነፋ ቢኖርም ሃቁ ግን ኢህአዴግ አልሻባብን እዋጋለሁ እያለ ሲምታታ የኖረበት ዘመን ማለቁ ነው፡፡

ለዓመታት የህወሓት ቀንደኛ ተቃዋሚ በመሆን የሰላ ትችቶችን በአደባባይ በማድረግ የሚታወቁት የኒው ጀርዚው እንደራሴ ክሪስ ስሚዝ ዛሬም ኢህአዴግን አብጠልጥለውታል፡፡ በኢትዮጵያ “እየደረሱ ያሉት የሰብዓዊ መብቶች ረገጣዎች ፈጽሞ ተቀባይነት የላቸውም” በማለት ኢህአዴግም ሆነ ሰሚዎቹ ሊክዱት በማይችሉበት ሁኔታ ማስረጃዎችን እየጠቀሱ ተናግረዋል፡፡

ከኦባማ አስተዳደር የሥልጣን ማብቃት ጋር ተያይዞ በወያኔነት ሲያገለግሉ የቆዩና በአሜሪካ ከፍተኛ የሥልጣን እርከኖች ላይ የነበሩ “ነጭ ወያኔዎች” መልቀቅ ህወሓትን እጅግ በርካታ ገንዘብ የሚያፈስበት የሎቢ (ውትወታ) “ፕሮጀክት” ውስጥ አስገብቶታል፡፡ ይህንኑ ውትወታ አልፎ “H. Res. 128, Supporting respect for human rights and encouraging inclusive governance in Ethiopia.” በሚል ርዕስ በሙሉ ድምጽ የጸደቀው ረቂቅ ሕግ ለህወሓት ተጨማሪ ራስ ምታት ሆኖ እንሚቀጥልበት ይነገራል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ ኢህአዴግ አሜሪካንን በተደጋጋሚ የጉዞ ማዕቀቧን እንድታነሳ ጠይቆ ፈቃደኛ ሳትሆን መቅረቷ የተቃዋሚው ጎራ አለመተባበርና አለመዘጋጀት ነው እንጂ አሜሪካንን ከኢህአዴግ ጋር ለማቆራረጥ ጊዜው አሁን ነው የሚሉ ወገኖችን አመለካከት ያጎላ ሆኗል፡፡

በኦባማ አስተዳደር ማብቂያ ላይ ወደ ኢትዮጵያ ሄደው የነበሩት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት የዴሞክራሲ፣ የሠብዓዊ መብቶችና የሥራ ረዳት ሚኒስትር ቶም ማሊኖውስኪ በወቅቱ የተናገሩትን አስመልክቶ ጎልጉል ይህንን ዘግቦ ነበር፡፡

ማሊኖውስኪ ይህንን ነበር ያሉት፤ “በኢትዮጵያ እንዲመጣ የሚፈለገው ለውጥ ሥርዓቱን ለዝነተ ዓለም ለማፅናት በሚደረግ ትግል

ፎቶ: የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የUSAID በኢትዮጵያ ሃላፊ ጌይል ስሚዝ (በመኪናው ላይ የሚታየው ምህጻረ ቃል “ማረት” – ማኅበረ ረድኤት ትግራይ) – Photo: David Kahrmann USAID Ethiopia)

ወይንም ሥርዓቱን በኃይል ለማፍረስ በሚወሰድ እርምጃም ሊሆን አይገባም፤ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ሥልጣን ማስረከብ ደረጃ ሊደረስ ይችላል፡፡” ሲቀጥሉም “እንደ ወዳጅ መክረናል … ምክንያቱም … ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ነገር ቢፈጠር ሙሉ ምስራቅ አፍሪቃ ምን ሊከተል እንደሚችል ስለምናውቅ … ነው” ካሉ በኋላ አገሪቱን እሳት ላይ ተቀምጦ እንደሚንተከተክ ማሰሮ የመሰሉትና ማስሮው እንዳይገነፍል ብቸኛው አማራጭ ክዳኑን መክፈት እንደሆነ ያመለክቱት ቶም ማሊኖውስኪ፣ “ተስፋ አለን ይሰሙናል፣ መልካም ነገር እንጠብቃለን” ብለዋል፡፡ ይህንን ማስጠንቀቂ በማሳያነት የሚጠቅሱ ክፍሎች ተቃዋሚው ጎራና ኢህአዴግ ተያይዘው ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል እንዲገቡ አሜሪካ አሁን ላይ የደረሰችበት እምነት ነው። ለዚህም ይመስላል ቅድመ ሁኔታ ያስቀመጠችው ይላሉ። ሌሎች ግን አሜሪካ ምንም የምታመጣው ነገር የለም፤ ብታመጣ ኖሮ እስከዛሬ አትቆይም ነበር፤ ይህ ተራ የፖለቲካ ጫወታ ነው ሲሉ የአሜሪካንን አካሄድ ያጣጥላሉ፡፡

ህወሓት/ኢህአዴግ “በአሻባሪነት” ስም በሶማሊ የሚያደርገው ማስፈራሪያ ጊዜው ያለፈበት ይመስላል፡፡ የህወሃትና የአልሸባብ ግንኙነት እንዳለ ሆኖ አሸባሪነትን ለመዋጋት በሚል አርባ ምንጭ የሰው-አልባ አሮፕላን ማረፊያ (ድሮን ቤዝ) ማቋቋም ደርሳ የነበረችው አሜሪካ ፕሮጀክቷን ያጠናቀቀች ይመስላል፡፡ “ሶማሊያ ውስጥ … በኮንዶም አንዋጋም!” እያለ የሚያምታታ መለስ የሌለው ህወሃት/ኢህአዴግ ቁንጮውን ብቻ ሳይሆን ከበረሃ ጀምሮ ሲያግዙት የነበሩትን “ነጭ ወያኔዎችም” እያጣ ነው፡፡

ዛሬ በረቂቅ ህግነት በሙሉ ድምጽ ያለፈው አዋጅ ወደ እንደራሴዎች ምክርቤት ቀርቦ ድምጽ እንዲሰጥበት ይደረጋል፡፡ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ኮሚቴው በሙሉ ድምጽ ማጽደቁ ለእንደራሴዎቹ ምክርቤት የድጋፍ ድምጽ መስጠት በር ከፋች ነው ብለዋል፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ያቀናበረው የምስል ዘገባ ከዚህ በታች ይገኛል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule