• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የነጭ ወያኔዎች” ሥልጣን መልቀቅና የተቀሩት “የዳግም ውልደት” ክህደት

December 11, 2016 10:36 am by Editor 1 Comment

የህወሃትና የአሜሪካ ፍቅር ቀደም ሲል ይወራ እንደነበረው “በመካከላቸው ንፋስ ገባ” ከሚባልበት ደረጃ ባለፈ እየሰለለ መምጣቱን የሚጠቁሙ እውነታዎች እየታዩ ነው። ራሱ ህወሃት ይህንኑ ፍትጊያ የሚያጎሉ ጉዳዮች እያከናወነ ይገኛል። ለልዩነቱ መክረር ፍንጭ እየታየ ነው። ከኦባማ ዘመን ማብቃት ጋር ተያይዞ የቀድሞ ወዳጆቹ የነበሩት “ነጭ ወያኔዎች” ሥልጣን መልቀቅ እውን ሊሆን ሲቃረብ የተቀሩት “በዳግም ውልደት” እየከዱት ነው የሚል መረጃ ሲነገር ይደመጣል፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያወጣው መግለጫና ማሳሰቢያ ክብደቱ መጨመሩ፣ የአገሪቱ ከፍተኛ የፖለቲካ ባለስልጣናትና ቁልፍ አማካሪዎች፣ እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ ሚዲያዎች ህወሃትን እያብጠለጠሉትና ክፉኛ እየነቀፉት ነው። ከውስጥ የሚወጡ መረጃዎች ደግሞ በውይይት ህወሃት “አደረጋለሁ” እያለ ማጨበርበሩ አሜሪካኖቹን አበሳጭቷል።

ለዚህም ይመስላል “the white woyane – ፈረንጆቹ (ነጮቹ) ወያኔዎች” ለሚባሉት ወዳጆቻቸው ሳይቀሩ “የማይሰሙ፣ የማይታዘዙ፣ ምነው መለስ በኖረ … ” ሲሉ መማረራቸውን እንደሚገልጹ ነው። አንዷ ነጭ ወያኔና የወያኔ ቁልፍ ተሟጋች “አሁንስ የደቡብ ሱዳንን መንግሥት አደረጉን” ስትል ተሰማቷል።

መለስ በG-20 ስብሰባ
መለስ በG-20 ስብሰባ

ነጮቹ ወያኔዎች ከኦባማ አስተዳደር ጋር ተጠራርገው በሚወጡበት የሽግግር ጊዜ ላይ፣ የቀድሞዎቹ ነጭ ወያኔዎች (ጥቁሮችም ሊሆኑ ይችላሉ) እና በቀጣዩ አስተዳደር ኃላፊነት ሊኖራቸው ይችላሉ ተብለው የሚጠበቁ አንዳንዶች “ዳግም በመወለድ” (born again) ሂደት ላይ መሆናቸውን ባልደረቦቻቸው በሹክሹክታ እንደሚናገሩ እየተደመጠ ነው። ይህ የገባው ህወሃት ጦሩን ከሶማሊያ በማውጣት ለማስፈራርት ቢሞክርም አልሆነለትም። እንደቀድሞው “እሹሩሩ” የሚለው አላገኘም። ይልቁኑም ፊቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ቻይና በማዞር የገባበትን ራስ ምታት ይፋ አድርጓል። ለዚሁ የራስ ምታት መድሃኒት ይሆን ዘንድ ከቻይና ጋር ሙሉ በሙሉ በጸጥታና በመከላከያ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርሟል።

በሱዳን በኩል ንፋስ እንዳይገባ የጸጥታ፣ የኢኮኖሚ፣ አንዲሁም ከትግራይ ካርቱም የሚዘልቅ የባቡርና የመንገድ ግንባታ ውል ተፈራርሟል። ይህ ብቻ አይደለም ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት ጉዳይ አጣድፎ ለመጨረስና ድንበር አካሎ በመፈራረም ህጋዊ ሰነድ ለማዘጋጀትም በስምምነቱ መካተቱን የጎልጉል ምንጮች አረጋግጠዋል።

cairo-egypt-9th-sep-2014-egyptian-president-abdel-fattah-al-sisi-meets-e78fjaበሌላም በኩል የሻዕቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቅና የግብጹ አል-ሲሲ በቅርቡ ያደረጉት የመከላከያና የኢኮኖሚ ስምምነት አል-ሲሲ ከተሰየሙበት ዓላማ ጋር ተዳምሮ ሲታይ ጉዳዩ የእነማ እጅ አለበት የሚለው ጉዳይ ህወሃቶችን ጤና እንደነሳቸው ውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ። ግብጽ ሱዳንን እንዳትከረብትባቸው ህወሃቶች ለሱዳን ማንኛውንም ነገር ከማድረግና ከመታዘዝ ወደኋላ እንደማይሉ የአብዛኞች ስምምነት ነው።

በዚህ የአጣብቂኝ ፖለቲካ ውስጥ ነው አሜሪካ እየከረረች የመጣችው። ለአንዳንድ ቁልፍ ዲፕሎማቶች ቅርብ የሆኑ የጎልጉል መረጃ አቀባዮች እንደሚሉት “ዳግም መወለድ ለነጮቹ ወያኔዎች ብቻ ሳይሆን ለዋናዎቹ ወያኔዎች በዚህ ወቅት እጅግ አስፈላጊ ነው”፡፡ ባለፈው ረቡዕ አሜሪካ ያወጣቸውን አዲሱን የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዜና ከአሜሪካ ሬዲዮ ወስደን ለአንባቢዎች እንዲመች እርማት አድርገን  ከዚህ በታች አቅርበነዋል። ማስጠንቀቂያው በተዘዋዋሪ መንገድ የአስቸኳይ አዋጁን አንሱ የሚል ይመስላል።

አሜሪካ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አራዘመች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ላሰቡ ዜጎች ያሰራጨው የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከዚህ ቀደም ጥቅምት 11 ቀን የወጣውን የሚተካ ሲሆን ምክንያት ያለውንም ይፋ አድርጓል። መንግስት በበኩሉ ጉዳዩን በቀጥታ ባይቃወምም አሁን አገሪቱ መረጋጋቷን አስታውቋል።

አሜሪካ የጉዞ ማስጠንቀቂያዋን አራዘመች

“መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ተሻሽሏል” ነገሪ ሌንጮ

በኢትዮጵያ ከህዳር 2008 ዓ.ም ጀምሮ የተቀሰቀሰው ፀረ-መንግሥት አመፅና በተጨባጭ የሚታየው የፀጥታ ሁኔታ ወዴት እንደሚያመራ ለመተንበይ አስቸጋሪ እንደሆነ አዲሱ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አመልክቷል። ማስጠንቀቂያው አያይዞም የአሜሪካ ኤምባሲ አገልግሎት በሚሰጥባቸው የተለያዩ አካባቢዎች ያለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ሊቋረጥ እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል።

የኢንተርኔትና የሞባይል ስልክ አገልግሎቶች በመላ ሃገሪቱ በየወቅቱ ያለማስጠንቀቂያ ስለሚቋረጡና ሙሉ በሙሉም ስለሚዘጉ ሁኔታው አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ዜጎቹን የመርዳት አቅሙን እንደሚያደናቅፍ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ያወጣው የማስጠንቀቂያ ማስታወቂያ አብራርቷል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች አማራጭ የግንኙነት ዘዴዎች እንዲኖሯቸውና ኢትዮጵያ ውስጥ ሲኖሩ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ሊያጋጥም እንደሚችል ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ያሉበትን አድራሻ ለቤተሰቦቻቸውና ለጓደኞቻቸው እንዲያሳውቁ የጉዞ ማስጠንቀቂያው መክሯል፡፡

መንግሥት ሰላማዊ ሰልፎችን ለመበተን ሰዎች ላይ በቀጥታ ሊተኩስ እንደሚችል፣ በሰላማዊ መንገድ ለመካናወን በሚጠሩ ሰልፎች የኃይል ምላሽ እንደሚሰጥና ሰልፎቹ ያለ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ወደ ሁከት ሊለወጡ እንደሚችሉ ዜጎቹ አስቀደመው በማሰብ እንደ አስፈላጊነቱ ጥንቃቄ እንዲወስዱ ያዘዘው ይህ የጉዞ ማስጠንቀቂያ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች የደኅንነት ሁኔታቸውን በመከታተል አስፈላጊ ከሆነም ፈጥነው ከሃገር መውጣት የሚያስችላቸውን የአደጋ ጊዜ ዕቅዶች እንዲያመቻቹ መክሯል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ነገሪ ሌንጮ “መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ተሻሽሏል፤ የአሜሪካ መንግሥት ያወጣው ማስታወቂያ ግን የራሱ አቋም በመሆኑ ለአሜሪካ መንግሥት እንተወዋለን” በማለት የተለሳለሰ ምላሽ ዜናውን ላጠናቀረው የቪኦኤ አማርኛ ዝግጅት ክፍል ምላሽ ሰጥተዋል።

የህወሃትና የነጭ ወያኔዎቹ ቀጣይ ግንኙነት ወዴት ሊያመራ እንደሚችል ከላይ የተጠቀሱት የተወሰኑ ፍንጮች በአንድ መልኩ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ግን አሜሪካ የግል ጥቅሟን ከማስጠበቅና ህወሃት ደግሞ ለጌቶቹ የመታዘዝ ግዴታው ከማሸርገድ ባህርዩ ጋር ተጣምሮ ህልውናውን ለማስቀጠል ሲል በአዲሱ የትራምፕ አስተዳደር በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ አዳዲስ ነጭ ወያኔዎችን በውትወታ (ሎቢ) ለመመልመል የመሞከሩ ጉዳይ መዘንጋት የሌለበት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር በተለይ በአሜሪካ የሚገኙ ተቃዋሚ ኃይላት ጉዳዩ ካለቀ በኋላ የተቃውሞ ሰልፍ ከመውጣት ይልቅ ካሁኑ በፊናቸው የውትወታ ሥራ እንዲደርጉ ለጎልጉል አስተየታቸውን የሰጡ ያሳስባሉ፡፡ (መግቢያ ፎቶ: የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የUSAID በኢትዮጵያ ሃላፊ ጌይል ስሚዝ (በመኪናው ላይ የሚታየው ምህጻረ ቃል “ማረት” – ማኅበረ ረድኤት ትግራይ) – Photo: David Kahrmann USAID Ethiopia)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    December 11, 2016 11:56 am at 11:56 am

    Christ for ever.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule