• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የነጭ ወያኔዎች” ሥልጣን መልቀቅና የተቀሩት “የዳግም ውልደት” ክህደት

December 11, 2016 10:36 am by Editor 1 Comment

የህወሃትና የአሜሪካ ፍቅር ቀደም ሲል ይወራ እንደነበረው “በመካከላቸው ንፋስ ገባ” ከሚባልበት ደረጃ ባለፈ እየሰለለ መምጣቱን የሚጠቁሙ እውነታዎች እየታዩ ነው። ራሱ ህወሃት ይህንኑ ፍትጊያ የሚያጎሉ ጉዳዮች እያከናወነ ይገኛል። ለልዩነቱ መክረር ፍንጭ እየታየ ነው። ከኦባማ ዘመን ማብቃት ጋር ተያይዞ የቀድሞ ወዳጆቹ የነበሩት “ነጭ ወያኔዎች” ሥልጣን መልቀቅ እውን ሊሆን ሲቃረብ የተቀሩት “በዳግም ውልደት” እየከዱት ነው የሚል መረጃ ሲነገር ይደመጣል፡፡

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያወጣው መግለጫና ማሳሰቢያ ክብደቱ መጨመሩ፣ የአገሪቱ ከፍተኛ የፖለቲካ ባለስልጣናትና ቁልፍ አማካሪዎች፣ እንዲሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ ሚዲያዎች ህወሃትን እያብጠለጠሉትና ክፉኛ እየነቀፉት ነው። ከውስጥ የሚወጡ መረጃዎች ደግሞ በውይይት ህወሃት “አደረጋለሁ” እያለ ማጨበርበሩ አሜሪካኖቹን አበሳጭቷል።

ለዚህም ይመስላል “the white woyane – ፈረንጆቹ (ነጮቹ) ወያኔዎች” ለሚባሉት ወዳጆቻቸው ሳይቀሩ “የማይሰሙ፣ የማይታዘዙ፣ ምነው መለስ በኖረ … ” ሲሉ መማረራቸውን እንደሚገልጹ ነው። አንዷ ነጭ ወያኔና የወያኔ ቁልፍ ተሟጋች “አሁንስ የደቡብ ሱዳንን መንግሥት አደረጉን” ስትል ተሰማቷል።

መለስ በG-20 ስብሰባ
መለስ በG-20 ስብሰባ

ነጮቹ ወያኔዎች ከኦባማ አስተዳደር ጋር ተጠራርገው በሚወጡበት የሽግግር ጊዜ ላይ፣ የቀድሞዎቹ ነጭ ወያኔዎች (ጥቁሮችም ሊሆኑ ይችላሉ) እና በቀጣዩ አስተዳደር ኃላፊነት ሊኖራቸው ይችላሉ ተብለው የሚጠበቁ አንዳንዶች “ዳግም በመወለድ” (born again) ሂደት ላይ መሆናቸውን ባልደረቦቻቸው በሹክሹክታ እንደሚናገሩ እየተደመጠ ነው። ይህ የገባው ህወሃት ጦሩን ከሶማሊያ በማውጣት ለማስፈራርት ቢሞክርም አልሆነለትም። እንደቀድሞው “እሹሩሩ” የሚለው አላገኘም። ይልቁኑም ፊቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ቻይና በማዞር የገባበትን ራስ ምታት ይፋ አድርጓል። ለዚሁ የራስ ምታት መድሃኒት ይሆን ዘንድ ከቻይና ጋር ሙሉ በሙሉ በጸጥታና በመከላከያ ጉዳይ ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርሟል።

በሱዳን በኩል ንፋስ እንዳይገባ የጸጥታ፣ የኢኮኖሚ፣ አንዲሁም ከትግራይ ካርቱም የሚዘልቅ የባቡርና የመንገድ ግንባታ ውል ተፈራርሟል። ይህ ብቻ አይደለም ለሱዳን የሚሰጠውን መሬት ጉዳይ አጣድፎ ለመጨረስና ድንበር አካሎ በመፈራረም ህጋዊ ሰነድ ለማዘጋጀትም በስምምነቱ መካተቱን የጎልጉል ምንጮች አረጋግጠዋል።

cairo-egypt-9th-sep-2014-egyptian-president-abdel-fattah-al-sisi-meets-e78fjaበሌላም በኩል የሻዕቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቅና የግብጹ አል-ሲሲ በቅርቡ ያደረጉት የመከላከያና የኢኮኖሚ ስምምነት አል-ሲሲ ከተሰየሙበት ዓላማ ጋር ተዳምሮ ሲታይ ጉዳዩ የእነማ እጅ አለበት የሚለው ጉዳይ ህወሃቶችን ጤና እንደነሳቸው ውስጥ አዋቂዎች ይገልጻሉ። ግብጽ ሱዳንን እንዳትከረብትባቸው ህወሃቶች ለሱዳን ማንኛውንም ነገር ከማድረግና ከመታዘዝ ወደኋላ እንደማይሉ የአብዛኞች ስምምነት ነው።

በዚህ የአጣብቂኝ ፖለቲካ ውስጥ ነው አሜሪካ እየከረረች የመጣችው። ለአንዳንድ ቁልፍ ዲፕሎማቶች ቅርብ የሆኑ የጎልጉል መረጃ አቀባዮች እንደሚሉት “ዳግም መወለድ ለነጮቹ ወያኔዎች ብቻ ሳይሆን ለዋናዎቹ ወያኔዎች በዚህ ወቅት እጅግ አስፈላጊ ነው”፡፡ ባለፈው ረቡዕ አሜሪካ ያወጣቸውን አዲሱን የጉዞ ማስጠንቀቂያ ዜና ከአሜሪካ ሬዲዮ ወስደን ለአንባቢዎች እንዲመች እርማት አድርገን  ከዚህ በታች አቅርበነዋል። ማስጠንቀቂያው በተዘዋዋሪ መንገድ የአስቸኳይ አዋጁን አንሱ የሚል ይመስላል።

አሜሪካ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አራዘመች። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ላሰቡ ዜጎች ያሰራጨው የጉዞ ማስጠንቀቂያ ከዚህ ቀደም ጥቅምት 11 ቀን የወጣውን የሚተካ ሲሆን ምክንያት ያለውንም ይፋ አድርጓል። መንግስት በበኩሉ ጉዳዩን በቀጥታ ባይቃወምም አሁን አገሪቱ መረጋጋቷን አስታውቋል።

አሜሪካ የጉዞ ማስጠንቀቂያዋን አራዘመች

“መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ተሻሽሏል” ነገሪ ሌንጮ

በኢትዮጵያ ከህዳር 2008 ዓ.ም ጀምሮ የተቀሰቀሰው ፀረ-መንግሥት አመፅና በተጨባጭ የሚታየው የፀጥታ ሁኔታ ወዴት እንደሚያመራ ለመተንበይ አስቸጋሪ እንደሆነ አዲሱ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አመልክቷል። ማስጠንቀቂያው አያይዞም የአሜሪካ ኤምባሲ አገልግሎት በሚሰጥባቸው የተለያዩ አካባቢዎች ያለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ሊቋረጥ እንደሚችል ስጋቱን ገልጿል።

የኢንተርኔትና የሞባይል ስልክ አገልግሎቶች በመላ ሃገሪቱ በየወቅቱ ያለማስጠንቀቂያ ስለሚቋረጡና ሙሉ በሙሉም ስለሚዘጉ ሁኔታው አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ዜጎቹን የመርዳት አቅሙን እንደሚያደናቅፍ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ያወጣው የማስጠንቀቂያ ማስታወቂያ አብራርቷል፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች አማራጭ የግንኙነት ዘዴዎች እንዲኖሯቸውና ኢትዮጵያ ውስጥ ሲኖሩ እንዲህ ዓይነቱ ችግር ሊያጋጥም እንደሚችል ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ያሉበትን አድራሻ ለቤተሰቦቻቸውና ለጓደኞቻቸው እንዲያሳውቁ የጉዞ ማስጠንቀቂያው መክሯል፡፡

መንግሥት ሰላማዊ ሰልፎችን ለመበተን ሰዎች ላይ በቀጥታ ሊተኩስ እንደሚችል፣ በሰላማዊ መንገድ ለመካናወን በሚጠሩ ሰልፎች የኃይል ምላሽ እንደሚሰጥና ሰልፎቹ ያለ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ወደ ሁከት ሊለወጡ እንደሚችሉ ዜጎቹ አስቀደመው በማሰብ እንደ አስፈላጊነቱ ጥንቃቄ እንዲወስዱ ያዘዘው ይህ የጉዞ ማስጠንቀቂያ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች የደኅንነት ሁኔታቸውን በመከታተል አስፈላጊ ከሆነም ፈጥነው ከሃገር መውጣት የሚያስችላቸውን የአደጋ ጊዜ ዕቅዶች እንዲያመቻቹ መክሯል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት ቃል አቀባይ ነገሪ ሌንጮ “መሬት ላይ ያለው ሁኔታ ተሻሽሏል፤ የአሜሪካ መንግሥት ያወጣው ማስታወቂያ ግን የራሱ አቋም በመሆኑ ለአሜሪካ መንግሥት እንተወዋለን” በማለት የተለሳለሰ ምላሽ ዜናውን ላጠናቀረው የቪኦኤ አማርኛ ዝግጅት ክፍል ምላሽ ሰጥተዋል።

የህወሃትና የነጭ ወያኔዎቹ ቀጣይ ግንኙነት ወዴት ሊያመራ እንደሚችል ከላይ የተጠቀሱት የተወሰኑ ፍንጮች በአንድ መልኩ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ግን አሜሪካ የግል ጥቅሟን ከማስጠበቅና ህወሃት ደግሞ ለጌቶቹ የመታዘዝ ግዴታው ከማሸርገድ ባህርዩ ጋር ተጣምሮ ህልውናውን ለማስቀጠል ሲል በአዲሱ የትራምፕ አስተዳደር በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ አዳዲስ ነጭ ወያኔዎችን በውትወታ (ሎቢ) ለመመልመል የመሞከሩ ጉዳይ መዘንጋት የሌለበት ነው፡፡ ከዚህ አንጻር በተለይ በአሜሪካ የሚገኙ ተቃዋሚ ኃይላት ጉዳዩ ካለቀ በኋላ የተቃውሞ ሰልፍ ከመውጣት ይልቅ ካሁኑ በፊናቸው የውትወታ ሥራ እንዲደርጉ ለጎልጉል አስተየታቸውን የሰጡ ያሳስባሉ፡፡ (መግቢያ ፎቶ: የወያኔ ቀንደኛ ደጋፊ የUSAID በኢትዮጵያ ሃላፊ ጌይል ስሚዝ (በመኪናው ላይ የሚታየው ምህጻረ ቃል “ማረት” – ማኅበረ ረድኤት ትግራይ) – Photo: David Kahrmann USAID Ethiopia)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    December 11, 2016 11:56 am at 11:56 am

    Christ for ever.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule