• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዶ/ር መረራ እስር፤ ህወሃትና ምዕራባውያን ፖለቲከኞች

December 7, 2016 09:27 am by Editor 2 Comments

ከአውሮጳ ስብሰባ ወደአገራቸው ሲመለሱ የታፈኑትና በኋላ መታሰራቸው የተሰማው ዶ/ር መረራ ጉዲና የአሜሪካና የአውሮጳ ፖለቲከኞች በኢትዮጵያ ጉዳይ የከረረ አቋም እንዲወስዱ እያደረጋቸው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ [ህወሃት] “ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አስተዳደር እያመራ” ሲሉ አንድ የአሜሪካ ሴናተር ተችተዋል፡፡

ana-gomes-euractiv
አና ጎሜዝ (ፎቶ EURACTIV)

መታሰራቸውን እንደሰሙ “I am very upset with this” ያሉት የአውሮጳ ፓርላማ አባል አና ጎሜዝ የዶ/ር መረራ እስር በጣም እንደሚያሳስባቸው በመግለጽ ለስቃይና እንግልት እንደሚዳረጉ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም “በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በጣም ጥብቅ የሆኑ አካሄዶች ከአውሮጳ ኅብረት በኩል ሊደረግ ይገባል” የሚል ማሳሰቢም ሰጥተዋል፡፡ (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)፡፡

በመቀጠል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ይህንን መግለጫ አወጣ፤ “የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር መረራ ጉዲና በኢትዮጵያ መንግሥት መታሠራቸውን ሰምተናል፡፡ ዘገባው አሳስቦናል፡፡ መንግሥቱ በዶክተር መረራ ላይ ያለውን ማንኛውንም ክሥ ለሕዝብ እንዲያሳውቅ በፅኑ እናበረታታለን፡፡ የመታሠራቸው ነገር እውነት ከሆነ አድራጎቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃ ድምፆችን ለማፈን የሚጣሉት ገደቦች እየተጠናከሩ ለመምጣታቸው አንድ ተጨማሪ ማሳያ ነው የሚሆነው፤ በግልፅ ለመናገር ደግሞ ኢትዮጵያ ያወጀችው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ምናልባት (ተቃዋሚዎችን ዝም ለማሰኘት እና የኢትዮጵያውንን ሕገመንግሥታዊ መብቶቻቸውን ለመካድ የታቀደ ነው እንድንል ያደርገናል፡፡ ይህ ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በታወጀ ጊዜ ከተሰጠው የፖለቲካ ተሃድሶ ተስፋ ጋር የሚጻረር ነው፡፡)” (መግለጫው እዚህ ላይ ይገኛል)

ben cardin
ሴናተር ቤን ካርዲን

“የዶ/ር መረራ ጉዲና እስር በመንግስቱ ላይ የሰላ ትችት የሚሰነዝሩ የፖሊቲካ ተቃዋሚ በመሆናቸው ብቻ ነው። በመሆኑም በአስቸኳይ መለቀቅ አለባቸው” በማለት የጠየቁት በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አንጋፋ አባል የሆኑት ሴናተር ቤን ካርዲን ናቸው፡፡ ሴናተሩ በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ የታሰሩት የተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና እና ሌሎች በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ መሪዎችና ጋዜጠኞች እንዲለቀቁ የጠየቁበትን ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥተዋል።

የምክር ቤት አባሉ አክለውም፤ የኢትዮጵያ መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችን፥ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትንና የሲቪል ማኅበረሰብ ታጋዮችንም እንዲፈታ፣ የፖለቲካ ምሕዳሩን ለማስፋት የሚያስችሉ ተጨባጭ እርምጃዎችን እንዲወስድና እንዲሁም በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎትና አቅርቦቶች ላይ የጣለውን ማዕቀብ እንዲያነሳ፤ ሲሉ ጠይቀዋል። (የሴናተሩ መግለጫ እዚህ ላይ ይገኛል)

chris coons
ሴናተር ክሪስ ኩንስ

በመቀጠልም በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አባል የሆኑት ሴናተር ክሪስ ኩንስ ከዶ/ር መረራ መታሰር ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ መንግሥት እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ያሳሰባቸው መሆኑን በመጥቀስ ይህንን ብለዋል፤ “ይህ የኢትዮጵያ መንግሥት ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አስተዳደር እያመራ ያለበትን አዝማሚያ የሚጠቁም ሌላ አዋኪ ምልክት ነው። ውስብስቡን ውስጣዊ የፖለቲካና የክልል አወቃቀር፤ እንዲሁም ከባድ ሊሰኙ የሚችሉትን ታሪካዊ ገጠመኞቻቸውን እገነዘባለሁ። ይሁንና መንግሥቱ በቅርቡ የወሰዳቸው የኃይል እርምጃዎች ግን ዘለቄታ ላለው ዲሞክራሲ ተጨባጭ አደጋዎች ናቸው” ብለዋል። (ህወሃት ላለፉት 25 ዓመታት አምባገነናዊ ሥርዓት ያላራመደ በሚምስል የተናገሩት) ሴናተሩ የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚከታተሉና በመናገር ነጻነት፣ በመያዶች፣ እና በሌሎች መብቶች ዙሪ በህዝቡ ላይ የተጣለው ገደብ ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አዝማሚያ የሚወስድ መሆኑን ያላቸውን ሥጋት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት ቃለምልልስ አስታውቀዋል፡፡ (እዚህ ላይ ይገኛል)

የተለያዩ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ስለ ዶ/ር መረራ መታሰር በስፋት ዘግበዋል ቢቢሲ፣ አልጃዚራ፣ ኤኤፍፒ ከFrance 24፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ሌሎችም በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ግፍና በደል ከመረራ እስር ጋር አያይዘው ዘግበዋል፡፡

የዶ/ር መረራ ጉዲናን መታሠርና በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ጉዳይ በተመለከተ በአሜሪካ የዴሞክራቲክ ፓርቲ ሴናተሮች በህወሃት ላይ ይህንን መሰሉን አቋም መውሰድ ከኦባማ የሥልጣን መልቀቅ ጋር የሚያይዙ ወገኖች አና ጎሜዝ በመግለጫቸው እንደተናገሩት ጥብቅ አቋም በኢህአዴግ ላይ የሚወሰድበት ሁኔታ ከተፈጠረ አሜሪካም ይህንኑ መስመር ልትወስድ ትችላለች የሚል አስቴየት ይሰጣሉ፡፡ ከቢል ክሊንተን የሥልጣን ዘመን ጀምሮ አሁን ደግሞ በኦባማ አስተዳደር የኢትዮጵያን ጉዳይ በተመለከተ ከአድዋ ወያኔ ባልተናነሰ መልኩ ለህወሃት ግልጽ ድጋፍ ሲሰጡ የቆዩት እንደነ ሱዛን ራይስ የመሳሰሉ ባለሥልጣናት የትራምፕን መመረጥ ተከትሎ ከሥልጣናቸው መልቀቃቸው “መጪውን ጊዜ ለኢህአዴግ ብሩህ” አያደርገውም የሚለውን ተስፋ የሚጋሩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ (የዶ/ር መረራ ፎቶ: Simona Foltyn)

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    December 10, 2016 04:32 am at 4:32 am

    Guys!! Concerning Dr. Mererra Gudina, everyone has his own opinion. Ms. Anna Gomez is not a member of EU parliament. But, since she has a lot of languages knowledge, she is so active around the area. The Europeans have no one language which represents the Union. It was supposed to be English. They didn’t approve the language until now. The individuals who are multi language talent, they have a chance to be hired and work in the union. Ms. Anna Gomez has got that chance. Dr.Mererra broke the laws of State of Emergency. He was invited by individuals or even by Ms Anna Gomez. Through that, he had got a fund raising advantage. I believed he had got the money that he needed. No patiency!! As soon as he got and went back home. I think the moeney is freezed. Poor Mererra!!!

    Reply
  2. Lusif says

    December 14, 2016 04:36 am at 4:36 am

    Even though he is from the old generation who over estimate and over pride in themselves, he is a seasoned politicians. ” A hungry constituents without options will devour on their leaders” is his saying that has strong significant to the current political turmoil.
    Putting him in prison is absolutely wrong and very damaging and a showcase to the true dictatorial behaviour of the ruling party.
    He has appeared couple of times to the US congress and EU parliament. He is a legitimate peaceful opposition party leader. That means he is a cerdiable opposition figure, not only among his constituents, but also in donating western nations.
    Had there been a savvy politician every precautions could have been taken before the ruling party bring out its true nature and trash it’s own image.
    By refraining from putting Dr. MERARA in prison, the ruling party could have shown what it means by transformation — benevolent, tolerant and respecting differencs and oppositions.
    Unfortunately that was not the case, I guess the ruling party will be forced to realise him. That is obvious from different angles.
    I watched a video by Fana broadcasting when one of the political science expert and a Dr. In the field mentioning one of the political machine problems is ” state capture ” He was absolutely right. Few ruling party officials are more powerful than the government and executive body, the judiciary and even the parliament. They act and no government organ asks then. The rest of the process is formality. Such illegal, unethical act has been common place for long time. So many individuals have gone through such kind procedures. It is unfortunate. What else one can say.
    Seeing all the messes and the crises at hand, some of us believe the country is not governed by the elected government as such but the few party leaders. I guess that was what that honorable political science expert talking about when he said state capture. Is that like a government within a government. God mercy!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule