• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዶ/ር መረራ እስር፤ ህወሃትና ምዕራባውያን ፖለቲከኞች

December 7, 2016 09:27 am by Editor 2 Comments

ከአውሮጳ ስብሰባ ወደአገራቸው ሲመለሱ የታፈኑትና በኋላ መታሰራቸው የተሰማው ዶ/ር መረራ ጉዲና የአሜሪካና የአውሮጳ ፖለቲከኞች በኢትዮጵያ ጉዳይ የከረረ አቋም እንዲወስዱ እያደረጋቸው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ [ህወሃት] “ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አስተዳደር እያመራ” ሲሉ አንድ የአሜሪካ ሴናተር ተችተዋል፡፡

ana-gomes-euractiv
አና ጎሜዝ (ፎቶ EURACTIV)

መታሰራቸውን እንደሰሙ “I am very upset with this” ያሉት የአውሮጳ ፓርላማ አባል አና ጎሜዝ የዶ/ር መረራ እስር በጣም እንደሚያሳስባቸው በመግለጽ ለስቃይና እንግልት እንደሚዳረጉ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም “በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በጣም ጥብቅ የሆኑ አካሄዶች ከአውሮጳ ኅብረት በኩል ሊደረግ ይገባል” የሚል ማሳሰቢም ሰጥተዋል፡፡ (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)፡፡

በመቀጠል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ይህንን መግለጫ አወጣ፤ “የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር መረራ ጉዲና በኢትዮጵያ መንግሥት መታሠራቸውን ሰምተናል፡፡ ዘገባው አሳስቦናል፡፡ መንግሥቱ በዶክተር መረራ ላይ ያለውን ማንኛውንም ክሥ ለሕዝብ እንዲያሳውቅ በፅኑ እናበረታታለን፡፡ የመታሠራቸው ነገር እውነት ከሆነ አድራጎቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ነፃ ድምፆችን ለማፈን የሚጣሉት ገደቦች እየተጠናከሩ ለመምጣታቸው አንድ ተጨማሪ ማሳያ ነው የሚሆነው፤ በግልፅ ለመናገር ደግሞ ኢትዮጵያ ያወጀችው የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ምናልባት (ተቃዋሚዎችን ዝም ለማሰኘት እና የኢትዮጵያውንን ሕገመንግሥታዊ መብቶቻቸውን ለመካድ የታቀደ ነው እንድንል ያደርገናል፡፡ ይህ ደግሞ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በታወጀ ጊዜ ከተሰጠው የፖለቲካ ተሃድሶ ተስፋ ጋር የሚጻረር ነው፡፡)” (መግለጫው እዚህ ላይ ይገኛል)

ben cardin
ሴናተር ቤን ካርዲን

“የዶ/ር መረራ ጉዲና እስር በመንግስቱ ላይ የሰላ ትችት የሚሰነዝሩ የፖሊቲካ ተቃዋሚ በመሆናቸው ብቻ ነው። በመሆኑም በአስቸኳይ መለቀቅ አለባቸው” በማለት የጠየቁት በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አንጋፋ አባል የሆኑት ሴናተር ቤን ካርዲን ናቸው፡፡ ሴናተሩ በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ የታሰሩት የተቃዋሚው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና እና ሌሎች በእስር ላይ የሚገኙ የፖለቲካ መሪዎችና ጋዜጠኞች እንዲለቀቁ የጠየቁበትን ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥተዋል።

የምክር ቤት አባሉ አክለውም፤ የኢትዮጵያ መንግስት በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችን፥ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትንና የሲቪል ማኅበረሰብ ታጋዮችንም እንዲፈታ፣ የፖለቲካ ምሕዳሩን ለማስፋት የሚያስችሉ ተጨባጭ እርምጃዎችን እንዲወስድና እንዲሁም በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎትና አቅርቦቶች ላይ የጣለውን ማዕቀብ እንዲያነሳ፤ ሲሉ ጠይቀዋል። (የሴናተሩ መግለጫ እዚህ ላይ ይገኛል)

chris coons
ሴናተር ክሪስ ኩንስ

በመቀጠልም በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የውጭ ጉዳዮች ንዑስ ኮሚቴ አባል የሆኑት ሴናተር ክሪስ ኩንስ ከዶ/ር መረራ መታሰር ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ መንግሥት እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃ ያሳሰባቸው መሆኑን በመጥቀስ ይህንን ብለዋል፤ “ይህ የኢትዮጵያ መንግሥት ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አስተዳደር እያመራ ያለበትን አዝማሚያ የሚጠቁም ሌላ አዋኪ ምልክት ነው። ውስብስቡን ውስጣዊ የፖለቲካና የክልል አወቃቀር፤ እንዲሁም ከባድ ሊሰኙ የሚችሉትን ታሪካዊ ገጠመኞቻቸውን እገነዘባለሁ። ይሁንና መንግሥቱ በቅርቡ የወሰዳቸው የኃይል እርምጃዎች ግን ዘለቄታ ላለው ዲሞክራሲ ተጨባጭ አደጋዎች ናቸው” ብለዋል። (ህወሃት ላለፉት 25 ዓመታት አምባገነናዊ ሥርዓት ያላራመደ በሚምስል የተናገሩት) ሴናተሩ የኢትዮጵያን ጉዳይ የሚከታተሉና በመናገር ነጻነት፣ በመያዶች፣ እና በሌሎች መብቶች ዙሪ በህዝቡ ላይ የተጣለው ገደብ ይበልጥ አምባገነናዊ ወደሆነ አዝማሚያ የሚወስድ መሆኑን ያላቸውን ሥጋት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት ቃለምልልስ አስታውቀዋል፡፡ (እዚህ ላይ ይገኛል)

የተለያዩ ዓለምአቀፍ ሚዲያ ስለ ዶ/ር መረራ መታሰር በስፋት ዘግበዋል ቢቢሲ፣ አልጃዚራ፣ ኤኤፍፒ ከFrance 24፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ሌሎችም በኢትዮጵያ እየተካሄደ ስላለው ግፍና በደል ከመረራ እስር ጋር አያይዘው ዘግበዋል፡፡

የዶ/ር መረራ ጉዲናን መታሠርና በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ጉዳይ በተመለከተ በአሜሪካ የዴሞክራቲክ ፓርቲ ሴናተሮች በህወሃት ላይ ይህንን መሰሉን አቋም መውሰድ ከኦባማ የሥልጣን መልቀቅ ጋር የሚያይዙ ወገኖች አና ጎሜዝ በመግለጫቸው እንደተናገሩት ጥብቅ አቋም በኢህአዴግ ላይ የሚወሰድበት ሁኔታ ከተፈጠረ አሜሪካም ይህንኑ መስመር ልትወስድ ትችላለች የሚል አስቴየት ይሰጣሉ፡፡ ከቢል ክሊንተን የሥልጣን ዘመን ጀምሮ አሁን ደግሞ በኦባማ አስተዳደር የኢትዮጵያን ጉዳይ በተመለከተ ከአድዋ ወያኔ ባልተናነሰ መልኩ ለህወሃት ግልጽ ድጋፍ ሲሰጡ የቆዩት እንደነ ሱዛን ራይስ የመሳሰሉ ባለሥልጣናት የትራምፕን መመረጥ ተከትሎ ከሥልጣናቸው መልቀቃቸው “መጪውን ጊዜ ለኢህአዴግ ብሩህ” አያደርገውም የሚለውን ተስፋ የሚጋሩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ (የዶ/ር መረራ ፎቶ: Simona Foltyn)

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    December 10, 2016 04:32 am at 4:32 am

    Guys!! Concerning Dr. Mererra Gudina, everyone has his own opinion. Ms. Anna Gomez is not a member of EU parliament. But, since she has a lot of languages knowledge, she is so active around the area. The Europeans have no one language which represents the Union. It was supposed to be English. They didn’t approve the language until now. The individuals who are multi language talent, they have a chance to be hired and work in the union. Ms. Anna Gomez has got that chance. Dr.Mererra broke the laws of State of Emergency. He was invited by individuals or even by Ms Anna Gomez. Through that, he had got a fund raising advantage. I believed he had got the money that he needed. No patiency!! As soon as he got and went back home. I think the moeney is freezed. Poor Mererra!!!

    Reply
  2. Lusif says

    December 14, 2016 04:36 am at 4:36 am

    Even though he is from the old generation who over estimate and over pride in themselves, he is a seasoned politicians. ” A hungry constituents without options will devour on their leaders” is his saying that has strong significant to the current political turmoil.
    Putting him in prison is absolutely wrong and very damaging and a showcase to the true dictatorial behaviour of the ruling party.
    He has appeared couple of times to the US congress and EU parliament. He is a legitimate peaceful opposition party leader. That means he is a cerdiable opposition figure, not only among his constituents, but also in donating western nations.
    Had there been a savvy politician every precautions could have been taken before the ruling party bring out its true nature and trash it’s own image.
    By refraining from putting Dr. MERARA in prison, the ruling party could have shown what it means by transformation — benevolent, tolerant and respecting differencs and oppositions.
    Unfortunately that was not the case, I guess the ruling party will be forced to realise him. That is obvious from different angles.
    I watched a video by Fana broadcasting when one of the political science expert and a Dr. In the field mentioning one of the political machine problems is ” state capture ” He was absolutely right. Few ruling party officials are more powerful than the government and executive body, the judiciary and even the parliament. They act and no government organ asks then. The rest of the process is formality. Such illegal, unethical act has been common place for long time. So many individuals have gone through such kind procedures. It is unfortunate. What else one can say.
    Seeing all the messes and the crises at hand, some of us believe the country is not governed by the elected government as such but the few party leaders. I guess that was what that honorable political science expert talking about when he said state capture. Is that like a government within a government. God mercy!!!!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule