የሃገራችን ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ከመቼውም ጊዜ በላይ አሳሳቢ ሆኗል። ኢትዮጵያውያን በተለይ ላለፉት ሶስት ዓመታት በተከታታይና በመረረ ሁኔታ መንግስታቸውን ሲቃወሙ ይታያል። እንዲህ ያለ በተከታታይና በቆራጥነት የተካሄደ ሕዝባዊ ተቃውሞ በሃገራችን ታሪክ አልታየም። ገበሬዎች ሰልፍ ወጥተው “የህወሓት አገዛዝ በቃን” እያሉ ነው። የትናንሽ ከተማ ነዋሪዎች በነቂስ እየወጡ በመረረ ሁኔታ ሲጮሁ ይሄው ሶስት ዓመት ሆነ። ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው አየወጡ ለውጥ እንፈልጋለን ሲሉ ይታያል። ነጋዴው ሱቁን እየዘጋ ተቃውሞውን ያሰማል። ኢትዮጵያውያን ያለ ልክ ለውጥ የፈለጉ መሆናቸውን የሚያሳይ መራራ ተቃውሞ በሃገሪቱ በሰፊው በየቀኑ ይታያል። ይሁን እንጂ ተቃውሞ በሚነሳባቸው አካባቢዎች የመንግስት ታማኝ ወታደሮች፤ በተለይ አጋዚ፤ የፌደራል ፖሊስና ልዩ ታጣቂዎች፤ ደህንነት በሚወስዱት ግብታዊ ርምጃ … [Read more...] about የኢትዮጵያ፤ የውይይትና መፍትሔ መድረክ መግለጫ
meles
AHRE urges international investigation on the current ethnic violence in Eastern Ethiopia
Press Release Association for Human Rights in Ethiopia (AHRE) is very troubled by repeated violent incidents of violence in Eastern Ethiopia that led to the killings of dozens of civilian ethnic Oromos and Ethiopian Somalis in the past week. The recent incident came amid ongoing tension in the border areas of Oromia and Ethio-Somali regional states that had already left several dead from both ethnic groups. Multiple sources reported that at least 16 Oromos were killed by Ethiopian … [Read more...] about AHRE urges international investigation on the current ethnic violence in Eastern Ethiopia
“ዶክተሩ” ደብረጽዮን ምላሽ አለው
“… የአመራሩ ድክመት ድርጅቱን ጎድቷል፤ … የበላይ አመራሩ ሥራውን ሲገመግም ብዙ ጉድለት ተገኝቶበታል” በማለት ለፋና ቃለምልልስ የሰጠው አዲሱ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር የወንበዴዎች ቡድን መሪ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ነው። በበፊቱ አመራር ውስጥ ምክትል ሊቀመንበር የነበረው ደብረጽዮን፤ 35 ቀናት በፈጀውና ዋናው ችግር አመራሩ መሆኑን በገመገመው ስብሰባ መሠረት መባረር ሲገባው ይልቁንም ሊቀመንበር ሆኗል። Capella University ከተባለው የዲግሪ ወፍጮ ቤት “የዶክትሬት ዲግሪ” ተቀብሏል የሚባልለት ደብረጽዮን እንደ ቀድሞ አመራር “የበላይ አመራሩ ጉድለት ተገኝቶበታል” ካለው ድርጅት ራሱን ማግለል ሲገባው ራሱን በዓለምአቀፍ የአሻባሪነት የመረጃ ቋት ውስጥ የተመዘገበው ህወሓት ሊቀመንበር አድርጎ ራሱን ሾሟል። በከሁለት ቀናት በፊት “በጨለንቆ በተፈፅመው የጅምላ ግድያ … [Read more...] about “ዶክተሩ” ደብረጽዮን ምላሽ አለው
ኦህዴድ በህወሓት ላይ ላወጣው መግለጫ ሃይለማርያም ምላሽ ሠጠ
በጨለንቆ በተፈፅመው የጅምላ ግድያ በስተጀርባ ማን ነው ያለው ? የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 87 (3) ስር የአገር መከላከያ ሰራዊት የአገርን ሉዓላዊነት ለማሰከበር ነው የተቋቋመው። በዚሁ ንዑስ አንቀፅ 4 እና 5 ስር የአገር መከላከያ ሰራዊት በማንኛውም ጊዜ ለህገመንግስቱ ታዛዥ በመሆን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ውግንና ሳያሳይ ነፃ ሆኖ የአገር ደህንነት የመጠበቅ ስራውን እንደሚሰራ ይደነግጋል። ይሄው የመከላከያ ሰራዊቱ ከውጭ የሚመጣውን የአገሪቱን ጠላት ለመከላከል በአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች የተገነባ ከተቋቋመለት አላማ ውጭ ታሪካዊ ስህተቶችን በህዝቦች ላይ ሲፈፅም ታይቷል። የህገ-መንግስቱ አንቀፅ 8 (1-5) ስር የአገሪቱ ህዝቦች ሉዓላዊነት አስመልክቶ የአገሪቱ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦና ህዝቦች የኢተዮጵያ ሉዓላዊ የስልጣን ባለቤት መሆናቸው ይደነግጋል። ይህ ህገ-መንግስት የአገሪቷ … [Read more...] about ኦህዴድ በህወሓት ላይ ላወጣው መግለጫ ሃይለማርያም ምላሽ ሠጠ
ግልፅ ደብዳቤ ለህወሃት
የደብዳቤውን ሙሉ ቃል ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው። … [Read more...] about ግልፅ ደብዳቤ ለህወሃት
አልሰሙም አልታረሙም
እነሆ ራሳቸው በጠሩዋቸው ጉባዔዎችና ኮንፍረንሶች ላይ ሁሉ በተደጋጋሚ ተነግረዋል አልሰሙም፤ ተመክረዋልም አልታረሙም። እኒህም የኢትዮጵያ ገዢዎች የኢህአዴጋውያን አዛዦች የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር ህወሃታውያን ናቸው። ማስረጃ ቢባል ማርሻል መለስ ከመራው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጉባዔ ጀምሮ እስከ ቅርብ ጊዜ የዘለቁት መሰል ጉባዔዎች ዋቢዎቻችን ናቸው(1)። እነሆም ህወሃታውያኑ በወጣትነት ዘመናቸው በሽፍትነትና ዘረኝነት እንደታበዩ ገድለው ዘርፈውና አጥፍተው በጎልማሳነታቸው ምኒልክ ቤተመንግሥትን በጠመንጃ ማረኩ። እነሆም በስተርጅና ዘመናቸው ባልገነቡት ቤተመንግሥት እየፏለሉ ከሽፍትነት የድውይ አስተሳሰባቸው፤ ከድኩም ባህሪያቸው፤ ከመሃይምነታቸው፤ ከመሰሪ ተፈጥሯቸው፤ ከናዚስት ዕምነታቸው ይታረሙና ይፀዱ ዘንድ ግን ከቶም አልተቻላቸውም። እነሆም በኢትዮጵያ መንበር ላይ ተኮፍሰው … [Read more...] about አልሰሙም አልታረሙም
ለጨለንቆ ሰማዕታት
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ነፍጥ አንጋቢዎች በግፍ ለተጨፈጨፉት የጨለንቆ ወገኖች በነቀምቴና በአዳማ ተማሪዎች መታሰቢያ አድርገዋል። የቢቢሲ የኦሮሚኛ ዘገባ እንዳስረዳው ከአንድ ቤት አምስት ሞተዋል። (ፎቶዎቹ ከማህበራዊ ድረገጾች የተገኙ ናቸው) በነቀምቴ ወለጋ አዳማ ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ለጨለንቆ ሰማዕታት
ሆላንድ ዜጋቸውን ጨፍጭፈው ለሚመጡ ወንጀለኞች መደበቂያ ገነት አትሆንም – ፍትህ ሚኒስትር
መቶ አለቃ እሸቱ አለሙ እድሜልክ እስራት ተፈረደባቸው ዛሬ ዲሴምበር 15 ቀን 2017 ከቀትር በኋላ በሆላንድ ዘሄግ ከተማ የዋለው ችሎት በመቶ አለቃ በእሸቱ አለሙ አቃቤ ህግ ባቀረበባቸው የጦር ወንጀል ክስ እድሜልክ እስራት በይኖባቸዋል። በተጠቀሳባቸው ክስ በሙሉ ጥፋተኛ ተብለዋል። ከሁለተኛው አለም ጦርነት በኋላ እንዲህ አይነት ፍርድ በሆላንድ ሃገር ሲሰጥ የመጀመርያው መሆኑን አቃቤ ህግ ተናግረዋል። በሃገሪቱ ህግ የእድሜ ልክ እስራት አመክሮ የለውም። ዜጋቸውን ጨፍጭፈው ለሚመጡ ወንጀለኞች የመደበቅያ ገነት እንደማትሆን የሆላንድ ፍትህ ሚኒስትር አስታወቁ። አቶ እሸቱ አለሙ በውሳኔው ሰዓት ችሎቱ ላይ መገኘት አልፈለጉም። በአራት ዳኞች በተሰየመው በዚህ International Crime Chamber የተሰኘ ችሎት የመሃል ዳኛዋ ማርየት ሬከንስ የፍርድ ውሳኔውን ባሰሙበት ወቅት … [Read more...] about ሆላንድ ዜጋቸውን ጨፍጭፈው ለሚመጡ ወንጀለኞች መደበቂያ ገነት አትሆንም – ፍትህ ሚኒስትር
ከ424 ዜጎች ጭፍጨፋ፤ ከ14 ዓመት መሬት ነጠቃ በኋላ የጋምቤላ “ኢንቨስትመንት” 9ቢሊዮን ብር ያህል ከስሯል
ጋምቤላን በረሃ አድርጎ፤ ሕዝቧን ገድሎ፤ በተለይ የአንድ ክልል “ዜጎችን” ብቻ ጠቅሞ በጋምቤላ የተተገበረው “ኢንቨስትመንት” ዘጠኝ ቢሊዮን ብር ያህል የማይከፈል ዕዳ ውስጥ መዘፈቁን ህወሓት/ኢህአዴግ አመነ። ልክ የዛሬ 14ዓመት ነበር መለስ በመራው ስብሰባ ላይ “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” የሚለው ትዕዛዝ የወጣው። በዚህም መሠረት 424 ንጹሃን በግፍ ተጨፈጨፉ፤ መሬታቸው ተነጠቀ፤ ለባለሃብቶች በሃያ ብር (በወቅቱ 1 ዶላር) ሒሳብ ተቸበቸበ። ህወሓት ደርግን ሲወነጅልበት የነበረውን ግዳጅ ሠፈራና መንደር ምሥረታ በአኙዋክ ወገኖች ላይ ተፈጸመባቸው። ይህ ሁሉ የሆነው ለ"ልማት" ነው ተባለ። ሪፖርተር (8 November 2017) ባወጣው ዘገባ ላይ እንዳሰፈረው “ለጋምቤላ እርሻዎች የተሰጠው ብድር የልማት ባንክን መመለስ ያልቻሉ ብድሮች ወደ ዘጠኝ ቢሊዮን ብር … [Read more...] about ከ424 ዜጎች ጭፍጨፋ፤ ከ14 ዓመት መሬት ነጠቃ በኋላ የጋምቤላ “ኢንቨስትመንት” 9ቢሊዮን ብር ያህል ከስሯል
“እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም”
እነዚህም የህወሓት ነፍሰበላዎች ይፈለጋሉ! የሰላም ሰዎች የሆኑት አኙዋኮች ከህወሓት ጋር መቃቃር ውስጥ የገቡት ገና ከጅምሩ ነበር። የቀድሞው የአኙዋክ ምክርቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ኦባንግ ሜቶ እንደሚሉት ችግሩ የተያያዘው ህወሓት የጋምቤላን ለም ምድር የራሱ ለማድረግ ከመፈለጉ ጋር ነው። ህወሓት ሥልጣን ላይ እንደተቆናጠጠ የጋምቤላን ብቸኛ ጄኔሬተር በመንቀል ከመውሰድ አልፎ በአሎሮ ግድብ ላይ የነበሩትን ወደ 400 የሚሆኑ ማሽነሪዎች እና የእርሻ መሣሪዎች በምሽት ወደ ትግራይ ነቅሎ ወስዷል ይላሉ አቶ ኦባንግ። በመቀጠልም ተዝቆ የማያልቀውን የጋምቤላን ድንቅ ሃብት በረኸኞቹ ህወሃቶች ለመዝረፍ ውሳኔያቸው አደረጉ። “መሬቴን አላስነካም” በሚለው አኙዋክና ህወሓት መካከል ያለውን መቃቃር አንድ “ዕልባት” ላይ ለማድረስ በሚል አኙዋክን ማጥፋት የህወሓት ቀዳሚ ሃሳብ ሆነ እንደ አቶ … [Read more...] about “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም”