• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም”

December 13, 2017 12:36 am by Editor Leave a Comment

  • እነዚህም የህወሓት ነፍሰበላዎች ይፈለጋሉ!

የሰላም ሰዎች የሆኑት አኙዋኮች ከህወሓት ጋር መቃቃር ውስጥ የገቡት ገና ከጅምሩ ነበር። የቀድሞው የአኙዋክ ምክርቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ኦባንግ ሜቶ እንደሚሉት ችግሩ የተያያዘው ህወሓት የጋምቤላን ለም ምድር የራሱ ለማድረግ ከመፈለጉ ጋር ነው። ህወሓት ሥልጣን ላይ እንደተቆናጠጠ የጋምቤላን ብቸኛ ጄኔሬተር በመንቀል ከመውሰድ አልፎ በአሎሮ ግድብ ላይ የነበሩትን ወደ 400 የሚሆኑ ማሽነሪዎች እና የእርሻ መሣሪዎች በምሽት ወደ ትግራይ ነቅሎ ወስዷል ይላሉ አቶ ኦባንግ። በመቀጠልም ተዝቆ የማያልቀውን የጋምቤላን ድንቅ ሃብት በረኸኞቹ ህወሃቶች ለመዝረፍ ውሳኔያቸው አደረጉ።

“መሬቴን አላስነካም” በሚለው አኙዋክና ህወሓት መካከል ያለውን መቃቃር አንድ “ዕልባት” ላይ ለማድረስ በሚል አኙዋክን ማጥፋት የህወሓት ቀዳሚ ሃሳብ ሆነ እንደ አቶ ኦባንግ ሜቶ ገለጻ። ጉዳዩን አቅጣጫ ለማስቀየርም ከዚህ በፊት ተነስተው የማያውቁ የጎሣ ግጭቶችን ህወሃት መቆስቆስ ጀመረ። ሸመጋይ መስሎም የመከላከያ ሠራዊት በቦታው ማስፈር ተግባሩ አደረገ። በመጨረሻም “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” የሚለው ትዕዛዝ ወጣ። “Let us kill them all! From today forward there will be no Anuak! There will be no more Anuak land! No one will arrest us! Erase the trouble makers!”

መለስ በመራው ስብሰባ ላይ፤

አዲሱ ለገሰ፣

ስብሃት ነጋ፣

በረከት ስምዖን፣

ኦሞት ኡባንግ ኡሎም (ያኔ የጋምቤላ ደኅንነት ኃላፊ)፣

አባይ ጸሃዬ፣

ሳሞራ ዩኑስ፣

ዮሐንስ ገብረመስቀል (ያኔ የወታደራዊ ስለላ ኃላፊ)፣

አባዱላ ገመዳ ተገኝተዋል።

የዕቅዱ አፈጻጸም ላይ አኙዋኮች እንዲጨፈጨፉ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጠው ጸጋይ በየነ (በጋምቤላ የሠራዊቱ ኃላፊ) ሲሆን ፈቃዱ ያገኘው ያኔ የፌዴራል ጉዳይ ኃላፊ ከነበረው ገብረአብ በርናባስ ነበር። የፖሊስ ኃላፊው ታደሰ ኃይለሥላሴም አኙዋኮችን የማስገደል ትዕዛዝ በመስጠቱ ውስጥ ነበረበት። ይህ ሁሉ በማስረጃ የተረጋገጠ መሆኑን አቶ ኦባንግ ያስረዳሉ።

“እንግዲህ ይህ ዘር የማጽዳት ዘመቻ በ1996 ከተካሄደ በኋላ የጋምቤላ መሬት እንደ ካሩቱሪና ሳውዲ ስታር ላሉ ባለሃብቶች በአንድ ዶላር ሒሳብ የተቸበቸበው። ብዙ ጊዜ ለውጭ ባለሃብት ተሰጠ ይባላል እንጂ ከጋምቤላ መሬት 78 በመቶውን የተቀራመቱት ትግሬዎች ሲሆኑ 12 በመቶው ብቻ ነው ለውጭ ባለሃብቶች የተሰጠው። ከዚህ ሌላ ይህ ሁሉ መሬትና ብድር ለትግራይ ተወላጆች ተሰጥቶ የእርሻ ልማት ባለቤቶች ሲሆኑ አንድም አኙዋክ ይህንን ዕድል አላገኘም፤ ይልቁንም ለውሃ ቅርብ የነበሩና በአባቶቻቸው መሬት ላይ የሚገኙትን አኙዋኮች በልማት ሰበብ በህወሃት ተፈናቅለው ወደ ሌላ ቦታ ሰፍረዋል” በማለት ኦባንግ ይናገራሉ።

ኦሞት ኦባንግ ኡሎም ከአገር ኮብልሎ ከመውጣቱ በፊት ከሙስና ጋር በተያያዘ ወንጀለኛ እንደሆነ ሲነገረው “እኔ ከተወነጀልኩና ከታሰርኩ ከእኔ ጋር አዜብ መስፍን አብራ መታሠር አለባት” ማለቱ ይታወሳል።

ከታህሳስ 23 ቀን 2004 ዓ ም ጀምሮ ሟቹ መለስ ዜናዊ በላከው አስገምጋሚዎች ለሳምንት በጋምቤላ በተካሄደ አውጫጪኝ ኦሞት ኦባንግ ኡሎም “የአኙዋክ ተወላጆችን አስጨፍጭፈሃል” የሚል መነሻውና ዓላማው ግልጽ ያልሆነ ጥያቄ ቀርቦለት ነበር። በወቅቱ ግምገማው ላይ የነበሩ እንዳሉት ለዚህ ጥያቄ ኦሞት “እኔ በዚህ ጉዳይ ተጠያቂ ከሆንኩ መሳሪያና ወታደር የሰጠኝ መለስም ይታሰራል” በማለት መልስ ሰጥቶ ነበር።

አስራ አራት ዓመት ቢያልፍም፤ መለስም ወደ ከርሰ መቃብር እንደ ቡሽ ክዳን ተስፈንጥሮ ቢወርድም፤ ኦሞትም ሆነ የህወሓት ነፍሰበላዎች አሁንም ይፈለጋሉ!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics, Social Tagged With: anuak, Anuak Massacre, eprdf, Gambella, Left Column, meles, omot, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule