• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጋምቤላ ልጆቿ በጥይት የተጨፈጨፉበት ምክንያት ይፋ ሆነ!

December 16, 2016 11:46 pm by Editor Leave a Comment

ዜናውን “መገጣጠም” ሲሉ በቁጭት ይገልጹታል። የትግራይ “ባለሃብቶች” በጋምቤላ መበደላቸውን ለውጭ አገርና ለአገር ውስጥ መገናኛዎች ያስታወቁበት ዕለትና የአኙዋክ ምስኪኖች በምድራቸው በግፍ የተጨፈጨፉበት ቀን ተሳሳመ። ደም እንደጎርፈ በፈሰሰበት፣ ንጹሃን እንደ እንስሳ የተቀሉብት ቀን ተዘንግቶ በሙታን ዱካ ተተክተው “ተበደልን” ያሉ የብሶት ዜና ተሰማበት – ታህሳስ 4፤ 2009 (ዲሴምበር 13 ቀን 2016)።

ታህሳስ 3፤ 1996 ዓ.ም በጋምቤላ ለተጨፈጨፉት ንጹሃኖች ፍትህና ርትዕ የሚሰጥ አካል እስካሁን አልተገኘም። በስደት ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያና የተለያዩ አገራት የሚኖሩ የአኙዋክ ተወላጆች ያንን ቀን ሲያስቡት አሁን ድረስ ያነባሉ። በመለስ አመራር ሌሎች በፌዴራል መንግሥት ስም የሚታወቁ የህወሃት ሰዎች ትዕዛዝ ከ400 በላይ አኙዋኮች ተረሽነዋል። አሁን እነሱ አፈር ውስጥ ሆነው ደማቸው ከላይ ይጮሃል።13anuakmemorial

በእነሱ ደምና አጽም ላይ ንግድ ጦፏል። ከያቅጣጫው ከተፈጥሮ ዛፎቿ ጀምሮ ጋምቤላ እየታለበች ነው። ካሩቱሪ፣ ሳውዲ ስታር እና 1000 የሚሆኑ የትግራይ “ባለሃብቶች” /ነባር ታጋዮች ናቸው/ በዚሁ የደም መሬት ላይ ሰፍረው ይበደራሉ፣ የክልሉን ህዝብ ጭሰኛ አድርገው ያመርታሉ፣ ይነግዳሉ፣ ይለውጣሉ፣ …

ታህሳስ 4፤ 2009 (ዲሴምበር 13 ቀን 2016) የቪኦኤ የትግራይ ዘጋቢ “የጋምቤላ እርሻ ባለሐብቶች የሕብረት ሥራ ማኅበር” በሚል ስያሜ የሚጠራውን የቀድሞ የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ታጋዮች “በደል” ይፋ አድርጓል። የማህበሩን ሊቀ መንበር አቶ የማነ ሰይፉን አነጋግሯል።

ማህበሩ ያሰማው ቅሬታ የትግራይ ተወላጅ በመሆናቸው ብቻ በደል እንደደረሰባቸው ነው። አንድ ሺህ የሚሆኑት የትግራይ ባለሃብቶች ያመረቱት ማሳ ላይ እያለ ብድር መከልከላቸው ሆን ተብሎ የተደረገና በማንነታቸው የደረሰባቸው በደል ነው። ከ2001 ጀምሮ ወደ ጋምቤላ ባለሃብት ሆነው የገቡት የትግራይ ተወላጆች፣ የባንክ ብድር ማግኘት የጀመሩት ከ2005 ጀምሮ ሲሆን በያዝነው ዓመት ተቋርጦባቸዋል። ይህም የሆነው እነሱን አክስሮ ከጫወታ ውጪ ለማስገባት ነው ብለዋል።

ቀደም ሲል በሄክታር 30 ብር ግብር ይከፍሉ ነበር አሁን በቅጽበት ወደ 111 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል። የባንክ ብድር ወለድም ከ8.5 ወደ 12.5 ከፍ እንደተደረገባቸው ያስረዱት ሊቀመንበሩ፣ ደጋግመው የተናገሩት ድርጊቱ ሆን ተብሎ እነሱ ላይ በተነጣጠረ ሴራ መሆኑን ነው።anuaks-killed

አበዳሪው ባንክ በበኩሉ ድራቢ የተወሰደ መሬት ስላለ ማጣራት እየተደረገ መሆኑንና ማጣራቱ ሲያልቅ ብድሩ እንደሚፈቀድ ተናግሯል። እንደ ባንኩ አባባል ውስብስብ ነገር ያለ አይመስልም። ባንኩ እንዲህ ያለ አቋም ካለው “በማንነታችን ሳቢያ /ትግሬ ስለሆን ተበደለን/” የሚለው አቤቱታ ለምን አስፈለገ? ሲሉ በርካቶች ይጠይቃሉ። ጉዳዩን ለተለያዩ ዓለም አቀፋዊ መገናኛዎች ማሳወቁስ “ለምን ይሆን” ሲሉ ዜናውን የሚመረምሩ አሉ። ዜናው ሲጠናቀርስ የተወገዘው የክልሉ ሃሳብ ለምን አልተካተተም? ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ነው? (ይህም ቢሆን አልተገለጸም) ወይስ ሌላ ምክንያት አለው? ግብር የሚጥል፣ ቀረጥ የሚሰበስብ፣ መሬቱን ሰፍሮ የሚሰጠው አካል ለምን ተዘለለ?

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) ነባር ታጋዮቼ የሚላቸውን በፖለቲካ ጉዳዩ፣ በአካል ጉዳትና በእድሜ ሲቀንስ አቅም እያስጨበጠ ወደ ባለሃብትነት ከፍ እንዳደረጋቸው ራሳቸው ታጋዮች በተለያዩ ጊዜያት ተናግረዋል። እነሱ ባይናገሩም በርካታ ማሳበቂያ ማስረጃዎች ስላሉ ጉዳዩ ለክርከር የሚቀርብ እንዳልሆነ የበርካቶች እምነት ነው፤ የጸረ ሙስና ኮሚሽንን ጨምሮ!!

በጎንደር የተነሳውን ተቃውሞ አቅጣጫ ለማስቀየር “ትግሬ በመሆናችን ተፈናቀልን” የሚለውን ስባሪ ዜና በዓለምአቀፍ ደረጃ ያጎላው ህወሃት፣ ዓላማው ለሚወሰደውና እየወሰደ ላለው እርምጃ ዓለምአቀፋዊ ድጋፍ ለማግኘት እንደሆነ መዘገቡን ያስታወሱ፣ “በጋምቤላ ካሩቱሪ ወስዶት የነበረውን መሬት ለትግራይ ባለሃብቶች እና ለሳዑዲ ለመሸጥ በመታሰቡ ቅድመ ሁኔታ ለማመቻቸት ነው” የሚሉ እየተሰሙ ነው።anuak man

የክልሉን የመከራከርና “ለምን” ብሎ የመጠየቅ፣ ከህወሃት ተጽዕኖ ውጪ በራሳቸው ተደራጅተውና ከባንክ ተበድረው መስራት የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችላቸው የመጠየቅና ቀደም ሲል በተፈጸመው ግፍ የመቆጨት ስሜት ያላቸውን ሃላፊዎች ለማራገፍ ሆን ተብሎ የተደረገ እንደሆነ እነዚሁ ክፍሎች ይናገራሉ። ለዚህም ተግባራዊነት ሃይለማርያም ደሳለኝ የሚመራ አንድ ቡድን መቋቋሙን እንደ ማስረጃ ያስቀምጣሉ።

በጋምቤላ በልማት ስም ሊተካ የማይችል የተፈጥሮ ደን ወድሟል። ተጨፍጭፎ ተቸብችቧል። ተወላጆች ተፈናቅለዋል። ከሁሉም በላይ ምስኪኖች ታርደዋል። በሦስት ቀን ውስጥ ከ400 በላይ ንጹሃን እንደ ተባይ ተረፍርፈዋል። በብሔር ብሔረሰቦች ስም ይምል የነበረው መለስ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማዞር የሠራው ድራማ በክልሉ መሪዎች ተጋልጧል። ዓለምአቀፉ የወንጀለኛ ፍርድቤት (አይ.ሲ.ሲ.) የመለስን ፋይል ገምዶ ክስ ሊመሰርትበት በዝግጅት ላይ እንዳለ ሞት እንደ ቡሽ ክዳን አስፈንጥሮት ሌሎች የቀመሱትን አፈር ልሷል። ከዚህ በፊት ግን “እኛን የሚያሳስበን በሊዝ ያልሸጥነው መሬት ነው” በማለት መለስ መናገሩ ይታወሳል፡፡

“ትግሬዎቹ ለገንዘብ፤ አኙዋክ ግን ለደሙ ያለቅሳል” ኦባንግ ሜቶ 

የአኙዋኮች በግፍ ከተጨፈጨፉበት ጊዜ ጀምሮ ጉዳዩን የሚከታተሉት አቶ ኦባንግ ሜቶ ለጎልጉል በሰጡት አጭር የስልክ ቃለምልልስ የትግራይ ተወላጆች ያነሱትን ጥያቄ “ፍጹም ሰብዓዊነት የሌለበት በሙታን ደም መቀለድ” ይሉታል፡፡

የአኙዋክ ሕዝብ ከህወሃት ጋር ገና ከጅምሩ ስምምነት እንደሌለው ያወሱት ኦባንግ የጥሉ ዋንኛ መነሻ ህወሃት የጋምቤላን ለም ምድር የራሱ ለማድረግ ከመፈለጉ ጋር ያያይዙታል፡፡ ህወሃት ሥልጣን ላይ እንደተቆናጠጠ የጋምቤላን ብቸኛ ጄኔሬተር በመንቀል ከመውሰድ አልፎ በአሎሮ ግድብ ላይ የነበሩትን ወደ 400 የሚሆኑ ማሽነሪዎች እና የእርሻ መሣሪዎች በምሽት ወደ ትግራይ ነቅሎ ወስዷል ይላሉ ኦባንግ፡፡ በመቀጠልም ተዝቆ የማያልቀውን የጋምቤላን ድንቅ ሃብት በረኸኞቹ ህወሃቶች ለመዝረፍ ውሳኔያቸው አደረጉ፡፡meles-genocide

መሬቴን አላስነካም በሚለው አኙዋክና ህወሃት መካከል ያለውን መቃቃር አንድ “ዕልባት” ላይ ለማድረስ በሚል አኙዋክን ማጥፋት የህወሃት ቀዳሚ ሃሳብ ሆነ እንደ አቶ ኦባንግ ሜቶ ገለጻ፡፡ ጉዳዩን አቅጣጫ ለማስቀየርም ከዚህ በፊት ተነስተው የማያውቁ የጎሣ ግጭቶችን ህወሃት መቆስቆስ ጀመረ፡፡ ሸመጋይ መስሎም የመከላከያ ሠራዊት በቦታው ማስፈር ተግባሩ አደረገ፡፡ በመጨረሻም “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም የሚለው” ትዕዛዝ ወጣ፡፡ መለስ በመራው ስብሰባ ላይ አዲሱ ለገሰ፣ ስብሃት ነጋ፣ በረከት ስምዖን፣ ኦሞት ኡባንግ ኡሎም (ያኔ የጋምቤላ ደኅንነት ኃላፊ)፣ አባይ ጸሃዬ፣ ሳሞራ ዩኑስ፣ ዮሐንስ ገብረመስቀል (ያኔ የወታደራዊ ስለላ ኃላፊ)፣ አባዱላ ገመዳ ተገኝተዋል፡፡ የዕቅዱ አፈጻጸም ላይ አኙዋኮች እንዲጨፈጨፉ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሰጠው ጸጋይ በየነ (በጋምቤላ የሠራዊቱ ኃላፊ) ሲሆን ፈቃዱ ያገኘው ያኔ የፌዴራል ጉዳይ ኃላፊ ከነበረው ገብረአብ በርናባስ ነበር፡፡ የፖሊስ ኃላፊው ታደሰ ኃይለሥላሴም አኙዋኮችን የማስገደል ትዕዛዝ በመስጠቱ ውስጥ ነበረበት፡፡ ይህ ሁሉ በማስረጃ የተረጋገጠ መሆኑን አቶ ኦባንግ ያስረዳሉ፡፡

“እንግዲህ ይህ ዘር የማጽዳት ዘመቻ በ1996 ከተካሄደ በኋላ የጋምቤላ መሬት እንደ ካሩቱሪና ሳውዲ ስታር Wanted-omotላሉ ባለሃብቶች በአንድ ዶላር ሒሳብ የተቸበቸበው፡፡ ብዙ ጊዜ ለውጭ ባለሃብት ተሰጠ ይባላል እንጂ ከጋምቤላ መሬት 78 በመቶውን የተቀራመቱት ትግሬዎች ሲሆኑ 12 በመቶው ብቻ ነው ለውጭ ባለሃብቶች የተሰጠው፡፡ ከዚህ ሌላ ይህ ሁሉ መሬትና ብድር ለትግራይ ተወላጆች ተሰጥቶ የእርሻ ልማት ባለቤቶች ሲሆኑ አንድም አኙዋክ ይህንን ዕድል አላገኘም፤ ይልቁንም ለውሃ ቅርብ የነበሩና በአባቶቻቸው መሬት ላይ የሚገኙትን አኙዋኮች በልማት ሰበብ በህወሃት ተፈናቅለው ወደ ሌላ ቦታ ሰፍረዋል” በማለት ኦባንግ ይናገራሉ፡፡

በአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ስለተዘገበው ዜና ከጎልጉል ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ “ሰምቼዋለሁ፣ እጅግ በጣም አዝኛለሁ፤ በተለይ የአኙዋክ ሕዝብ ፍትሕ ሳያገኝ ደሙ እየጮኸ 13 ዓመታት ማለፉ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በሐዘን እየታሰበ ሳለ የትግራይ ተወላጆች ይህንን ዓይነት ነገር በዚያኑ ቀን ማሰማታቸው የአኙዋክን ሕዝብ እንደገና እንደገደሉት የሚቆጠር ነው፤ ዜናውን የሰማ አንዱ ወዳጄ ልቤን እንደገና ቀድደው አወጡት ነው ያለኝ፤ ሰብዓዊነት ያስፈልጋል፤ እነርሱ እያለቀሱ ያሉት ለገንዘባቸው ነው ያውም በብድር ለዘረፉት ገንዘብ ነው፤ የአኙዋክ ህዝብ ደም እያነባ ያለው ለፈሰሰበት ደም ነው” ያሉት ኦባንግ ሜቶ በሌላ በኩል እነዚሁ የትግራይ ተወላጆች ይህንን ዓይነት አቤቱታ ማሰማታቸው የአኙዋክ ደም የፈሰሰውና መሬቱን የተዘረፈው እነርሱን ለማበልጸግ ነው ሲባል የነበረውን ያለጥርጥር ያረጋግጣል ብለዋል፡፡ ከዚህም ሌላ በዚህ “በደል ደረሰብን” በሚል ሰበብ የካሩቱሪን መሬት ለትግራይ ልጆች ለመስጠት የሚደረግ ቅድመ ዝግጅት ተብሎ ሊታይ ይችላል በማለት ኦባንግ ያስረዳሉ፡፡

obang-las-vegas
“ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ በቬጋስ

በአሁኑ ጊዜ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኦባንግ ሜቶ ይህንን የህወሃት አሠራር በዘር ላይ የተመሠረተ የአፓርታይድ ሥርዓት ይሉታል፡፡ “ኢትዮጵያ በቅኝ ያልተገዛች አገር ብትሆንም በጣሊያን ጊዜ የነበሩት ባንዳዎች የልጅ ልጆች አሁን አገሪቱን በዘር ላይ ባተኮረ አፓርታዳዊ ስልት እየዘረፉ፤ ራሳቸውን እየጠቀሙ ነው” በማለት በግልጽ ያስረዳሉ፡፡

ምክንያቱም በኢትዮጵያ ውስጥ አንድን ዘር ለማበልጸግ ሲባል ጉራጌው ከመርካቶ ተፈናቅሎ መርካቶ የትግራይ ተወላጆች ሆናለች፤ ወልቃይት ከህዝቡ ተወስዶ ለትግራይ ተሰጥቷል፤ ተራራም ሳቀር ተሰርቋል፤ በማስተር ፕላን ስም የኦሮሞ ወገኖች መሬት ተወስዶ ለትግራይ ተወላጆች ማበልጸጊ እንዲሆን ተደርጓል፤ በደቡብ ኦሞ ሱርማዎችና ሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎች በኢሰብዓዊነት መሬታቸው ተነጥቋል፤ ኮንሶ የግፍ ምድር ሆኗል፤ “ዝም የተባለው ዳርፉር” – ኦጋዴን ሕዝቡ “አናስተርፋችሁም” ተብለው ተጨፍጭፈዋል፤ ዝርዝሩ አያቆምም፡፡ ለዚህ ሁሉ ዋንኛ መፍትሔው ህወሃት በቀደደው የዘር ቱቦ መፍሰስ ሳይሆን “ከዘር ይልቅ ሰብዓዊነትን ማስቀደም” ነው ይላሉ “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በዕርቅ ላይ የተመሠረተ ርትዓዊ ፍትሕ ለኢትዮጵያ የሚበጅ መፍትሔ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule