የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው፤ የሕግ ማስከበር ዘመቻው የአማራን ህዝብ አንድነት ለማጠናከር ያለመ ነው ሲሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ/ር) አስታውቀዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ ከጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ጋር እየመከሩ ነው። የጎንደር ከተማን ሰላምና እድገት ለማረጋገጥ መሰራት ስላለባቸው ጉዳዮች የጋራ አቋም ለመያዝ ያለመ የምክክር መድረክ እየተካሄደ ያለው። ጎንደር የስልጣኔያችን ምልክት፤ የሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ሐብቶች መናገሻ የኾነች የዓለም መዳረሻ ከተማ መኾኗን ያነሱት ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ ገጽታዋን ለማጠልሸት በሐይማኖትና በብሔር ሽፋን ግጭት እንዲቀሰቀስ የሚሰሩ ሐይሎች መበራከታቸውን ገልጸዋል። በቅርቡ በጎንደር ከተማ የተከሰተው ግጭትም የሕዝቡን ማኅበራዊ እሴት የማይመጥን … [Read more...] about “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል
amhara region
“ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ
በአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አዘጋጅነት “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መሪ ሃሳብ ለክልሉ አርሶ አደሮች የግብርና ሜካናይዜሽን መሳሪያዎች ርክክብ መርሐ ግብር ተካሂዷል። የግብርና ሜካናይዜሽን መሳሪያዎች በክልሉ የቴክኖሎጂ አቅርቦት ውስንነትን ለመቅረፍና የግብርና ሥራን በዘመናዊ መንገድ በመከወን ምርታማነትን ለማሳደግ ያግዛሉ ተብሏል። በተካሄደው ርክክብ÷ ትራክተር፣ ኮምባይነር፣ አነስተኛ መውቂያ መሳሪያዎች እንዲሁም የውሃ መሳቢያ ፓምፖች እንደሚገኙበትም ነው የተመላከተው። በዛሬው ዕለት 136 ትራክተሮች በክልሉ ግብርና ቢሮ በኩል ለስርጭት የቀረቡ ሲሆን÷ ከጥር ወር ጀምሮም 324 ትራክተሮችን ለአርሶ አደሮች ማስተላለፍ መቻሉ በመርሐ ግብሩ ተገልጿል። በርክክብ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ÷ ያለንን የግብርና … [Read more...] about “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ
“ነገርን ከሥሩ ውሃን ከጥሩ”
የአማራ ሕዝብ ምንም አይነት የመሰረተ ልማት ባልነበረበት፣ የግንኙነት አውታሮች እጅግ ኋላ ቀር በሆኑበት ሁኔታ አንድነቱን አስጠብቆ ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን ገንብቷል። የባህል መስተጋብሩና ሌሎች ማህበራዊ እውነታዎቹ ከራሱ አልፎ ኢትዮጵያን ድርና ማግ ሆኖ አስተሳስሯል። የሁለቱ ታላላቅ ኃይማኖቶች (ክርስትና እና እስልምና) መንፈሳዊ መሪዎች መፍለቂያ መሆኑ አጥር የማይበጅለት አቃፊና ተጋሪ የማንነት ባለቤት አድርጎታል። ለዚህ በርካታ ማሳያዎችን ማቅረብ የሚቻል ቢሆንም የነገረ-ፍሬየ መዳረሻ አይደለምና እዘለዋለሁ። ሊሰመርበት የሚገባው የአማራ ሕዝብ አንድነት ግን የሰላሳ ዓመታት ሳይሆን በሺህ የሚቆጠሩ ዓመታትን የተሻገረ ነው። የዳማት ዙፋን ወራሽ፣ የአክሱም ሥልጣኔ ባለቤት ነው!! ይህ የአማራ ያገጠጠ ሃቅ በትህነግ ዘመን ለመፍጠር ከታሰበው አማራ እና ፖለቲካዊ … [Read more...] about “ነገርን ከሥሩ ውሃን ከጥሩ”
የትህነግ አዲሱ ሤራ – አማራን በውክልና እልህ ውስጥ መክተት
* የአማራ ክልል ሰላም መሆን ለትህነግ ሤራ ስኬት ዕንቅፋት መሆኑ ተገመገመ ስብሃት ነጋ የሚባለው የትህነግ (ህወሃት) ማፊያ ቡድን አውራ ገና ወደ በረሃ ከመግባቱ በፊት አዲስ አበባ ፒያሳ ከገብረ ትንሳኤ ኬክ ቤት ዝቅ ብሎ ፍሎሪዳ ቡና ቤት መጠጥ ጠግቦ ሲወጣ ሽንት ያዘው። ከዚያም ከፍሎሪዳ እንደወጣ ያለው አደባባይ ላይ ለመሽናት አብሮት ከነበረው ባልደረባው ጋር በመሆን በሞቅታ እያወጋ ተጠጋ። አደባባዩ ላይ ሲሸና እየገለፈጠ “አማራ ላይ እንሽና” ማለቱን በወቅቱ አብሮት ከነበረው ሰው በጀብድ ሲወራ መስማቱን የመረጃ ምንጫችን ይናገራል። ራሱን የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ብሎ በመሰየም አገር ሲያተራምስና ሲዘርፍ ኖሮ መንግሥት እንዲሆን ባዕዳን ኢትዮጵያ አናት ላይ አስቀምጠውት የነበረው የጥቂት ወንበዴዎች ጥርቅም ከጅምሩ የአማራን ሕዝብ በጠላትነት ፈርጆ ለማጥፋት … [Read more...] about የትህነግ አዲሱ ሤራ – አማራን በውክልና እልህ ውስጥ መክተት
ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው
ኃይሌ ሆቴሎች በጣና ዳርቻ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ግዙፍና ዘመናዊ ሪዞርት ለማልማት እንዳቀደ ታወቀ። ጎርጎራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቀጣይ ለማልማት ካሰቧቸው ሦስት የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። ኃይሌ ኩባንያው በጎርጎራ በዓይነቱ ከዚህ በፊት ከተገነቡ ሪዞርቶች ለየት ያለ ሪዞርትና የመዝናኛ ማዕከል ለመገንባት እንዳቀደ ለሪፖርተር ተናግሯል። ሪዞርቱ የሚገነባው ቀድሞ ጎርጎራ ሆቴል ተብሎ በሚታወቀው በአሥር ሔክታር ቦታ ላይ ነው። ይህ ቦታ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ማሠልጠኛና የቀድሞ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ያርፉበት የነበረ ሥፍራ ነው። ፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል፣ ሰው ሠራሽ ባህር ዳርቻና ቪላ ቤቶች ግንባታ ያጠቃልላል። “ጎርጎራ ድብቅ ገነት ነው። ውኃው ንፁህና ጥልቀት ያለው በመሆኑ ለዋናና … [Read more...] about ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው