• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው

August 23, 2020 03:18 am by Editor Leave a Comment

ኃይሌ ሆቴሎች በጣና ዳርቻ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ግዙፍና ዘመናዊ ሪዞርት ለማልማት እንዳቀደ ታወቀ።

ጎርጎራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቀጣይ ለማልማት ካሰቧቸው ሦስት የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። ኃይሌ ኩባንያው በጎርጎራ በዓይነቱ ከዚህ በፊት ከተገነቡ ሪዞርቶች ለየት ያለ ሪዞርትና የመዝናኛ ማዕከል ለመገንባት እንዳቀደ ለሪፖርተር ተናግሯል። ሪዞርቱ የሚገነባው ቀድሞ ጎርጎራ ሆቴል ተብሎ በሚታወቀው በአሥር ሔክታር ቦታ ላይ ነው። ይህ ቦታ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ማሠልጠኛና የቀድሞ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ያርፉበት የነበረ ሥፍራ ነው።

ፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል፣ ሰው ሠራሽ ባህር ዳርቻና ቪላ ቤቶች ግንባታ ያጠቃልላል። “ጎርጎራ ድብቅ ገነት ነው። ውኃው ንፁህና ጥልቀት ያለው በመሆኑ ለዋናና ለጀልባ ሽርሽርና ሌሎች የውኃ ላይ ጨዋታዎች ምቹ ነው፤” ያለው ኃይሌ፣ ኩባንያው የውጭ ባለሀብቶች በሽርክና ለማስገባት እያሰበ እንደሆነ ተናግሯል። “ብቻችንን የታለመውን ውጤት ላናመጣ እንችላለን፤” ብሏል።

ኃይሌ ሪዞርት በሕግ ጉዳዮች ላይ እየሠራ ሲሆን፣ የፕሮጀክቱ የመጀመርያ ዙር ንድፍ ሥራ እንደተጀመረ ታውቋል።

በተያያዘ ዜና ኃይሌ ሪዞርት በአዳማ ከተማ በ400 ሚሊዮን ብር የገነባው ባለ አራት ፎቅ ዘመናዊ ሆቴል ባለፈው ሳምንት ሥራ ጀምሯል።

በ12,000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው አዳማ ኃይሌ ሪዞርት 110 መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የልጆች መጫወቻ ሥፍራ፣ ጂምናዚየም፣ ስፓ፣ ምግብ ቤቶችና የተለያዩ መጠን ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች አሟልቶ የያዘ ነው።

የሆቴሉ ግንባታ ሦስት ዓመት እንደፈጀ የገለጸው ኃይሌ፣ ሆቴሉ አንድ ዘመናዊ ሆቴል ሊኖረው የሚገባው አገልግሎቶች ሁሉ እንዲማሉ መደረጉን ገልጿል። ፕሮጀክቱ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ተናግሯል። ኃይሌ ሪዞርት የማስፋፊያ ሥራ ለማከናወን ከአጠገቡ የሚገኘውን ባዶ ቦታ እንዲሰጠው ለአዳማ ከተማ አስተዳደር አመልክቷል።

“ምክር ቤቱ የሠራነውን ሥራ ተመልክቶ ከሆቴሉ አጠገብ ያለውን ባዶ ቦታ ቢፈቅዱልን ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች እንገነባበታለን፤” ብሏል። የአዳማው ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ለ300 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።

ኃይሌ ሪዞርት ሰባት ሆቴሎች ያሉት ሲሆን፣ 1,400 ሠራተኞች ያስተዳድራል። በቅርቡ የሐዋሳና አርባ ምንጭ ሆቴሎቹ የትሪፕ አድቫይዘር 2020 ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።

ኃይሌ ሪዞርት ሦስት ሆቴሎችን በአዲስ አበባ፣ ሶዶና ኮንሶ በመገንባት ላይ ሲሆን፣ በጎርጎራና ደብረ ብርሃን ዘመናዊ ሆቴሎች ግንባታ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል። “የመንግሥት ቢሮዎች ቢሮክራሲን በመቀነስ የተቀላጠፈ አገልግሎት ቢሰጡን ተጨማሪ የኢንቨስትንመንት ፕሮጀክቶች ቀርፀን ተግባራዊ ማድረግ እንችላለን። የአርባ ምንጭ ሪዞርት ግንባታ አንድ ዓመት ከአምስት ወራት ብቻ ነው የፈጀብን። አገራችን ትልቅ የቱሪዝም ዕምቅ ሀብት አላት። ከእኛ የሚጠበቀው ጠንክሮ መሥራት ነው፤” ብሏል። ቀጣዩ የኢንቨስትመንት መዳረሻው ደብረ ብርሃን እንደሆነች ኃይሌ አረጋግጧል። (ቃለየሱስ በቀለ፤ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: amhara region, gorgorra, haile resort

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule