• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው

August 23, 2020 03:18 am by Editor Leave a Comment

ኃይሌ ሆቴሎች በጣና ዳርቻ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ግዙፍና ዘመናዊ ሪዞርት ለማልማት እንዳቀደ ታወቀ።

ጎርጎራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቀጣይ ለማልማት ካሰቧቸው ሦስት የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። ኃይሌ ኩባንያው በጎርጎራ በዓይነቱ ከዚህ በፊት ከተገነቡ ሪዞርቶች ለየት ያለ ሪዞርትና የመዝናኛ ማዕከል ለመገንባት እንዳቀደ ለሪፖርተር ተናግሯል። ሪዞርቱ የሚገነባው ቀድሞ ጎርጎራ ሆቴል ተብሎ በሚታወቀው በአሥር ሔክታር ቦታ ላይ ነው። ይህ ቦታ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ማሠልጠኛና የቀድሞ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ያርፉበት የነበረ ሥፍራ ነው።

ፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል፣ ሰው ሠራሽ ባህር ዳርቻና ቪላ ቤቶች ግንባታ ያጠቃልላል። “ጎርጎራ ድብቅ ገነት ነው። ውኃው ንፁህና ጥልቀት ያለው በመሆኑ ለዋናና ለጀልባ ሽርሽርና ሌሎች የውኃ ላይ ጨዋታዎች ምቹ ነው፤” ያለው ኃይሌ፣ ኩባንያው የውጭ ባለሀብቶች በሽርክና ለማስገባት እያሰበ እንደሆነ ተናግሯል። “ብቻችንን የታለመውን ውጤት ላናመጣ እንችላለን፤” ብሏል።

ኃይሌ ሪዞርት በሕግ ጉዳዮች ላይ እየሠራ ሲሆን፣ የፕሮጀክቱ የመጀመርያ ዙር ንድፍ ሥራ እንደተጀመረ ታውቋል።

በተያያዘ ዜና ኃይሌ ሪዞርት በአዳማ ከተማ በ400 ሚሊዮን ብር የገነባው ባለ አራት ፎቅ ዘመናዊ ሆቴል ባለፈው ሳምንት ሥራ ጀምሯል።

በ12,000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው አዳማ ኃይሌ ሪዞርት 110 መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የልጆች መጫወቻ ሥፍራ፣ ጂምናዚየም፣ ስፓ፣ ምግብ ቤቶችና የተለያዩ መጠን ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች አሟልቶ የያዘ ነው።

የሆቴሉ ግንባታ ሦስት ዓመት እንደፈጀ የገለጸው ኃይሌ፣ ሆቴሉ አንድ ዘመናዊ ሆቴል ሊኖረው የሚገባው አገልግሎቶች ሁሉ እንዲማሉ መደረጉን ገልጿል። ፕሮጀክቱ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ተናግሯል። ኃይሌ ሪዞርት የማስፋፊያ ሥራ ለማከናወን ከአጠገቡ የሚገኘውን ባዶ ቦታ እንዲሰጠው ለአዳማ ከተማ አስተዳደር አመልክቷል።

“ምክር ቤቱ የሠራነውን ሥራ ተመልክቶ ከሆቴሉ አጠገብ ያለውን ባዶ ቦታ ቢፈቅዱልን ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች እንገነባበታለን፤” ብሏል። የአዳማው ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ለ300 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።

ኃይሌ ሪዞርት ሰባት ሆቴሎች ያሉት ሲሆን፣ 1,400 ሠራተኞች ያስተዳድራል። በቅርቡ የሐዋሳና አርባ ምንጭ ሆቴሎቹ የትሪፕ አድቫይዘር 2020 ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።

ኃይሌ ሪዞርት ሦስት ሆቴሎችን በአዲስ አበባ፣ ሶዶና ኮንሶ በመገንባት ላይ ሲሆን፣ በጎርጎራና ደብረ ብርሃን ዘመናዊ ሆቴሎች ግንባታ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል። “የመንግሥት ቢሮዎች ቢሮክራሲን በመቀነስ የተቀላጠፈ አገልግሎት ቢሰጡን ተጨማሪ የኢንቨስትንመንት ፕሮጀክቶች ቀርፀን ተግባራዊ ማድረግ እንችላለን። የአርባ ምንጭ ሪዞርት ግንባታ አንድ ዓመት ከአምስት ወራት ብቻ ነው የፈጀብን። አገራችን ትልቅ የቱሪዝም ዕምቅ ሀብት አላት። ከእኛ የሚጠበቀው ጠንክሮ መሥራት ነው፤” ብሏል። ቀጣዩ የኢንቨስትመንት መዳረሻው ደብረ ብርሃን እንደሆነች ኃይሌ አረጋግጧል። (ቃለየሱስ በቀለ፤ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: amhara region, gorgorra, haile resort

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule