• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኃይሌ ጎርጎራ ላይ በአንድ ቢሊዮን ብር ሪዞርት ሊገነባ ነው

August 23, 2020 03:18 am by Editor Leave a Comment

ኃይሌ ሆቴሎች በጣና ዳርቻ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ግዙፍና ዘመናዊ ሪዞርት ለማልማት እንዳቀደ ታወቀ።

ጎርጎራ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቀጣይ ለማልማት ካሰቧቸው ሦስት የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። ኃይሌ ኩባንያው በጎርጎራ በዓይነቱ ከዚህ በፊት ከተገነቡ ሪዞርቶች ለየት ያለ ሪዞርትና የመዝናኛ ማዕከል ለመገንባት እንዳቀደ ለሪፖርተር ተናግሯል። ሪዞርቱ የሚገነባው ቀድሞ ጎርጎራ ሆቴል ተብሎ በሚታወቀው በአሥር ሔክታር ቦታ ላይ ነው። ይህ ቦታ የቀድሞ የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ማሠልጠኛና የቀድሞ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ያርፉበት የነበረ ሥፍራ ነው።

ፕሮጀክቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሪዞርትና መዝናኛ ማዕከል፣ ሰው ሠራሽ ባህር ዳርቻና ቪላ ቤቶች ግንባታ ያጠቃልላል። “ጎርጎራ ድብቅ ገነት ነው። ውኃው ንፁህና ጥልቀት ያለው በመሆኑ ለዋናና ለጀልባ ሽርሽርና ሌሎች የውኃ ላይ ጨዋታዎች ምቹ ነው፤” ያለው ኃይሌ፣ ኩባንያው የውጭ ባለሀብቶች በሽርክና ለማስገባት እያሰበ እንደሆነ ተናግሯል። “ብቻችንን የታለመውን ውጤት ላናመጣ እንችላለን፤” ብሏል።

ኃይሌ ሪዞርት በሕግ ጉዳዮች ላይ እየሠራ ሲሆን፣ የፕሮጀክቱ የመጀመርያ ዙር ንድፍ ሥራ እንደተጀመረ ታውቋል።

በተያያዘ ዜና ኃይሌ ሪዞርት በአዳማ ከተማ በ400 ሚሊዮን ብር የገነባው ባለ አራት ፎቅ ዘመናዊ ሆቴል ባለፈው ሳምንት ሥራ ጀምሯል።

በ12,000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው አዳማ ኃይሌ ሪዞርት 110 መኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የልጆች መጫወቻ ሥፍራ፣ ጂምናዚየም፣ ስፓ፣ ምግብ ቤቶችና የተለያዩ መጠን ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች አሟልቶ የያዘ ነው።

የሆቴሉ ግንባታ ሦስት ዓመት እንደፈጀ የገለጸው ኃይሌ፣ ሆቴሉ አንድ ዘመናዊ ሆቴል ሊኖረው የሚገባው አገልግሎቶች ሁሉ እንዲማሉ መደረጉን ገልጿል። ፕሮጀክቱ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ተናግሯል። ኃይሌ ሪዞርት የማስፋፊያ ሥራ ለማከናወን ከአጠገቡ የሚገኘውን ባዶ ቦታ እንዲሰጠው ለአዳማ ከተማ አስተዳደር አመልክቷል።

“ምክር ቤቱ የሠራነውን ሥራ ተመልክቶ ከሆቴሉ አጠገብ ያለውን ባዶ ቦታ ቢፈቅዱልን ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች እንገነባበታለን፤” ብሏል። የአዳማው ሆቴል ሙሉ በሙሉ ሥራ ሲጀምር ለ300 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።

ኃይሌ ሪዞርት ሰባት ሆቴሎች ያሉት ሲሆን፣ 1,400 ሠራተኞች ያስተዳድራል። በቅርቡ የሐዋሳና አርባ ምንጭ ሆቴሎቹ የትሪፕ አድቫይዘር 2020 ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።

ኃይሌ ሪዞርት ሦስት ሆቴሎችን በአዲስ አበባ፣ ሶዶና ኮንሶ በመገንባት ላይ ሲሆን፣ በጎርጎራና ደብረ ብርሃን ዘመናዊ ሆቴሎች ግንባታ ለመጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል። “የመንግሥት ቢሮዎች ቢሮክራሲን በመቀነስ የተቀላጠፈ አገልግሎት ቢሰጡን ተጨማሪ የኢንቨስትንመንት ፕሮጀክቶች ቀርፀን ተግባራዊ ማድረግ እንችላለን። የአርባ ምንጭ ሪዞርት ግንባታ አንድ ዓመት ከአምስት ወራት ብቻ ነው የፈጀብን። አገራችን ትልቅ የቱሪዝም ዕምቅ ሀብት አላት። ከእኛ የሚጠበቀው ጠንክሮ መሥራት ነው፤” ብሏል። ቀጣዩ የኢንቨስትመንት መዳረሻው ደብረ ብርሃን እንደሆነች ኃይሌ አረጋግጧል። (ቃለየሱስ በቀለ፤ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, Social Tagged With: amhara region, gorgorra, haile resort

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule