1 - ተመስገን ደሳለኝ 2- እስክንድር ነጋ 3- ናትናኤል መኮንን 4- አንዳለም አራጌ 5- ውብሽት ታዬ 6- አበበ ቀስቶ 7- ሃብታሙ አያሌው 8- ድልንኤል ሺበሺ 9- አብርሃ ደስታ 10- የሽዋስ አሰፋ 11- ዘላለም ወርቅአገኘሁ 12- አቤል ዋበላ 13- ናትናኤል ፈለቀ 14- በፍቃዱ ሃይሉ 15- አጥናፍ ብርሃኔ 16- ፍቅረማርያም አስማማው 17- እየሩሳሌም ተስፋው 18- ብርሃኑ ተክለያሬድ 19- ኦልባና ለሌሳ 20- ቴድሮስ አስፋው 21- ማትያስ መኩርያ 22- ብሌን መስፍን 23- ተዋቸው ደምሴ 24- ንግስት ወንዳፈራሁ 25- ሜሮን አለማየሁ 26- ደሴ ካህሳይ 27- ናትናኤል ያለምዘውድ 28- ሰንታየሁ ቸኮል 29- ማስተዋል ፈለቀ 30- ንግስት ወንድይፍራው 31- ሂሩት ክፍሌ 32- እማዋይሽ አለሙ 33- ሰለሞን ከበደ 34- የሱፍ … [Read more...] about ያልተፈቱት “አሸባሪዎች”
Politics
“የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ነው!”
ስለ ሳሙኤል ግድያ ብዙ ነገር ተብሏል፡፡ ብዙዎች ቁጭታቸውን ገልፀዋል፡፡ ለእኔ ከሳሙኤል አወቀ ግድያ ምን እንማራለን? የሚለው ነው ትልቁ ቁም ነገር፡፡ ሳሙኤል በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ንግግር ተናግረው የተገደሉ ሰዎች ጋር የሚመደብ ሰው ነው፡፡ የሳሙኤል ትውልድ አካል በመሆኔ ኩራት ይሰማኛል፡፡ እንደገሚገሉት እያወቀ፣ ነገር ግን ያ ሞቱ ከንቱ እንዳይሆን አስፈላጊውን መረጃ አስቀምጦልናል፡፡ አቡነ ጴጥሮስ መንፈሳዊ አባት ማለት ምን ማለት እንደሆነ አስተምረው ህዝቡ ለጣሊያን እንዳይገዛ ሰብከው ተገድለዋል፡፡ ለዚህም ሀውልት ቆሞላቸዋል፡፡ ይህ መታሰቢያ ለኢትዮጵያዊነት የመንፈስ ልዕልና እና የአልበገሬነት ምልክት ሆኖ ለዘላለም ይኖራል፡፡ የአቡነ ጴጥሮስን ታሪክ ተማሪዎችም ይማሩበታል፡፡ የሳሙኤልን ንግግርም ወደፊት እድሜ ከሰጠን እኛ እናየዋለን፡፡ እኛ ባንደርስበት እንኳ መጪው ትውልድ … [Read more...] about “የሳሙኤል ግድያ ለታጋዮችም ለገዳዮችም ትልቅ ትምህርት ነው!”
“የአማራ ክልል ዳኞች አቤቱታ”
ከአዘጋጆቹ፡- ማንነታቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የፌስቡክ ወዳጃችን “የአማራ ክልል ዳኞችን ድምፅ አስተጋቡልን” በማለት በውስጥ መስመራችን የላኩልንን ከዚህ በታች አቅርበነዋል፡፡ ጋዜጠኝነት “ወንጀል” በሆነባት ኢህአዴግ በሚገዛት አገራችን በስም የተጠቀሱትን ሹመኛ ለመጠየቅና ሁኔታውን ለማረጋገጥ አንችልም፡፡ ሆኖም ግን መረጃው ስህተት ነው የሚል የኢህአዴግ አካል ምላሽ ከሰጠን ለሕዝብ እናቀርባለን፡፡ “የአማራ ክልል ዳኞችን ድምፅ አስተጋቡልን”!!!!! ደመወዝና ጥቅማጥቅም ስላነሰን ከእነ ልጆቻችን ተራብን፣ ተጠማን፣ ብለን ሀሳብ እንዳንሰጥ “ችግር አለባቸው” እየተባልን ከነአካቴው ከስራ ልንወገድ ሆነ፡፡ ጎን ለጎን ሌላ ስራ ፈጥረን እንዳንሰራ ዳኛ በንግድ ስራ መሰማራት አይችልም ተባልን፡፡ ኧረ የት እንድረስ!!! ደመወዝና ጥቅማጥቅም ይስተካከልላቸው ተብሎ ከክልሉ ዳኞች አስተዳደር … [Read more...] about “የአማራ ክልል ዳኞች አቤቱታ”
“ደብረማርቆስና ባህርዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ልታደርጉ ነው የምትሄዱት” ፖሊስ
• ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ለሌላ ለቅሶ በመሄድ ላይ የነበሩ ዜጎች ተደብድበው ተመልሰዋል የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ደብረማርቆስ ከተማ የተገደለው የሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በጠዋት ከአዲስ አበባ ተነስተው የሳሙኤል አወቀ ቤተሰቦች ወደሚገኙበት ምስራቅ ጎጃም ዞን ግንደወይን እያቀኑ በነበረበት ወቅት አባይ ድልድይ ላይ በፌደራል ፖሊስ ታፍነው ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ጎሃ ፂዮን ከተማ ውስጥ እስከ ምሽቱ 2 ተኩል ድረስ ታግተው ውለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ወደ ለቅሶ እንዳይሄዱ ያገዱት ከአዲስ አበባ የሄዱና ከቦታው ተዘጋጅተው ሲጠብቁ የነበሩ የፌደራል ፖሊሶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ለፖሊስ ቃል ሲሰጡ ከሳሙኤል አወቀ ጋር የነበራቸውን … [Read more...] about “ደብረማርቆስና ባህርዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ልታደርጉ ነው የምትሄዱት” ፖሊስ
“ከ10 ሌባ መሀል አንተ ንጹህ ሆነህ ሙስናን መታገል አትችልም” የፍትህ መምሪያ ሀላፊ
* “ግድያው ከሟች የፖለቲካ አቋም ጋር የሚገናኝ አይደለም፤ የመንግስትም እጅ የለበትም” ህወሃት/ብአዴን/ኢህአዴግ * “ለሞት ያበቃቸው ክስተት ግን ግለሰባዊ ግጭት” የህወሃት/ብአዴን ሹመኛ * “የሰማያዊ ፓርቲ አባልነትህን የማታቋርጥ ከሆነ አንተን ማስደፋት ቀላል ነው!” የደብር ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ * “የሰማያዊ ፓርቲ አባልነቴን አንተ አታስቆመኝም፡፡ አገሬም ኢትዮጵያ ነው! ከኢህአዴግ ጋር ስታገልም ይህን ሁሉ አውቃለሁ፡፡ የፈለግከውን ማድረግ ትችላለህ!” ሳሙኤል አወቀ እንዲህ ዓይነቱ በማስረጃ የተደገፈ ክስተት እያለ ሠንደቅ ጋዜጣ አነጋግሬ አመጣሁ ባለው ዜና ላይ የሳሙኤል ግድያ "ልማታዊ" ነው ይላል:: ለመሆኑ ራሱ ሳሙኤል አወቀ ምን ይላል? ሳሙኤል ሚያዝያ 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 8 የነገረ ኢትዮጵያ እትም ላይ በምስራቅ ጎጃም ዞን … [Read more...] about “ከ10 ሌባ መሀል አንተ ንጹህ ሆነህ ሙስናን መታገል አትችልም” የፍትህ መምሪያ ሀላፊ
100% ደፋኝ “ጎበዞች”
በ1994ዓም የኢራቁ ፕሬዚዳንት ሳዳም ሁሴን “በምርጫ” 100% ደፍነው ነበር፡፡ ያለፈው ዓመት ደግሞ የሰሜን ኮሪያው ኪም ጆንግ-ኧን ያለአንዳች ተቀናቃኝ ባደረጉት “ከፍተኛ ትንቅንቅ” በነበረበት የምርጫ ውድድር ብቻቸውን ተወዳድረው በመጨረሻው ላይ ትንፋሻቸውን ይዘው 100% ለመድፈን በቅተዋል፡፡ ሳዳም 100 ከደፈኑ በኋላ ብዙም አልቆዩም፡፡ በሌላ በኩል የቀድሞው የሰሜን ኮሪያ ታላቁ ባለራዕይ መሪ ኪም ጆንግ ኢል ከልጃቸው ኪም ጆንግ-ኧን በ0.1% በመበለጥ በ2001ዓም 99.9% ያገኙ “ጎበዝ” ነበሩ፡፡ የኩባው ራዑል ካስትሮ በ2000ዓም 99.4% ሲያገኙ የሶሪያው ባሽር አል አሳድ 97.6% ያስቆጠሩ ሌላው “ደፋኝ” ናቸው፡፡ የቱርክሜኒስታኑ ሳፓርሙራት ኒያዞቭ በ1984 እንዲሁም የቼችኒያው የተባበሩት ሩሲያ ፓርቲ በ2003ዓም 99.5% ያስቆጠሩ ሌሎቹ “ጎበዞች” ናቸው፡፡ በ1996ዓም … [Read more...] about 100% ደፋኝ “ጎበዞች”
የመድረክ ምርጫ አስተባባሪ በደቡብ ኢትዮጵያ ተደብድበው ተገደሉ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ በደቡብ ክልል አንድ የምርጫ አስተባባሪው አርብለት ተገድለው መገኘታቸውን አስታወቀ። የተቃዋሚ ፓርቲም በምርጫ 2007 ዙሪያ የዛሬውን ጨምሮ 4 አባላቱና ደጋፊዎቹ መገደላቸውን አስታውቋል። በዚህ ሳምንት እንደተገደሉ ተቃዋሚዎች ከገለጿቸው ሶስት ሰዎች በተጨማሪ በኦሮሚያና ደቡብ ክልል ህይወታቸው ማለፉ የተገለጸው አጠቃላይ ቁጥር ስድስት ደርሷል። በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን ሶሮ ወረዳ የተገደሉት አቶ ብርሃኑ ኤረቦ ሐሙስለት በሁለት ፖሊስ ባልደረቦች ከመኖሪያ ቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ተደብድበው ህይወታቸው አልፎ ወንዝ ዳር መገኘታቸውን የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ምርጫ 2005 በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ወደ 46ሽህ የሚጠጉ የድምጽ መስጫ ጣቢያዎች ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከናወኑን የኢትዮጵያ መንግስትና ምርጫ ቦርድ … [Read more...] about የመድረክ ምርጫ አስተባባሪ በደቡብ ኢትዮጵያ ተደብድበው ተገደሉ
ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ በድብቅ ጅዳ ገቡ
የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚ/ር አቶ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ በድብቅ ጅዳ ማምሻውን ገብተዋል፡፡ ወደ ሳዑዲ አረቢያ የመጡበት ምክንያት ባይታወቅም በዚያው የሚገኙ የኢህአዴግ ሹሞችና ልማታዊ ዲፕሎማቶች ድንገተኛውን ጉብኝት ተከትሎ ከብርሃነ ጋር ለመወያየት ሽርጉድ ይሉ ለነበሩ የጅዳና አካባቢው ካድሬዎች፣ ለልማት ማህበራት ተወካዮችና ለደጋፊዎቻቸው በሚስጥር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ ምስጢራዊውን ጥሪ የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን አንድ ባለስልጣን በዚህ መልክ ወደ ጃዳ መግባታቸው ዲፕሎማት ብለው ለሾሟቸው አገልጋዮቻቸው ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን በዲፕሎማቱ ላይ እምነት እንደሌላቸው አመላካች መሆኑን ይናገራሉ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ለስራ ጉብኝትም ይሁን ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲገቡ የኤምባሲው ዲፕሎማቶች መረጃ የሚያገኙት ከተለያዩ ድህረ ገጾች መሆኑን … [Read more...] about ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ በድብቅ ጅዳ ገቡ
የዛሬ 24 ዓመት ኢህአዴግ አዲስ አበባን ባይቆጣጠር
ደርግ 17 ዓመታት ሙሉ በህወሓት እና ሻብያ የተከፈተውን ጦርነት ሲዋጋ እንደነበር እና ጦርነቱ በቀን ብቻ በሚልዮን የሚቆጠር ብር ያስወጣ ነበር። በመቶሺዎች የሚቆጠር ሰራዊት መግቦ፣ ታንክ እና ብረት ለበስ ተሽከርካሪ ነዳጅ እና ግዥ ፈፅሞ ማደር በራሱ ከፍተኛ ወጪ ነበር። ይህ ገንዘብ እንዳሁኑ የእርዳታ እና የብድር ገንዘብ ሳይሆን ህዝቡ ለእናት ሀገር እያለ ከሚያዋጣው እንደነበር ይታወቃል። በእርግጥ የሩስያ እርዳታ እና ብድር እንዳለ ሆኖ። በአንድ ወቅት ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርይም የሰሜኑ ጦርነት ባይኖር በጥቂት አመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ከሰሜን እስከ ደቡብ ከምዕራብ እስከ ምስራቅ በባቡር ማገናኘት በተቻለ ነበር። ሲሉ መደመጣቸው ይታወሳል። በተለይ ህወሓት በዋነኛነት ድልድዮች እና መንገዶችን ማፍረስ ስራዬ ብሎ ይዞ ስለነበር እነርሱን ተከታትሎ መጠገን ሌላው ሥራ ነበር። የመከላከያ … [Read more...] about የዛሬ 24 ዓመት ኢህአዴግ አዲስ አበባን ባይቆጣጠር
የምርጫና ነጻነት ቁልቁለት
* ከ45 ዓመት በፊት የፓርላማ ምርጫን ያሸነፉት አራት ሴቶች ሰማንያ አራት ዓመት ባስቆጠረው የኢትዮጵያ ፓርላማ የመጀመርያው ሕዝብ በቀጥታ የተሳተፈበትና እንደራሴዎቹን የመረጠበት ምርጫ የተካሄደው በ1948 ዓ.ም. ነበር፡፡ በቀዳሚው ምርጫ ካሸነፉት ተወዳዳሪዎች መካከል አንዷ ወ/ሮ ስንዱ ገብሩ ናቸው፡፡ በታሪክ እንደተመዘገበው ወ/ሮ ስንዱ የመጀመሪያዋ የሴት የሕግ መምሪያ ምክር ቤት አባልና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ለአራት ዓመት አገልግለዋል፡፡ ከወ/ሮ ስንዱ በኋላ ጥቂት የማይባሉ ሴቶች እስከ 1965 ዓ.ም. ድረስ በተካሄዱት አምስት ምርጫዎች ተፎካክረዋል፡፡ በ1961 ዓ.ም. በተካሄደው አራተኛው የሕዝበ እንደራሴዎች ጠቅላላ ምርጫ ከመላው ኢትዮጵያ ከተመረጡት 250 እንደራሴዎች መካከል አሸናፊ የነበሩት አራት ሴቶች ሲሆኑ፣ ከተወዳደሩት መካከል 24ቱ ሴቶች … [Read more...] about የምርጫና ነጻነት ቁልቁለት