• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲስ አበባ ተቆላልፋለች

October 6, 2016 08:23 am by Editor 3 Comments

ወቅታዊ ሪፖርታዥ

በሳምንቱ መግቢያ የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ እና ድርድር እንዲደረግ ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል። አምስቱ የሕወሃት ቁንጮዎች ትእቢት የተሞላበት ምላሽ ነው የሰጡት። ከድርድር ይልቅ ከሕዝብ ጋር ጦርነት መግጠምን መርጠዋል።

አብዛኛው የፖሊስ እና የሃገር መከላከያ ሰራዊቱ “ሕዝብ ላይ አልተኩስም” ማለታቸው የህወሃት አመራርን ጭንቅ ውስጥ አስገብተውታል።

አዲስ አበባ ተቆላልፋለች። በአራቱም አቅጣጫ በኩል የሚገባም የሚወጣም የለም። መንገዶች በሙሉ ተዘጋግተዋል። ስልክ እና ኢንተርኔት ጠፍቷል።enat-bank

በአዲስ አበባ ዙርያ ባሉ ከተሞች ሰኞ መስከረም 23 ቀን የተጀመረውን ሕዝባዊ አመጽ ለማዳፈን በህወሃት የተወሰደው የአፈሳ እርምጃ አመጹን አላቆመውም። ሰኞ ማምሻውን በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ታፍሰው ወዳልታወቀ ስፍራ በመወሰዳቸው ሳብያ አመጹ በዛሬው እለት ተባብሶ ቀጥሏል። የአካባቢ ፖሊሶችም ከሕዝብ ጋር በመሆን በአመጹ እየተሳተፉ በመሆኑ የስራአቱን ቁንጮዎች ጭንቀት ውስጥ ከቷቸዋል።

ሰበታ ላይ የነበረው የቱርክ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ እና የሃይል ማመንጫ ኩባንያ በትናንትናው እለት መውደሙን ሮይተርስ ከስፍራው ዘግቧል። በሆለታ በነበረው አመጽ ሚስ ሻሮን ሬይ የተባለች አሜሪካው የግብርና ኤክፐርት መገደልዋንም ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቦ ነበር። ይህ ዜና በአለም የመገናኛ ብዙሃን ከተሰማ በኋላ ህወሃት የስልክ እና የኢንተርነት አገልሎት እንዲቋረጥ አድርጓል። የአመጹ ዜና ወደ ሌሎች እንዳይሰራጭ ታቅዶ የተደረገው  ይህ ድርጊታቸው የህዝብን ቁጣ እያበረታው መጥቶ ካድሬዎችን እየለቀሙ መምታት እንዲጀመር አስተዋጽኦ አድርጓል።

ሕዝብ በጋራ ተነስቶ የህወሃት ተላላኪዎችን እያስጠነቀቀ ሲሆን እንቢ ያሉት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ይገናል። የወንጂ ስኳር ፍብሪካ ከፉተኛ ቃጠሎ የደረሰበት ሲሆን፣ ኩሪፉቱ የሼክ አላዓሙዲን የከብት ማድለቢያ ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሟል። በቀርሳ ወረዳ አንድ የህወሃት ተላላኪ alem-genaበህዝብ ተገድሏል፣ በሆሮ ጉድሩ እና በጉጂም የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ላይ ሕዝብ እርምጃ ወስዶባቸዋል። በድሬ ዳዋ ዲፖ ጋዝ ስቴሽን በእሳት ጋይቷል።

የናይጄሪያዊው ኪሎ ዲንጎቴ ንብረት የነበረው ዲንጎቴ ሲሚንቶ ፋብሪካ  ሙሉ በሙሉ በህዝባዊ አመጽ መውደሙን የአፍሪካ ሜድያ ኔትወርክ ዘግቧል። ጉጂ ዞን ያለው የሼክ አላሙዲን የወርቅ ማእድን በትላንትናው እለት መውደሙን ማህበራዊ ድረ-ገጾች ዘግበዋል።

ባዶ እጁን እየወጣ ሲገደል የነበረው የኦሮሞ ሕዝብ አሁን ራሱን ራሱን የሚከላከልበት መሳርያ እየያዘ  መውጣቱን የሚደርሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ። በአለም ገና ዳሽን ባንክ እና ከገዥው ፓርቲ ጋር ንክኪ ያላቸው መኪናዎች ተቃጥለዋል።

በአርሲ፣ በመቱ እና በጂማ በተማሪዎች የተቀሰቀሰው አመጽ እንደቀጠለ ነው። የጅማ ወህኒ ቤት ተቃጥሎ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ እንዲፈቱ የተደረገው ትላንት ምሽት ላይ ነበር።

አዲስ አበባ ከእሬቻው እልቂት በኋላ የሙት ከተማ መስላለች። የንግድ እንቀስቃሴ በሙሉ ቆሟል። ሱቆች ዝግ ናቸው፣ የህዝብ ትራንስፖርትም የለም። መርካቶም ጸጥ-ረጭ እንዳለች ነው። በዛሬው እለት ታክሲ በከተማዋ ባለመኖሩ አብዛኛው ሰው ስራdangote-cement አልገባም። ከተወሰኑ የግል ትምህርት ቤቶች  በስተቀር የመንግስት ትምህርት ቤቶች አሁንም ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ተወስኗል። አንዳንድ የግል ት/ቤቶች ወላጆችንን  ልጆቻቸውን ወደ ት/ቤት  እንዳይልኩ እየመከሩ ይገኛሉ።

ለአዲስ ተማሪዎች ጥሪ ያደረገው የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ብቻ ነው። ሌላዎቹ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ተማሪ ገብቶ የመማሩ ጉዳይ የሚታሰብ አይደለም።

በደቡብ ወደ ሻሸመኔ እና ወደ አዋሳ የሚወስደው መንገድ እሁድ ጀምሮ ዝግ ነው። በሰሜን ሱልልታ፣ ለገዳዲ፣ ቦሌ ቡልቡላ፤ በም እራብ በአስኮ፣  በቡራዩ፣  ሰበታ፣ አለምገና፣ ብስራተ-ገብሬል፣ አየር ጤና፣ ወሊሶ፣ ወደ ሆሳዕና እና ጅማ የሚወስዱ መንገዶች በሙሉ ተዘግተዋል። በዚያ የሚተላለፍ ተሽከርካሪ ቢገኝ የድንጋይ ናዳ ይወርድበታል።

አጋዚ ይህ ሕዝባዊ አመጽ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆነበት አዲስ አበባን ብቻ ከብቦ እየጠበቀ፣ ንጹሃን ዜጋን በማፈስ ስራ ላይ ተጠምዷል።

agaziህወሃት በአማራው ሕዝብ ላይ በይፋ ያወጀው ጦርነት አልተሳካም። ራሱን ከመከላከል አልፎ አካባቢውን ከአጋዚ ነጻ እይደረገ ይገኛል። በርካታ የፖለቲካ እስረኞች ከእስር ነጻ ወጥተዋል። የባህርዳር ዩንቨርስቲ እስካሁን እንደተከበበ ነው። የኮሶበር ህዝብ የዳሽን ቢራን ጭኖ የነበረ ከባድ መኪና ከአገልግሎት ውጪ ሆኗል።

በባህር ዳር ወጣቶችን ሲያሰቃይ የነበረ የማንኩሳ ተወላጅ ማንነቱ ባልታወቀ አካል ተገድሎ መገኘቱ በማህበራዊ ድረ-ገጽ ተዘግቧል።

የህወሃት ባለስልጣናት አሸንዳን በርችት፣ እሬቻን በጥይት ካስተናገዱ በኋላ በወገን ላይ በደረሰው አሰቃቂ እልቂት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ብሄራዊ ሃዘን ላይ ነበር።

ብሄራው ሃዘን ላይ የነበረው ህዝብ ወደ ብሄራዊ አመጽ የገባ ይመስላል። ሰላማዊ ሕዝብን እንደ ግራዚያኒ፣ እንደ ሞሶሎኒ በጥይት እና በመርዝ ጭስ ከጨረሱ በኋላ በቴሌቭዥን ወጥተው አዝነናል እያሉ፣ ቁስልን የባሰ ሲነካኩበት ከዚህ ውጭ አማራጭ የለም። ሕወሃቶች ይልቁንም ለራሳቸው ይዘኑ። ሰላማዊውን ህዝብ እየጨረሱ ያሉት ሁሉ በተራቸው የሚያለቅሱበት ግዜ ሩቅ አይደለም። በደም የታጠበ እጃቸው ገና ሳታደርቅ በቴሌቭዥን ወጥተው በሟች አጽም ላይ መቀለዳቸው ሳያንስ በተለመደ የሽብርተኞች ዲስኩር ህዝብ ላይ እጅ መቀሰር ድፍረት ነው።hawassa

ግዜ ሊወስድ ይችል ይሆናል እንጂ  እነዚህ ነብሰ-ገዳዮች የእያንዳንዱ ነብስ ዋጋ መክፈላቸው አይቀሬ ነው።

የቢሾፍቱው ግድያ የህወሃት “ጥልቅ ተሃድሶ” ጅማሬ መሆኑ ነው። ግን ህዝብን እየረገጡ ብዙ ሊዘልቁ አይችሉም። ፍም እሳት የሆነ የአመጽ ትውልድ ተፈጥሯል። እነሱ ባሰሩ እና በገደሉ ቁጥር ሚሊዮን ሆኖ የሚነሳ ትውልድ። ምንም ነገር ሳይዝ በድምጹ ብቻ የሚያስፈራ ትውልድ። ህዝብን ጠላት አድርጎ ለመግዛት የሚሞክር ስርዓት ይህንን ሁሉ ህዝብ ከቶውንም ገድሎ ሊጨርስ አይችልም።

ክንፉ አሰፋ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Lemma says

    October 6, 2016 06:06 pm at 6:06 pm

    ፍም እሳት የሆነ የአመጽ ትውልድ ተፈጥሯል። እነዚህ ነብሰ-ገዳዮች የእያንዳንዱn ነብስ ዋጋ መክፈላቸው አይቀሬ ነው!!!!

    Reply
  2. Admasu Dua says

    October 6, 2016 10:33 pm at 10:33 pm

    Nice!

    Reply
  3. Tesfa says

    October 7, 2016 03:26 pm at 3:26 pm

    ብየ ነበር…
    አይመችም ሰውን በዘር ማሰለፍ
    አሸንዳን በርችት
    እሬቻን በጥይት መቀበል
    በጎሳና በዘር እየለዩ እሳትን መለኮስ
    ብየ ነበር
    ሃገር ሃገር አትሆንም ተሰምራ በክልል
    መስሎን እንጂ የመጠቅን የሰለጠን
    የክልላችን አለቆች፤ እኛው በእኛው ተዳዳሪዎች
    የራሳችን እድል በራሳችን ወሳኞች
    ያፈራነውን ፍሬ ቀማሾች
    በቋንቋችን የኮራን
    የክልል ሰንደቃችን ከፍ ያረግን
    በልተን ለበላተኛ የምናካፍል
    በእጃችን የቀረውን ስናይ
    የተቸረን ፍርፋሪ እንጂ
    ያመረትነው ምርት አይደለም።
    እፎይ ብለን በዘራችን በቋንቋንች ስንኩራራ
    ቀኑ መሽቶ ነግቶልን ብንነቃ
    አገኘነው የዘር አሰላለፋችንን
    ሆኖ የልጆች ጫዋታ
    ያደረ እንጀራ ቁርስርስ
    የቆመ ነገር ፍርስርስ።
    እኔስ ብየ ነበር አይጠቅመንም
    ብሄራዊነት የለሌው ሰልፋችን
    ካለፈ ታሪክ ለማይማር
    እንደ ወያኔ ላለ ግራዚያኒ
    መጠቀሚያ መገልገያ
    የግዛት ዘመናቸው ማራዘሚያ
    ብልሃታቸው እኛኑ መከፋፈል በዘር በጎሳ ማሰለፍ
    ማተራመስ፤ የዘር ቁማር መጫወት።
    ሲጨንቃቸው ጊዜ ሲጨልምባቸው
    አሁን ደግሞ ይሉናል
    ጥልቅ ተሃድሶ ያሻናል
    የህዝብ ድምጽ ሰምተናል
    እስራቱ፤ ግድያው፤ አፈናና ዘርፊያው ይቀጥላል
    በማለት ቁማር ይጫወቱብናል።
    ግን በየ ነበር…. ሲፈራርሱ
    ሃገሪቱን ከላይ እስከ ታች በእሳት ሲለኩሱ
    ያለ የሌለውን ይዘው ሲኮበልሉ
    እኛም እንደ እነርሱ ያዘው ጥለፈው
    ከማለት እንድንቆጠብ፤
    የርስ በርስ ደም ማፋሰስ እንዲቆም
    አሁን ነው ጊዜው ህዝባችን የምንመክረው
    ራሱን እንዲከላከል፤ ወዳጅ ጠላቱን ለይቶ
    እሳትን በእሳት ፈትኖ
    ደም አፍሳሽን ተጋፍጦ
    የዛሬውን ገራፊ
    ህዝባችንን አስለቃሽ
    በተራው እንዲያለቅስ
    የቢሾፍቱው ብሄራዊ ሃዘናችን
    ህቡእና ግልጽ የሆነ አመጻችን
    አመድ እንዲያደርግ የዘርና የጎሳ አሰላለፋችን
    ብየ ነበር አይጠቅመንም የተናጠል ሩጫ
    ህብር ያልሆነ ፍርጥጫ፤
    ያደርገናል መሳቂያ
    ለጠላቶቻችን ማላገጫ
    ለስልጣን ጥመኞች መሰንበቻ።
    ተስፋ በወቅቱ
    መስከረም 26 2009
    አሜሪካ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule