“የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል ሲለኝ - ደነገጥኩ” የሚል አስተያየት የሰጠው ኳስ አፍቃሪ ከጎልጉል የአዲስ አበባ ወኪል ጋር የተገናኘው አዲስ አበባ ስታዲየም ነበር። ጉዳዩ ለሚዲያ ግብዓት እንደሚውል ባይረዳም ገጠመኙን ለመናገር የተገደደው ስለ ምርጫ አንስተው ሲወያዩ ነው። ድንገት ተገናኝተው ቆሎ በመገባበዝ የጀመሩት ጨዋታ ዘጋቢውን ወደ 1997 ምርጫ ትዝታ ወረወረው። ተግባብተው አወጉና ተለያዩ። የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል!! ለምን? መርዝ ዘርቶ በጥይት ለማጨድ? የስታዲየሙ ሰው የመኪና ማስጌጫ ለመግዛትና ለማስገጠም ሰባራ ባቡር እንደሄደ ይናገራል። እዛም እንደ ደረሰ የሚፈልገውን ገዝቶ እያስገጠመ ሳለ አንድ ጎረምሳ ቢጤ ይጠጋቸውና ወሬ ይጀምራል። ጎረምሳው የትግራይ ተወላጅ ነው። አንዳንድ ማስጌጫዎች የሚፈልግ ከሆነ እሱ ዘንድ በርካሽ እንደሚያገኝ እየነገረው ቃላት መለዋወጥ ጀመሩ። … [Read more...] about “የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል” ሲለኝ – ደነገጥኩ
Politics
መለሰ ዜናዊ ናፈቁኝ – የለቅሶ አየር ሰዓት አማረኝ
ሰላም ወገኖቼ!! ተጠፋፋን። ግን አንለያይም። ድሮ የዘፈን ምርጫ ክፍለ ጊዜ ነበር። እሁድ እሁድ ወታደሮች ከደጀን፣ እናትና አባት፣ ቤተሰብ ከቤት ሆነው ይኮሞክሙት ነበር። አሁን ግን ለምን ተከለከለ? ባድመ፣ ሽራሮ፣ ዛላምበሳ፣ ገመሃሎ፣ ላከ ኤርትራም አሉ፤ ዘላበድኩ መሰለኝ … ብቻ የዘፈን ምርጫ ክፍለ ጊዜው ትዝ ብሎኝ ነው። ቀጭኑ ዘ-ቄራ ነኝ!! “የለቅሶ ማስተላለፊያ የአየር ሰዓት/ክፍለ ጊዜ ቢጀመር ጥሩ ነው። ምርጫውን ያደምቀዋል” የሚል አስተያየት ሟርተኞች ያቀርባሉ። ግን ምን አለበት የከፋቸው ቢያለቅሱ። በየጓዳው እያለቀሱ ነው። አደባባይ ወጥተው ቢያለቅሱ ምን ነውር አለው? ለመለስ ደረት እየተመታ ሲለቀስ የአየር ሰዓት ተፈቅዶ የለ? ለሞተ ሰው ከተፈቀደ በህይወት ላለው፣ ግብር ለማያጓድለው ለምን ይከለካል? ወይስ ነዋሪው በሟች ተበልጧል? ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲባል … [Read more...] about መለሰ ዜናዊ ናፈቁኝ – የለቅሶ አየር ሰዓት አማረኝ
ምርጫ በኢትዮጵያ ምን ይመስላል?
በሃገራችን ታሪክ ውስጥ ብሄራዊ ምርጫ የተጀመረው እንደ ኣውሮፓውያን ኣቆጣጠር በ1957 በዓጼ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ሲሆን በ1955 የወጣውን ህገ -መንግስት መሰረት ያደረገ ንጉሱንና የላይኛውን ቤት ወይም ሴነቱን የማይመለከት ነገር ግን የተወካዮች ምክር ቤት ኣባላትን መምረጥ ተጀምሮ ነበር። እማኞች ሲነግሩን ምርጫውና ቆጠራው ግን ሃቀኛ ነበር ኣሉ። ታዲያ ንጉሱ በነበሩበት ዘመን የነበሩት ምርጫዎች ጅማሪያቸው መልካም ቢሆንም ዓለም በማህበራዊ ለውጥ ላይ በነበረችበት በመጨረሻው ሰዓት የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ ህገ-መንግስታዊ ሞናርኪ ቀይሮ የፖለቲካውን ስልጣንና የህዝቡን ተሳትፎ ማስፋት ስላልተቻለ ወታደራዊ ደርግ ኣብዮቱን ኣንግቦ ብቅ ኣለ። ደርግ ወታደራዊ መንግስት ስልጣን ከያዘ በኋላ የሶሻሊዝም ርእዮት ተከታይ ነኝ በማለቱ በየማህበራቱ የሚደረጉት ምርጫዎች ሁሉ ከዚያው ከኣንድ ምንጭ … [Read more...] about ምርጫ በኢትዮጵያ ምን ይመስላል?
“ስኳር ለባለካርድ ብቻ” – ምርጫ ቦርድ
የሥልጣን ተቀናቃኞቻቸውን ይሁን ባላንጣዎቻቸውን ወይም ከእርሳቸው የተለየ ሃሳብ የሚያመነጩትን “ስኳር ወዳድ”፣ “በስኳር የተታለለ”፣ … እያሉ ለእስር ሲዳርጉ የነበሩት አቶ መለስ፤ ሞት ሳይቀድማቸው በፊት ራሳቸው ያቋቋሙትና እርሳቸውን ደግሞ ደጋግሞ እያገላበጠ አንዴ ፕሬዚዳንት ሌላ ጊዜም ጠቅላይ እያደረገ ሲሾማቸው የኖረው “የምርጫ ቦርድ” ሕዝቡን በስኳር እየፈተነ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ “ስኳር” ቀምሰው ሳያውቁ ስለ ስኳር “አስከፊነት” ዘለግ ያለ መግለጫ በመስጠት ይታወቁ የነበሩት መለስ ለፓርቲያቸው መለያ “ንብ” መምረጣቸው በስኳር ላይ ያላቸውን ጥላቻ በትጋት ያሳየ እንደሆነ ታሪካቸው አሁንም ይመሰክራል፡፡ የሆነው ሆኖ ጓዶቻቸውን “በስኳር ወዳጅነት” ለእስር የዳረጉት መለስ እርሳቸው እየመላለሰ እንዲያነግሥ የመሠረቱት “የምርጫ ቦርድ” ሰሞኑን በ“አፍቅሮተ ስኳር” መጠመዱን ቢሰሙ ኖሮ ምን … [Read more...] about “ስኳር ለባለካርድ ብቻ” – ምርጫ ቦርድ
የኢህአዴግ የኢኮኖሚ ስሌት
ኢኮኖሚያችን በድርብ አኻዝ እያደገ ነው! በአፍሪካ ፈጣን ኢኮኖሚ በማስመዝገብ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለመሰለፍ እያደረግን ያለው ጥረት ተስፋ ሰጪ መሆኑ …፤ ህዳሴ፣ ልማት፣ ዕድገት፣ … “ሥራ ላይ ነን” … “መጪው ጊዜ ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ ነው!” … [Read more...] about የኢህአዴግ የኢኮኖሚ ስሌት
“ተፌ!”
ታጋይ፣ ከንቲባ፣ መከላከያ ሚ/ር፣ ምክትል ጠ/ሚ/ር፣ አቅም ገንቢ፣ አቅም ተገንቢ … ከዚህ ሁሉ አልፈው አሁን አቅማቸው ተገንብቶ የስፔስ (ሕዋ) ሳይንስ “አቅም ግንባታ” ለመሆን የበቁት ጡረተኛው ተፈራ ዋልዋ “የኢትዮጵያን የሕዋ (ስፔስ) ሳይንስ ሶሳይቲን” ገንብተው በሪፖርተር በኩል ብቅ ብለዋል፡፡ “አቅም ገንቢ ሚ/ር” በነበሩበት ወቅት “ሂድና ከአባዱላ ተማር የአንተ አቅም ግንባታ እንኳን አቅም ሊገነባ ያለውንም ሊያስቀጥል አልቻለም” ተብለው በአቶ መለስ የተገመገሙት አቶ ተፈራ አቅማቸው ተገንብቶ ለስፔስ መድረሱን “ባለራዕዩ መሪ” ሳያዩና ሪፖርተር ላይ ሳያነቡ መሰዋታቸው አቶ ተፈራን እጀ ሰባራ አድርጓቸዋል፡፡ የአላሙዲን “ወዳጅ” ሪፖርተር የአቶ ተፈራን አንደበት ገድቦት ነው እንጂ ተፈራ “ሼኸ፣ ዶ/ር፣ አቅም አስገንቢ … አላሙዲንን” ባነሱበት አንደበታቸው በግል ጄታቸው … [Read more...] about “ተፌ!”
“ይድረስ ከየካቲት ለግንቦት”
“. . . ይህንን የትግሉን ህዝባዊ ገፅታ ችላ ብለን እነዚህን ሚሊዮኖች የሚያካትት ህዝባዊ የትግል ማእበል ለመቀስቀስ፣ መቀስቀስ ብቻ ሳይሆን ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችለን የጋራ ስትራቴጂ አውጥተን ካልተንቀሳቀስን በስተቀር “በእኛና በእነሱ” መሃከል በተወሰነ የትግል ክፈፍ ከብረት ድስትና ከሸክላ ድስት ፍልሚያ፤ ሸክላ በአሸናፊነት ይወጣል በሚል የአጉል ህልም ዓለም ውስጥ ነን ማለት ይሆናል፡፡” ዶ/ር ነገደ ጎበዜ በምርጫ 97 ወቅት አቶ መለስ ዜናዊ በፓርላማቸው ውስጥ ተቃዋሚዎችን ለመወንጀል እየተንጨረጨሩ ያነሱት ስም ነገደ ጎበዜ የሚለውን ነበር። ያ ስም እንደገና ተመልሶ መጥቷል። አሁንም ከመጽሐፍ ጋር ነው የመጣው። ዶ/ር ነገደ ጎበዜ “ይድረስ ከየካቲት ለግንቦት” የሚል አዲስ መጽሐፍ ይዘው መጥተዋል። ቀደም ሲል “ሕገ መንግሥት ምርጫና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ (ከትላንት ወዲያ … [Read more...] about “ይድረስ ከየካቲት ለግንቦት”
አኖሌ ሃውልት ፖለቲከኞችና የታሪክ ምሁራንን እያወዛገበ ነው
በምኒልክ ዘመን በኦሮሞ ተወላጆች ላይ ተፈፅሟል የተባለውን የጡትና እጅ መቁረጥ ኢ-ሰብአዊ ድርጊትና ጭፍጨፋ ለማስታወስ በሚል በአርሲ አኖሌ አካባቢ በ20 ሚሊዮን ብር የተሰራው ሃውልት፣ በቅርቡ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙክታር ከድርን ጨምሮ በርካታ የኦህዴድ ባለስልጣናት በተገኙበት ተመርቋል፡፡ ሃውልቱን ያሰራው አካል ያለፈን ታሪክ መዞ ቂም በቀልን ለማውረስ ሳይሆን ቀጣዩ ትውልድ ከአስከፊው ድርጊት እንዲማርና ወደፊት ድርጊቱ እንዳይደገም ነው ሃውልቱ የተገነባው ብሏል፡፡ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችና ምሁራን በበኩላቸው ለሁለት ተከፍለዋል፡፡ አንደኛው ወገን ሃውልቱ በህዝቦች መካከል ቅራኔና ቂም በቀል የሚፈጥር ነው በማለት ሲቃወም ሌላው ወገን በበኩሉ ድርጊቱ ዳግመኛ እንዳይከሰት መማርያ እንጂ የበቀል አይደለም ሲሉ የሃውልቱን መቆም ይደግፋሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ … [Read more...] about አኖሌ ሃውልት ፖለቲከኞችና የታሪክ ምሁራንን እያወዛገበ ነው
በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የተከሰተው ውጥረት ወደ ደም መፋሰስ እንዳያመራ አባላቱ ስጋታቸውን ገለጹ!
ከተመሰረተ 20 አመታትን እንዳስቆጠረ የሚነገርለት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር የተፈጠረው ቅራኔ መልኩን ለውጦ መቀጠሉን የሚናገሩት ምንጮች በቀደሞው የኮሚኒቲው ሊቀመንበር እና በማህበሩ ስራ አመራር መሃከል በተነሳው አለመግባባት የፊታችን አርብ ፌብሩዋሪ 21 /2014 ምሸት ስራ አመራሩ በጠራው የአባላት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ አሰቃቂ ነገር ሊፈጠር እንደሚችል ገልጸዋል፡፤ በቅርቡ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር የጠራውን የአባላት ሰብሰባ ተከትሎ የአምባሳደር መሃመድ ሃሰን የቅርብ ዘመድ እንደሆኑ የሚነገርላቸው ሼክ ሙስጠፋ ሁሴን ደጋፊዎቻቸውን ወደ አዳራሹ በማስገባት ከማህበሩ ሊቀመንበርነቴ የተነሳሁት ያለአግባብ ነው በሚል በኮሚኒቲው ሊቀመንበር ላይ ቡጢ በመሰንዘራቸው ተከትሎ በተቀሰቀሰው መለስተኛ ግጭት ስብሰባው ሳይጀመር መበተኑ ይታወሳል። ይህ በዚህ እንዳለ የአምባሳደር መሃመድ … [Read more...] about በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የተከሰተው ውጥረት ወደ ደም መፋሰስ እንዳያመራ አባላቱ ስጋታቸውን ገለጹ!
የጅዳ ቆንስል ሃላፊ ዘነበ ከበደ ከኃላፊነታቸው ተነሱ!
* ትናንት ረፋዱ ላይ በገደምዳሜ "ጉልቻ ቢቀያየር ..." ብለን ያንሹካሾክነው መረጃ ተረጋገጠ! * ለጊዜው ቆንስል ጀኔራሉን ተክተው በጊዜያዊነት ቆንስል መስሪያ ቤቱን ለቀጣይ ሁለት ወራት የሚያስተዳድሩት በቆራጥ አመራራር ብቃታቸው የማይመሰገኑት ቆንስል ሸሪፍ ከይሩ ናቸውም ተብሏል። * ቆንስል ጀኔራል አቶ ዘነበ ከበደ ትናንት ምሽት ጉዳዩን ለማሳወቅ የኢህአዴግ ድርጅት አባላት ስብሰባ ጠርተው እንደነበርና አብዛኛው አለመገኘታቸው ታውቋል። ድርጅት አባላት በተለይም ከጎናቸው የማይጠፉ የነበሩት ተጽዕኖ ፈጣሪ የህወሃት አባላት እንኳ አልተገኙም ተብሏል። አቶ ዘነበ ከበደ በቆንስሉ ዙሪያ የህወሃት አባላትን አምባገነንነትን በማውረድና በማቀዝቀዝ፣ በሙስና፣ በድለላ፣ በማጭበርበር ስራ በቆንስሉ ዙሪያ የነበሩትን በማጥፋት እና በሌብነት አካባቢውን በማጽዳት ይታወቃሉ። ህግ አዋቂ ሆነው … [Read more...] about የጅዳ ቆንስል ሃላፊ ዘነበ ከበደ ከኃላፊነታቸው ተነሱ!