ሃገራችን በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ ነው ያለችው። ይህ ቀውስ ወደ እርስበርስ ጦርነት እያመራ ይገኛል። ጉዳዩ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ላይ ጥቅም ያላቸው የውጭ ዜጎችንም ማሳሰቡ አልቀረም። በሆላንድ፣ ዘ ሄግ ከተማ፣ ዲያማንት ኮሌጅ 24 ሴፕቴምበር 2016 በተደረው በዚህ ወርክሾፕ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና የሆላንድ ዜጎች ተገኝተው ነበር። በወርክሾፑ እንዲወያዩ የተጋበዙት ታዋቂው ፕሮፌሰር ጆን አቢንክ፣ መስፍን አማን እና ገረሱ ቱፋ ናቸው። አወያዮቹ ሚ/ር ፍራንስ እና አብይ አሸናፊ ነበሩ። ተናጋሪዎቹ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ከፍተኛ ቀውስ በማስረጃ እያጣቀሱ ካብራሩ በኋላ የገዥው ፓርቲ አጠያያቂ ህጋዊነት እና የማክተሙ አዝማምያን ያመላከተ ድምዳሜ ሰጥተዋል። መጪውን ሁኔታ የሚጠቁሙ ሶስት ቢሆኖች (Scenarios) ላይም የውይይቱ ተሳታፊዎች አስተያየቶቻቸውን … [Read more...] about የሆላንዱ ወርክሾፕ – ኢትዮጵያ እና መጭው የርስበርስ ጦርነት
Politics
“ይቺ ሀገር እንደ ሀገር እንድትቀጥል ከተፈለገ እኛ አድማጭ እናንተ ተናጋሪ የምትሆኑበት አካሄድ ማክተም አለበት”
በዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ካሳ ተ/ብርሀን አጠቃላይ የውይይት መድረኩ መነሻ አሳብ ትረካ እና የእለቱ የውይይት አጀንዳ በሆነው ያለፉት 25 ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ጉዞ ዙሪያ የሚያጠነጥን ገለፃ በኋላ በምርጦቹ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የተነሱ አስተያቶች እና የአካሄድ ጥያቄዎች:- 1. የመጀመሪያ ተናጋሪ፡- 1.1 “የዚህ ወይይት አጀንዳ ከጠበኩት በታች ወርዶብኛል በወላይቲኛ አንድ አባባል አለ - ያቺ እንትን'ኮ ወደቀች ቢሏት፤ ቀድሞም አቀማመጧ ለመውደቅ ነው አለች”፡፡ 1.2 “ካሳ! አንተ ሚኒስትር ነህ በዛ ላይ የዩኒቨርሲቲያችን የቦርድ ሊቀመንበር በዚህ ሁሉ ኃላፊነት ውስጥ ሆኖ PhD candidate መሆን አይቻልም ስለዚህ ስራህን ልቀቅ” 1.3 “ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ይምጣና ያወየን፣ እናንተ ውረዱና ከእኛ ጋር ተቀመጡ” 2. ሁለተኛ ተናጋሪ … [Read more...] about “ይቺ ሀገር እንደ ሀገር እንድትቀጥል ከተፈለገ እኛ አድማጭ እናንተ ተናጋሪ የምትሆኑበት አካሄድ ማክተም አለበት”
የተወጠረችው አዲስ አበባ ታስፈራለች – ብሶት ይንፈቀፈቅባታል!!
እድሜው አርባዎቹን ስለመሻገሩ ገጹ ይናገራል። በተፈጥሮ ያለው እርጋታ አዲስ አበባ ካጋጠመው ትንግርት ጋር ተዳምሮ አፍዞታል። ፊቱን ፈገግ የሚያደርገው ስለ አዲስ አበባ አራዳዎች ሲናገር በቻ ነው። ጨዋታውን የጀመረው በጫማ አሳማሪዎች ነበር። ጫማ አሳማሪዎች ደረጀ ወጥቶላቸዋል። “የታቀፉና ያልታቀፉ” ሁሉንም ገጠመኞቹን ሲያስረዳ “አዲስ አበባ እንደ ወበቅ ነች” ይላል። የወበቅ ጭንቀት የሚለቀው በደንብ ሲዘንብና አየሩን አፍኖ የያዘው ደመና ሲገፈፍ ነው። ወበቅ ለሱ በሽታ ነው። ነዋሪነቱ አውሮጳ ሲሆን አዲስ አበባ የከረመበት ምክንያት ቤት ቢጤ ስላለው እሱኑ ሸጦ ለአንዴና ላልተወሰነ ጊዜ የሚወዳትን “ወበቃም” ከተማ ለመለየት ነው። ቦሌ ፒኮክ ቁጭ ብለን ስናውጋ ቀድሞ አደራ ያለኝ ፊቱ ማስታወሻ አውጥቼ የሚነግረኝን እንዳልጽፍ ነው። ለወትሮም ቢሆን ስለማላደረርገው ተስማማሁና አወጋን። … [Read more...] about የተወጠረችው አዲስ አበባ ታስፈራለች – ብሶት ይንፈቀፈቅባታል!!
ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር
የአፍሪካ ነፃነት አብሪ ኮከብና በጀግና ህዝቧ አኩሪ ተጋድሎ ባለክብር የነበረቺው ኢትዮጵያ ዛሬ በከፋ ፈተና ውስጥ ገብታለች። በብርቱ ትግልና ጥንቃቄ መወገድ ያለባቸው ያገርና የህዝብ ደህንነት ስጋቶች ከፊቷ ተጋርጠዋል። የርስ በርስ ጦርነት ስጋት፣ የአስተማማኝና ዘላቂ ሰላም እጦት፣ የማእከላዊ መንግስት አቅጣጫ ብዥታና የውጭ ጠላት ስጋት፣ ጥቂቶቹ ናቸው። እነዚህንና መሰል ያገርና ህዝብ ደህንነት ስጋቶች ለማስወገድና ጤናማ የፖለቲካ ድባብ ለመፍጠር ባስቸኳይ መንቀሳቀስና ሀገርና ህዝብን ካሳፋሪ ውድቀት ማዳን ያስፈልጋል። በኢትዮጵያና ህዝቧ ላይ ያንዣበቡትን እነዚህን አደጋዎች ማስወገድ የሚቻለው እንዴት ነው? በእርግጥስ ይቻላል? እነዚህን ያገርና የህዝብ ህልውና ፈተናዎች በማስወገድ የኢትዮጵያን ሁኔታ ሰላማዊ አቅጣጫ እንዲይዝ ማድረግ የሚችለውስ ማነው? የሁሉም ጥያቄዎች መልስ … [Read more...] about ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር
መልዕክት ለመምህራን
እንደሚታወቀው ከቅርብ ቀናት በፊት ከመስከረም 4 ጀምሮ የሚሰጠውን የመምህራን ስልጠና በምን መልኩ ወደ ተቃውሞ መድረክ መቀየር እንደምንችል መምህራኖችን መጠየቃችን ይታወሳል። መምህራኖችም ግልፅ በሆነ ቋንቋ ሀሳባቸውን ገልፀውልናል። ለዚህም ልናመሰግናቸው እንወዳለን። እኛም ሀሳባቸውን ጨምቀን አቅርበናል። ከዛ በፊት ግን ይህንን ስብሰባ መቃወም ለምን እንደሚያስፈልግ መግለፁ ተገቢ ነው። 1) ይህ ስብሰባ መምህራን ሙያቸውን የሚያሻሽሉበት ሳይሆን ገዥው ፖርቲ የራሱን ፕሮፖጋንዳ የሚነዛበት የፖለቲካ መድረክ ነው። ይህንን ደግሞ ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድና ለስልጠናው ከተዘጋጁት ማኑዋሎች መረዳት ይቻላል። ስለዚህ ከዚህ ስልጠና ለመማር ማስተማሩ ሂደት የሚጠቅም አንዳች ነገር አይኖርም። 2) ወያኔ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ለመፍታት ወስኗል። ይህንን ምርጫም … [Read more...] about መልዕክት ለመምህራን
#ተቃውሞ #እምቢተኝነት #ተጋድሎ
እንባ እንባ ይለኛል ይተናነቀኛል እንባ ከየት አባቱ ደርቋል ከረጢቱ: ሳቅ ሳቅም ይለኛል ስቆ ላይስቅ ጥርሴ ስቃ እያለቀሰች መከረኛ ነብሴ:: (በአሉ ግርማ “ኦሮማይ”) ምነው! ፈጣሪ አምላክ! አላለቅስም ያልኩት ... እንባ የፈሪ ነው ብዬ ዋጥ ያ’ረኩት፣ አይቻል ተችሎኝ ይዤው የከረምኩት፣ ገንፍሎ ወጣና እንባዬ ፈሰሰ ጉንጮቼን ሰንጥቆ ፌቴን አዳረሰ በዛ እንባዬ መሀል አንገቴን አቅንቼ ለፈጣሪ ጮኽኩኝ! እጆቼን ዘርግቼ ምነው? ፈጣሪ አምላክ ምነው! ረሳኸን ምነው! ይሄን በደል አላይልን አልከን ምነው? የኛን ጩኸት ሰምተህ ጨከንክብን ብዬ ወተውትኩት አልኩበት እዬዬ አሁንም ይፈሳል አልቆመም እንባዬ ምነው! ፈጣሪ አምላክ! ... ወለላዬ የዛሬ 25 ዓመት ህወሃት የጀመረው በዚህ ነበር - … [Read more...] about #ተቃውሞ #እምቢተኝነት #ተጋድሎ
ኢትዮጵያ፡ #ከተቃውሞ እና #ከተጋድሎ በኋላ!?
አሰላሙ አሌይኩም፣ እንደምን አላችሁ፣ አካም ጂርቱ፣ እንደምን አረፈዳችሁ (good afternoon everyone)፡፡ የኢትዮጵውያን ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ኅብረት በዚህ ስብሰባ ላይ እንድናገር ስለ ጋበዘኝ ልባዊ ምስጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ፡፡[1] ከእናንተ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጋር በመሆን ስለምትወዷት አገራችን የወደፊት ሁኔታ ለመወያየት መብቃት ታላቅ ዕድል ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት አገራችን በከባድ ቀውስ ውስጥ እንደምትገኝ ሁላችንም የምናውቀው ሃቅ ነው፤ ይህም ቀውስ በአንድ ጊዜ የተከሰተ ሳይሆን ለዓመታት ሲጠራቀምና ሲከማች የቆየ ነው፡፡ የአገራችን የወደፊት ሁኔታ ሁላችንንም የሚያሳስበን በመሆኑ እናንተም ይህንኑ ሃሳብ እንዳቀርብ በጠየቃችሁኝ መሠረት እኛ ኢትዮጵያውያን በኅብረት በመሥራት ለአገራችን የተሻለ የወደፊት ተስፋ ማምጣት እንዴት እንደምንችል ሃሳቤን ከዚህ … [Read more...] about ኢትዮጵያ፡ #ከተቃውሞ እና #ከተጋድሎ በኋላ!?
ህወሃት/ኢህአዴግ በአማራው ሕዝብ ላይ የዘር ዕልቂት (genocide) አወጀ
በአማራ ክልል እየተቀጣጠለ የመጣውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት (#AmharaResistance) ፖለቲካዊ መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ የመከላከያ ኃይል እርምጃ እንዲወስድ ሃይለማርም ደሳለኝ በኦፊሴል አዟል፡፡ በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) ሙሉ ቁጥጥር ሥር ያለው የሃይለማርያም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን በየቦታው “በቃን፤ አንፈልግም” የተባለውን የህወሃት የበላይነትን እንደገና ለማስፈን የጦርነት አዋጅ አውጇል፡፡ በኦሮሚያ (#OromoProtests) ለ10 ወራት የዘለቀው የኦሮሞን ሕዝብ የመፍጀት ሥልታዊ ጥቃት አሁንም የበርካታዎችን ደም እያፈሰሰ ባለበት ባሁኑ ወቅት በአንድ ክልል ሕዝብ ላይ የተነጣጠረው ይህ በሃይለማርያም ትዕዛዝ የተሰጠው የህወሃት እርምጃ ታሪክ የማይረሳው፣ ሰላም ሊያመጣ የማይችል፣ የዕድሜ ልክ ቁርሾ የሚያስከትል የዘር ማጥፋት (genocide) ወንጀል … [Read more...] about ህወሃት/ኢህአዴግ በአማራው ሕዝብ ላይ የዘር ዕልቂት (genocide) አወጀ
ኦሮሞና አማራ – “ሁለት ዛፎች”!
ኦሮሞ እና አማራ “እሣት እና ጭድ ናቸው” ብላችሁ ክብሪት ለመጫር ለምትቋምጡ የወያኔ ሎሌዎች የሚከተለውን ብትገነዘቡ መልካም ነው፡፡ 1) ኦሮሞ እና አማራ መታየት ያለባቸው እንደ እሳት እና ጭድ ሳይሆን ጎን ለጎን በቅለው ለረጅም ጊዜ አብረው እንዳደጉ ትልልቅ ዛፎች ነው። እነዚህ ዛፎች ለረዥም ጊዜ ተጎራብተው ከመኖራቸውና ከግዙፍነታቸው የተነሳ በመሬት ውስጥ የተሳሰሩት ሥሮቻቸው ምግብ ሊሻሙ ይችላሉ። በአየር ላይ የሚነካኩት ቅርንጫፎቻቸው በንፋስ ጊዜ እርስበእርስ ሊላተሙ ይቻላሉ። ነገር ግን ዛፎቹ ሥር የሰደዱና የተዋሃዱ እንደመሆናቸው መቼም ውሃ አያጡምና፣ እንደ ጭድ ደርቀው በክብሪት እሣት አይቀጣጠሉም። 2) ምናልባት ከሁለቱም ዛፎች ደርቀው የረገፉ ቅጠሎችን እና ጭራሮዎችን ተጠቅማችሁ እሳት መለኮስ ካሰባችሁም ጉዳቱ ለናንተው እንደሚያመዝን እውቁ። የምትለኩሱትን እሳት የንፋስ … [Read more...] about ኦሮሞና አማራ – “ሁለት ዛፎች”!
የሰሜን ምዕራብ ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ ነገ…
* ኢህአዴግ የቁልቁለት ጉዞውን ተያይዞታል * ከገዳዮች ቁጥር በላይ ለመሞት የተዘጋጀዉ ህዝብ ይበልጣል እንደ መግቢያ የኢትዮጵያን ነገረ-ፖለቲካ በቅርበት የሚከታተሉ የአገር ውስጥና የምዕራቡ አለም ምሁራን የድህረ-መለስ ኢህአዴግ ፖለቲካዊ ማሻሻያዎችን ያደርጋል ብለው በተስፋ ቢጠብቁም ከታሰበው በተቃራኒ መንገድ ሲጓዝ እየታየ ነው። ተራማጅ የፖለቲካ ሀሳብ ያረጠበት ድርጅት አፈናና ግድያ መገለጫው ሆኗል። የአገዛዙን ምሰሶ ለማጥበቅ ሲባል ህገ-መንግስታዊ ድጋፍ የሌላቸውን የፖለቲካ ሹመቶች በመንግስታዊ መዋቅር ከመሰግሰግ ጀምሮ በፓርቲና በመንግስት መካከል ፍጹም ልዩነት የለሽ አሰራሮችን አጠንክሮ መጓዝን መፍትሄ አድርጎ ይዞታል። በአራት ነጥብ ግትር አቋም የታጠረው ኢህአዴግ፤ የፖለቲካ ተቋማት የፖለቲካ ብዝሃነትን እንዲያስተናግዱ ምቹ መደላድል ከመፍጠር ይልቅ የአንድ ፓርቲ ፍጹም … [Read more...] about የሰሜን ምዕራብ ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ ነገ…










