• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት/ኢህአዴግ በአማራው ሕዝብ ላይ የዘር ዕልቂት (genocide) አወጀ

August 30, 2016 11:52 pm by Editor 4 Comments

በአማራ ክልል እየተቀጣጠለ የመጣውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት (#AmharaResistance) ፖለቲካዊ መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ የመከላከያ ኃይል እርምጃ እንዲወስድ ሃይለማርም ደሳለኝ በኦፊሴል አዟል፡፡

በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) ሙሉ ቁጥጥር ሥር ያለው የሃይለማርያም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን በየቦታው “በቃን፤ አንፈልግም” የተባለውን የህወሃት የበላይነትን እንደገና ለማስፈን የጦርነት አዋጅ አውጇል፡፡

በኦሮሚያ (#OromoProtests) ለ10 ወራት የዘለቀው የኦሮሞን ሕዝብ የመፍጀት ሥልታዊ ጥቃት አሁንም የበርካታዎችን ደም እያፈሰሰ ባለበት ባሁኑ ወቅት በአንድ ክልል ሕዝብ ላይ የተነጣጠረው ይህ በሃይለማርያም ትዕዛዝ የተሰጠው የህወሃት እርምጃ ታሪክ የማይረሳው፣ ሰላም ሊያመጣ የማይችል፣ የዕድሜ ልክ ቁርሾ የሚያስከትል የዘር ማጥፋት (genocide) ወንጀል ነው፡፡

ውሳኔውን ተወደደም ተጠላም “የአማራውን ሕዝብ ጨርሱት” የሚል ነው!

የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ያቀናበረውን ለማዳመጥ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

በሸገር ኤፌ.ም. የተሰራጨው መረጃ እንዲህ ይነበባል

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የተለያዩ አካባቢዎች ባለፉት 3 ቀናት ዳግም የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ መንግስት የፀጥታ ሃይሉን ማዘዙ ተሰማ፡፡

የክልሉ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በሶስት ቀናት በነበረው ተቃውሞ የሰዎች ህይወት መቀጠፉንና ንብረት መውደሙን ለሸገር ዛሬ ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የተለያዩ ከተማዎች ውስጥ የአገልግሎት መስጪያ ተቋማት አገልግሎት ተቋርጦ ነበር ሲሉም ነግረውናል፡፡

ህዝቡ የሚያሳቸውን ህጋዊ የመብት ጥያቄዎችን በሌላ መንገድ የሚወስዱ ወገኖች በክልሉ ያለውን ጥፋት በማባባሳቸው የመከላከያ ኃይል እርምጃ እንዲወስዱ በክልሉ መንግስት መታዘዙንም አቶ ንጉሱ ይናገራሉ፡፡

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ስር ከሚገኙ በደብረ ታቦር፣ በባህር ዳር፣ በጎንደርና በደብረ ታቦር የተነሱ ተቃውሞዎች ብዙ ንብረት መውደሙንና ህይወት መጥፋቱን የተለያዩ ወገኖች ሲናገሩ ተሰምቷል፡፡

ከ3 ቀናት በፊት በተነሳው ዳግም ግጭት ምክንያት በደብረ ታቦር ብቻ ስድስት ሰዎች ሞተዋል ሲል የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት መኢአድ ሲናገር ተሰምቷል፡፡

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊው አቶ ንጉሱ በበኩላቸው በ3ቱ ቀናት በታዩት ግጭቶች ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱና ንብረት እንደወደመ ተጠይቀው “ለጊዜው የሚባል ነገር የለም በቅርቡ ጥቅል መረጃዎች ይወጣሉ” ብለዋል፡፡ (የኔነህ ሲሳይ – SHEGER FM 102.1 RADIO)

ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. rasdejen says

    August 31, 2016 10:25 am at 10:25 am

    ጀግናዉ ዎሎ፤ጀግናዉ ሸዋ ሆይ፥፡

    የህወሃት ገዳይ ዎታደር አና ኣጋዜ ባንተ በኩል ኣድርጎ በጎጃምና በጎንድር ዎገኖችህን ሊጨፈጭፍ አየጎረፈ ነዉ። በምታዉቀዉ ጋራ፣ሸንተረር፣ሸለቆና መሿለኪያ አያጠመድክ መንገድ ላይ አንድታስቀረዉ በሰፊዉ ዎገንህ ስም ይህን ጥሪ ኣቀርብልሃለሁ። ተነስ የጀግንነትና ሰዉ ኣድን ታሪክ ኣሁን ስራ!!!! ተ….ነ…………ስ………….!!!!!!!!!!!!!!

    ጀግናዉ ጋየንት አና ጀግናዉ የፋርጣም ህዝብ ሾልኮ የሚሄደዉን ወገን ኣራጅ ሃይል እንድታስቀረዉ ጥብቅ ወገናዊ ጥሪ በወገን ስም ከአክብሮት ጋር ኣቀርባለሁ!!!!!!!!!!!!!

    እንዴ፤አትነሳም… እንዴ? https://www.youtube.com/watch?v=KmLwEgwBey8

    ለወገን ደራሽ ወገን ነዉ
    ይህ ጥሪ ከፍተኛ እድልም ነዉ፤ ኣጥብቀዉ እየተመኙ ያላገኙት በዙወች ነን
    እድልም ነዉና ኣይለፍችዉ፤ ኣይለፍሽ፤ኣይለፍህ!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

    Reply
  2. Naji says

    August 31, 2016 07:24 pm at 7:24 pm

    The deployment of such kind of heavy military hardware shows that trend — genocide. If it is real and true It is an unfortunate. I heard about the military movement but hardly saw such heavy military equipment.How can an entity endowed with human senses use such destructive, mass killing technology on unarmed civilians? It is unbelievable.
    I heard the PM’s proclamations. Most of us disagreed and acknowledged as irresponsible, short-sighted and egoistic.
    Most of us believe the demand and grievances of the people could have been handled and managed administratively through dialogue and consensus. The government talks about it but did not make it practical. What is the problem conversing peacefully with its own citizens?
    The government may have its own problem that makes it scare and not put face to face with its own people. I can’t give any rational justification. I am still bewildered, in no man’s land without direction, with no compass.
    Fortunately, I am pretty certain that whatever it takes, whatever happens, the Ethiopian people will soon decide everybody’s fate.

    Reply
  3. asrat says

    September 2, 2016 04:54 am at 4:54 am

    It’s called intimidation by way of deception. First for most you can
    Never defeat the people. And second if that is really the case who are
    You fighting with your own people? Or i guess not. Nothing can stop
    For what is coming, winning war using fake intimidation you tactics id an age old
    Secret. Even a frog fool her enemies spearing to be big, swollen.
    When the going gets tough the tough will get going. Lions really don’t
    Live long a slow shy turtles outlives lions 3 times as much. Weyane
    You have caused serious mark on Ethiopian sovereignty and the back
    Slash will come back to eradicate you once for all.

    Reply
  4. beya says

    September 11, 2016 09:07 pm at 9:07 pm

    ሁላችሁም ለራሳችሁ ጥቅም ነው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule