
“ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”፡፡ “(ትግሉን) በአንድ ጥላ ሥር እያስተባበርን ነው”፡፡
የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተነተነበት ጽሁፍ ላይ የጠቀሳቸው ሁለት ግለሰቦች የተናገሩት ነበር ከላይ የሰፈረው፡፡ ጋዜጠኛው ዘገባውን ሲጀምር “ኢትዮጵያ እየተሰነጣጠቀች ነውን” በማለት ይጠይቅና በሁሉም አቅጣጫ ያለውን አመለካከት ያሰፍራል፡፡ (ከዜና ዘገባው ጋር Violent Protests in Ethiopia በሚል ርዕስ የጸጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙትን አሰቃቂ ግፍ እና ጨካኝ ድብደባ እዚህ ላይ መመልከቱ የግድ ይላል)፡፡
“ልማት” አካሂዳለሁ የሚለው ህወሃት/ኢህአዴግ የሕዝብን መሠረታዊ ጥያቄዎች አለመመለሱን የሚያትተው ዘገባ የዓለምአቀፍ ቀውስ ቡድን ተመራማሪ የሆኑትን ራሺድ አብዲ “ይህችን አገር አንድ አድርጎ ወደፊት ለመግፋት ሁልጊዜ አስቸጋሪ” እንደሆነ በመጥቀስ አሁን ለሚታየው ሕዝባዊ ዓመጽ ማብብራሪያ ይሰጣል፡፡
ኢኮኖሚውን አሳድጌአለሁ የሚለው ኢህአዴግ የሰብዓዊ መብት መግፈፉንም አብሮ እንዳሳደገው የሚናገረው የዜና ትንተና በአገር ውስጥ የሚደረገው አፈና፣ ግድያ፣ እስር፣ እንግልት፣ … በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ምስክርነታቸውን ሲሰጡበት የቆየ መሆኑን ያስረዳል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚቀርበው አቤቱታ ስፍር ቁጥር የለውም፤ መሬት ከመንጠቅ ጀምሮ የፓርላማ ወንበርን መቶ በመቶ የራስ እስከማድረግ እና የአንድን ቡድን የበላይነት ከፍ እስከማድረስ የዘለቀ ነው፡፡ ይህም በየጊዜው የፈጠረው ምሬት አሁን ያለበት ሁኔታ ላይ እንዲደረስ አድርጎታል፡፡
በኢትዮጵያ የዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ስዩም ተሾመ የተናገሩትን የዜና ዘገባው ይጠቅሳል፤ “ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”፡፡
ለዚህ አገር አቀፋዊ ዓመጽ ምክንያቶች ናቸው ያላቸውን ሦስት ነጥቦችን ጋዜጠኛው ያነሳል፤
- ልባምስልኮች – ዘመናዊዎቹ “ስማርት” ስልኮች (ልባምስልኮች) በርካታ መረጃ በማስተላለፍ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡ የኢንተርኔት አገልግሎት አገዛዙ እንደፈለገ እየከፈተ የሚዘጋው ቢሆንም እንኳን ወጣቱ ትውልድ እነዚህን ስልኮች በመጠቀም ፎቶ በማንሳት፤ ቪዲዮ በመቅረጽ፤ በማኅበራዊ ድረገጾች በማስተላለፍ መረጃ ይለዋወጣል፡፡ ወጣቶች በነዚህ ስልኮች ግንኙነት በማድረግ ለተቃውሞ ሰልፍ መውጣታቸውን ጋዜጠኛው እማኝ አድርጎ ይጠቅሳቸዋል፡፡
- በአማራና በኦሮሞ ወገኖች በመካከል የተፈጠረው የጋራ እንቅስቃሴ ሌላው ተጠቃሽ ነጥብ ነው፡፡ ህወሃት የሥልጣን ዘመኑን ለማራዘም በሁለቱ መካከል ልዩነትን እያሰፋ የተጠቀመበትና በታሪክ በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ቁርሾ በህወሃት አማካኝነት ለተፈጠረው በደል እንዲተባበሩ ምክንያት ሆኗቸዋል፡፡ ሁኔታዎች መቀየራቸውን በመናገር ጋዜጠኛው በኦሮሞ ትግል ውስጥ አመራር የሆኑት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር ሙላቱ ገመቹ “(ትግሉን) በአንድ ጥላ ሥር እያስተባበርን ነው” ማለታቸውን ጠቅሶ የትብብሩን አቅጣጫ ጠቁሟል፡፡ ከኢትዮጵያ ሕዝብ በአናሳነት የሚጠቀሰው የትግራይ ክፍል (ስድስት በመቶ ነው) የአገሪቱን የወታደራዊ፣ የስለላ፣ የደኅንነት፣ የንግድና የፖለቲካ መዘውሩን በእጁ ማስገባቱን በመጥቀስ የግፍ መበራከት ሁለቱን ወገኖች አስተባብሯቸዋል የሚል እንደምታ ይሰጣል፡፡
- ህወሃት እንደ መለስ ዓይነት መሰሪ መጣቱ አሁን ለሚታየው ተቃውሞ እንቅስቃሴ ምክንያት እንደሆነ ዘገባው ያስረዳል፡፡ መለስ የሚመጣባቸውን ውድቀትና ጥፋት አስቀድሞ በማየት ወጥመድ ከማዘጋጀት እስከ ማለሳለስ ድረስ የመጠቀም ብቃት የነበራቸው መሆኑን በማብራራት የመለስ ጫማ የሰፋቸው የደቡቡ ኃይለማርያም ደኅንነቱንና ስለላውን በሚቆጣጠሩት ትግሬዎች አመኔታ እንደሌላቸው ይናገራል፡፡
ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ የበለጠ ደም መፋሰስ እንደሚኖርና አሁንም በየማኅበራዊ ድረገጾች እንዲሁም ተቃውሞ በተደረገባቸው አንዳንድ ቦታዎች ከጥላቻ ጀምሮ እስከ ጥቃት የዘለቀ በግልጽ የሚታይ እንቅስቃሴ እንዳለ ጋዜጠኛ ጌትልማን ይናገራል፡፡
የምዕራብ ተላላኪና አሽከር በመሆን በሥልጣን ለመቆየት የበቃው ህወሃት/ኢህአዴግ ከአንጋሾቹ በሚያገኘው ዕርዳታ ዜጎችን መግደሉና መብቶችን ማፈኑ ምዕራባውያንን ባልፈለጉበት ቦታ ላይ አስቀምጧቸዋል፡፡ የህወሃትን አሠራር ለመቃወምም ለመንቀፍም አጣብቂኝ ውስጥ አስገብቷቸዋል፡፡ ዴሞክራሲን መጨፍለቅና ሎሌያቸውን መደገፍ ወይም ፊታቸውን ማዞርና ከህዝብ ጋር መቆም!
ራሺድ አብዲ ይህ ሁኔታ ምዕራባውያንን “በጣም ቀጭን በሆነ ገመድ ላይ እንዲራመዱ እያደረጋቸው ነው” ማለታቸውን ጠቅሶ ዘገባው ያበቃል፡፡
“የትውልድ ዓመጽ” የሆነው የሰሞኑ የነጻነት ጥያቄ ህወሃትን ብቸኛ እያደረገው እንደሆነ በስፋት ይነገራል፡፡ አፍቃሪ ህወሃት የሆኑ በኦሮሞና በአማራ መካከል ልዩነቶች መኖራቸውን በመናገር አሁንም ልዩነቶችን ለማስፋት የሚደርጉት ሙከራ የበለጠ የመለስን እኩይ ባህርይና “እውነተኛ ውርስ” በግልጽ ያስረዳ እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡ ከዚህ ሌላ ግን አሁን በኢትዮጵያ የተነሳው የተቃውሞ እንቅስቃሴ በአንድ ፓርቲ ወይም ቡድን የተቀሰቀሰና ለአንድ ፓርቲ የሚገዛ ሳይሆን የሕዝብ ዓመጽ ነው፡፡ አብዛኛዎቹ ደግሞ ህወሃት/ኢህአዴግ ስልጣን በያዘ ጊዜ ህጻናት የነበሩ ወይም ገና ያልተወለዱ፤ ህወሃት ግፍ እየፈጸመ ለዓቅመ ዓመጽ ያደረሳቸው ናቸው፡፡
“ትውልድ አምጿል”!
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
I love your conclusions. Most youths have been born in the last twenty five years and living in misery. They have tried to be part of the system and help build their poor country. Instead they have been pushed away by the group of greedy, corrupt,nepotism system. They have been raising their concern that the ruling party and the government is doing is not right. Instead they have been labeled as, for example, if one is an Oroma his narrow minded, if one is Amahara he is remnants of Derge and feudalism. If one is from Tegray and other regions he is sick and deviant. Shabia puppet, redevelopment and anti peace elements, antidemocratic nationalist chauvinist and the like are some of the names who ask questions and demand answers.
How long do the ruling party think it can go on like this? It may think for the next fourty fifty years. That is abject madness and collusion with reality.
The people are speaking. They want their country. Livelihoods, political and economic rights into their hands. Right know every Ethiopian youth is aware that the country belongs to all of them. Everybody thinks that they were misled and regrets the mistakes they have been through.
The struggle is underway in full scale. There is no Turing back. The objective is to gain the souvernity of the people. The goal is brotherhood, sisterhood, the keeper of each other, living in peace and prosperous life. I hope everything will work out well.
ጎልጉል፤ ጻድቃን በህወሓት ብሎግ ሆርን አፌርስ ስለ ለጠፈው ጽሑፍ ትንሽ ልበል። ሁለቴ በጥንቃቄ አንብቤለታለሁ። በዝብዝቡ መንገላታት አያሻንም። በግልጽ ያስቀመጣቸውን እንመልከት። 1/ ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታ ከጓደኞቼ ጋር ተመካክረን ነበር ብሎናል፣ ጓደኞቹ እነማን እንደሆኑ ግልጽ ነው 2/ ስለኢትዮጵያ የነገረን የማናውቀውን አይደለም፤ ህወሓትን አሳጥቶ መጻፉ ለአንዳንዶች አስገራሚ መስሎ ይታይ ይሆናል። ጉዳዩ ግን፣ ህወሓት በራሱ ሊለው የማይችለውን ተመካክረው እያለላቸው ነው 3/ ምርጫ ይኑር፣ የምርጫ ውጤት ለመቀበል ፈቃደኛ መሆን አለብን ብሎአል 4/ የርሱ ሃብት ማካበት በራሱ ጥረት እንደሆነ ሊያሳምነን ሞክሯል 5/ ስዬን ጠቅሷል 6/ የኢትዮጵያን ሠራዊት በትኖ የህወሓትን መተካቱን በወቅቱ “National defense and economic development”ብሎ ያቀረበውን ሰነድ ቆንጽሎ ሙሉውን ሰነድ ሊደብቀን ሞክሯል 7/ ዛቻ ብጤም አሰምቷል፤ ካለዚያ ደም በደም እንሆናለን ብሎ። ድምዳሜዬ? 1/ የህወሓት አካሄድ እንደማያዋጣ ተረድቷል፤ ስዬ እንደሞከረው [ትዝ ይልሃል? አንዴ እስር ቤቱ ኦሮምኛ ይናገራል ያላትን?] 2/ ደቡብ ሱዳን ላይ ለአሜሪካኖች ዓላማ አስተባባሪ ሆኖ እየሠራ ነው፤ ስዬ ምዕራብ አፍሪካ ላይ። 3/ ህወሓት ከመለስ ሞት በኋላ መስማማት ስላልቻሉ ኃ/ማርያምን አስቀምጠው ካብ ለካብ እየተያዩ ነው፤ “ኮሌክቲቭ ሊደርሽፕ” በሚል ማጭበርበሪያ ኃ/ማርያምን ደብረጽዮን፣ በረከት፣ አባይ፣ ብርሃነ ገ/ክ ገንዘቡን ሥልጣኑን ተቀራምተውታል፤ አንዱ ችግር ይኸው ነው። አሜሪካኖች የችግሩን መጠን ያውቁታል፤ አታላይነቱ ስለገባቸው የመለስ መወገድ እረፍት ሆኗቸው ነበር፣ አሁን ደግሞ የዋለለ ጉዳይ እንዲቀጥል አይፈልጉም። ህወሓት ሶማሌን፣ ደቡብ ሱዳንን በኢትዮጵያውያን ደም እየነገደ አመቻችቶላቸዋል። ይህን ነገር መፍትሔ ስጡ እያላቸው ነው። የወገኖቻችን ደም መፍሰስ ምንም ያልመሰለው ለዚህ ነው። በተባበሩት መንግሥታት ጸጥታ ጉዳይ ኢትዮጵያ ወንበር ያገኘችው በአሜሪካና በእንግሊዝ እርዳታ ነው። አሁን የሚፈለገው ጻድቃን [ወይም ስዬ] እንደ ታዳጊ ቀርቦ የአሜሪካኖችን ዓላማ ያስፈጽማል፤ በዚያውም የህወሓትን የበላይነት ይታደጋል ማለት ነው። ፕሮፌሰር መሳይ ይህን እንዴት እንዳልተረዳው ገርሞኛል። በናይጄሪያ ያደረጉት ይህንኑ ነው፤ ጆናታን ጉድለክ በጄኔራል ሙሐመዱ ቡሃሪ የተተካው በአሜሪካኖች እርዳታ ቦኮሃራምን ለመዋጋር በሚል ነው። ብዙ ሌላ ሐተታ በማቅረብ እንዳላሰለች ጉዳዩን ለማስረዳት የቀረበው በቂ ይመስለኛል። [በነገራችን ላይ የህወሓት ብሎግ ሆርን አፌርስ በእንግሊዝኛ የተረጎሙት ለህወሓት አመቻችተው ነው፤ ጊዜ ካገኛችሁ ትርጉሙን ከአማርኛው ቅጂ ጋር አስተያዩ። አሁንማ የጻድቅቃንን ኢንተርቪው እያሰሙን ነው። ፐብሊክ ሪሌሽንስ ነው ነገሩ፤ ለምርጫ ውድድሩ ፓርቲ ሳይኖር ተጀምሯል!]። ሌላ የሚያሣስበው የነዶ/ር ብርሃኑ መወላገድ ነው፤ ከጻድቃን ባላነሰ ለአገራችን መቅሠፍት ናቸው የሚል ግንዛቤ ላይ ደርሻለሁ። ብትፈቅዱ ይህን አስተያየቴን አትሙልኝ። እኔም ለአገሬ ማሰቤ ነውና፣ ሌሎች ይስሙትና የሚመስላቸውን ግንዛቤ ይውሰዱ። አመሰግናለሁ።