• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መልዕክት ለመምህራን

September 15, 2016 08:12 pm by Editor Leave a Comment

እንደሚታወቀው ከቅርብ ቀናት በፊት ከመስከረም 4 ጀምሮ የሚሰጠውን የመምህራን ስልጠና በምን መልኩ ወደ ተቃውሞ መድረክ መቀየር እንደምንችል መምህራኖችን መጠየቃችን ይታወሳል። መምህራኖችም ግልፅ በሆነ ቋንቋ ሀሳባቸውን ገልፀውልናል። ለዚህም ልናመሰግናቸው እንወዳለን። እኛም ሀሳባቸውን ጨምቀን አቅርበናል። ከዛ በፊት ግን ይህንን ስብሰባ መቃወም ለምን እንደሚያስፈልግ መግለፁ ተገቢ ነው።

1) ይህ ስብሰባ መምህራን ሙያቸውን የሚያሻሽሉበት ሳይሆን ገዥው ፖርቲ የራሱን ፕሮፖጋንዳ የሚነዛበት የፖለቲካ መድረክ ነው። ይህንን ደግሞ ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድና ለስልጠናው ከተዘጋጁት ማኑዋሎች መረዳት ይቻላል። ስለዚህ ከዚህ ስልጠና ለመማር ማስተማሩ ሂደት የሚጠቅም አንዳች ነገር አይኖርም።

2) ወያኔ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ለመፍታት ወስኗል። ይህንን ምርጫም በ10 ወር ዉስጥ ከ1000 የሚበልጡ ንፁሀን ዜጎችን በመግደልና የወያኔ ቱባ ባለስልጣናት በሚያሰሙት ፉከራ አረጋግጠዋል። ስለዚህ ከዚህ የመምህራን ስብሰባ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ ለመፍታት የሚያስችል ነገር አይኖርም።

3) ይህ ስብሰባ የሚመራው በኦህዴድ መሪዎች ነው። እነሱም ሆኑ ድርጅታቸው በመምህራኑ ሊነሱ የሚችሉትን ጥያቄ የመመለስ ምንም አይነት ስልጣን የላቸውም። የኦህዴድ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ የገጠመውን ማስተር ፕላን ሰርዘናል ብሎ ለህዝቡ ቢነግሩም ሰሞኑን የወያኔ ቱባ ባለስልጣናት የሆኑት አባይ ፀሐዬና በረከት ስምዖን “ማስተር ፕላኑ ለጊዜው እንዲቆይ ተደረገ እንጂ አልተሰረዘም” ማለታቸው ኦህዴድም ሆነ የድርጅቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ምንም አይነት የመወሰን ስልጣን እንደሌላቸው የቅርብ ምሳሌ ነው።

ስለዚህ የታቀደውን የፕሮፖጋንዳ መድረክ መቃወም ይኖርብናል። ሆኖም ግን የሚደረገው ተቃዉሞ የጥቅምና ጉዳት ትንተና መሰረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። መምህራኖችን ማወያየት ያስፈለገበት ምክንያትም ይኸው ነበር። የቀረቡትን የተቃዉሞ አማራጮችን በዚህ መልኩ ገምግመውታል።

1) ከስብሰባው ሙሉ በሙሉ መቅረት (Boycott)። ይሄኛዉ እጅግ ተመራጭ ቢሀንም ሁሉም መምህራን ካልተሳተፉበት መምህራኑን ለደመወዝ ቅጣትና ከስራ ለመባረር አደጋ ያጋልጣል።

2) በስብሰባዉ ላይ መሳተፍና መድረኩን ሙሉ በሙሉ ወደ ተቃዉሞ መግለጫ መቀየር። ይህ የሰዎችን ቀልብ የሚገዛ ቢሆንም ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። ችግሮችን ለመፍታት በኦሆዴድ በኩል አቅም ከማጣትና በህወሀት በኩል ፍላጎት ካለመኖሩ በስተቀር በእስካሁኑ ሂደት መንግስት ጋር ያልደረሰ ጥያቄም ሆነ የመፍትሄ ሀሳብም የለም።ይህኛው አካሄድ የሚቀርቡትን ጥያቄዎችና ሀሳቦችን ቆራራጦ በሚዲያ በማቅረብ ለፕሮፖጋንዳ እንዲጠቀሙበት እድል ይሰጣቸዋል። ከሁሉም በላይ በመድረኩ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ጠንካራ መምህራንን ለይቶ ለመጉዳትም ያስችላቸዋል። ይህ ደግሞ ከዚህ በፊትም በተግባር ያየነው ነገር ነዉ።

3) በስብሰባው ላይ መሳተፍና ምንም አይነት ሀሳብም ሆነ ጥያቄ አለማንሳት (Silent Protest)። ይህ ከሁሉም ተመራጭ የሆነ የተቃዉሞ ዘዴ ነዉ። መምህራንን ለምንም አይነት አደጋ አያጋልጥም (It has Zero Cost) ። በአብዛኛው ዝም በማለት የጠላትን ልቦና ለማዳከምና ለማሸበር (Psychological Terror) ይረዳል። በተጨማሪም በመምህራኑ ዉስጥ አስርገው የሚያስገቧቸው አስመሳዮችና የመንግስት ካድሬዎችን ለመለየትና ለወደፊቱም ለመጠንቀቅ ይረዳል።

በመሆኑም ከነገ ጧት ጀምሮ ሁሉም መምህራን በስብሰባው በመገኘት በአንድነትና በፅናት በዝምታ ተቃውሟቸውን እንዲገልፁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ከዚህ በፊት ስታነሷቸው የነበሩት ጥያቄዎችና እናንተ ያፈራችኋቸው ተማሪዎቻችሁ ይህንን ስርዓት እንዳናጋው ሁላ በዚህ ስብሰባም ድምፃቹን በጋራ መንፈጋችሁ ይበልጡኑ ስርዓቱን ግራ ያጋባዋል።

በአንድነት ዝምታን በመምረጥ
ጠላትን ግራ አጋቡት!

#Oromoprotests

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule