• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መልዕክት ለመምህራን

September 15, 2016 08:12 pm by Editor Leave a Comment

እንደሚታወቀው ከቅርብ ቀናት በፊት ከመስከረም 4 ጀምሮ የሚሰጠውን የመምህራን ስልጠና በምን መልኩ ወደ ተቃውሞ መድረክ መቀየር እንደምንችል መምህራኖችን መጠየቃችን ይታወሳል። መምህራኖችም ግልፅ በሆነ ቋንቋ ሀሳባቸውን ገልፀውልናል። ለዚህም ልናመሰግናቸው እንወዳለን። እኛም ሀሳባቸውን ጨምቀን አቅርበናል። ከዛ በፊት ግን ይህንን ስብሰባ መቃወም ለምን እንደሚያስፈልግ መግለፁ ተገቢ ነው።

1) ይህ ስብሰባ መምህራን ሙያቸውን የሚያሻሽሉበት ሳይሆን ገዥው ፖርቲ የራሱን ፕሮፖጋንዳ የሚነዛበት የፖለቲካ መድረክ ነው። ይህንን ደግሞ ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድና ለስልጠናው ከተዘጋጁት ማኑዋሎች መረዳት ይቻላል። ስለዚህ ከዚህ ስልጠና ለመማር ማስተማሩ ሂደት የሚጠቅም አንዳች ነገር አይኖርም።

2) ወያኔ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ለመፍታት ወስኗል። ይህንን ምርጫም በ10 ወር ዉስጥ ከ1000 የሚበልጡ ንፁሀን ዜጎችን በመግደልና የወያኔ ቱባ ባለስልጣናት በሚያሰሙት ፉከራ አረጋግጠዋል። ስለዚህ ከዚህ የመምህራን ስብሰባ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ ለመፍታት የሚያስችል ነገር አይኖርም።

3) ይህ ስብሰባ የሚመራው በኦህዴድ መሪዎች ነው። እነሱም ሆኑ ድርጅታቸው በመምህራኑ ሊነሱ የሚችሉትን ጥያቄ የመመለስ ምንም አይነት ስልጣን የላቸውም። የኦህዴድ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ የገጠመውን ማስተር ፕላን ሰርዘናል ብሎ ለህዝቡ ቢነግሩም ሰሞኑን የወያኔ ቱባ ባለስልጣናት የሆኑት አባይ ፀሐዬና በረከት ስምዖን “ማስተር ፕላኑ ለጊዜው እንዲቆይ ተደረገ እንጂ አልተሰረዘም” ማለታቸው ኦህዴድም ሆነ የድርጅቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ምንም አይነት የመወሰን ስልጣን እንደሌላቸው የቅርብ ምሳሌ ነው።

ስለዚህ የታቀደውን የፕሮፖጋንዳ መድረክ መቃወም ይኖርብናል። ሆኖም ግን የሚደረገው ተቃዉሞ የጥቅምና ጉዳት ትንተና መሰረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። መምህራኖችን ማወያየት ያስፈለገበት ምክንያትም ይኸው ነበር። የቀረቡትን የተቃዉሞ አማራጮችን በዚህ መልኩ ገምግመውታል።

1) ከስብሰባው ሙሉ በሙሉ መቅረት (Boycott)። ይሄኛዉ እጅግ ተመራጭ ቢሀንም ሁሉም መምህራን ካልተሳተፉበት መምህራኑን ለደመወዝ ቅጣትና ከስራ ለመባረር አደጋ ያጋልጣል።

2) በስብሰባዉ ላይ መሳተፍና መድረኩን ሙሉ በሙሉ ወደ ተቃዉሞ መግለጫ መቀየር። ይህ የሰዎችን ቀልብ የሚገዛ ቢሆንም ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። ችግሮችን ለመፍታት በኦሆዴድ በኩል አቅም ከማጣትና በህወሀት በኩል ፍላጎት ካለመኖሩ በስተቀር በእስካሁኑ ሂደት መንግስት ጋር ያልደረሰ ጥያቄም ሆነ የመፍትሄ ሀሳብም የለም።ይህኛው አካሄድ የሚቀርቡትን ጥያቄዎችና ሀሳቦችን ቆራራጦ በሚዲያ በማቅረብ ለፕሮፖጋንዳ እንዲጠቀሙበት እድል ይሰጣቸዋል። ከሁሉም በላይ በመድረኩ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ጠንካራ መምህራንን ለይቶ ለመጉዳትም ያስችላቸዋል። ይህ ደግሞ ከዚህ በፊትም በተግባር ያየነው ነገር ነዉ።

3) በስብሰባው ላይ መሳተፍና ምንም አይነት ሀሳብም ሆነ ጥያቄ አለማንሳት (Silent Protest)። ይህ ከሁሉም ተመራጭ የሆነ የተቃዉሞ ዘዴ ነዉ። መምህራንን ለምንም አይነት አደጋ አያጋልጥም (It has Zero Cost) ። በአብዛኛው ዝም በማለት የጠላትን ልቦና ለማዳከምና ለማሸበር (Psychological Terror) ይረዳል። በተጨማሪም በመምህራኑ ዉስጥ አስርገው የሚያስገቧቸው አስመሳዮችና የመንግስት ካድሬዎችን ለመለየትና ለወደፊቱም ለመጠንቀቅ ይረዳል።

በመሆኑም ከነገ ጧት ጀምሮ ሁሉም መምህራን በስብሰባው በመገኘት በአንድነትና በፅናት በዝምታ ተቃውሟቸውን እንዲገልፁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ከዚህ በፊት ስታነሷቸው የነበሩት ጥያቄዎችና እናንተ ያፈራችኋቸው ተማሪዎቻችሁ ይህንን ስርዓት እንዳናጋው ሁላ በዚህ ስብሰባም ድምፃቹን በጋራ መንፈጋችሁ ይበልጡኑ ስርዓቱን ግራ ያጋባዋል።

በአንድነት ዝምታን በመምረጥ
ጠላትን ግራ አጋቡት!

#Oromoprotests

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule