• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መልዕክት ለመምህራን

September 15, 2016 08:12 pm by Editor Leave a Comment

እንደሚታወቀው ከቅርብ ቀናት በፊት ከመስከረም 4 ጀምሮ የሚሰጠውን የመምህራን ስልጠና በምን መልኩ ወደ ተቃውሞ መድረክ መቀየር እንደምንችል መምህራኖችን መጠየቃችን ይታወሳል። መምህራኖችም ግልፅ በሆነ ቋንቋ ሀሳባቸውን ገልፀውልናል። ለዚህም ልናመሰግናቸው እንወዳለን። እኛም ሀሳባቸውን ጨምቀን አቅርበናል። ከዛ በፊት ግን ይህንን ስብሰባ መቃወም ለምን እንደሚያስፈልግ መግለፁ ተገቢ ነው።

1) ይህ ስብሰባ መምህራን ሙያቸውን የሚያሻሽሉበት ሳይሆን ገዥው ፖርቲ የራሱን ፕሮፖጋንዳ የሚነዛበት የፖለቲካ መድረክ ነው። ይህንን ደግሞ ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድና ለስልጠናው ከተዘጋጁት ማኑዋሎች መረዳት ይቻላል። ስለዚህ ከዚህ ስልጠና ለመማር ማስተማሩ ሂደት የሚጠቅም አንዳች ነገር አይኖርም።

2) ወያኔ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ለመፍታት ወስኗል። ይህንን ምርጫም በ10 ወር ዉስጥ ከ1000 የሚበልጡ ንፁሀን ዜጎችን በመግደልና የወያኔ ቱባ ባለስልጣናት በሚያሰሙት ፉከራ አረጋግጠዋል። ስለዚህ ከዚህ የመምህራን ስብሰባ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ ለመፍታት የሚያስችል ነገር አይኖርም።

3) ይህ ስብሰባ የሚመራው በኦህዴድ መሪዎች ነው። እነሱም ሆኑ ድርጅታቸው በመምህራኑ ሊነሱ የሚችሉትን ጥያቄ የመመለስ ምንም አይነት ስልጣን የላቸውም። የኦህዴድ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከፍተኛ የህዝብ ተቃውሞ የገጠመውን ማስተር ፕላን ሰርዘናል ብሎ ለህዝቡ ቢነግሩም ሰሞኑን የወያኔ ቱባ ባለስልጣናት የሆኑት አባይ ፀሐዬና በረከት ስምዖን “ማስተር ፕላኑ ለጊዜው እንዲቆይ ተደረገ እንጂ አልተሰረዘም” ማለታቸው ኦህዴድም ሆነ የድርጅቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ምንም አይነት የመወሰን ስልጣን እንደሌላቸው የቅርብ ምሳሌ ነው።

ስለዚህ የታቀደውን የፕሮፖጋንዳ መድረክ መቃወም ይኖርብናል። ሆኖም ግን የሚደረገው ተቃዉሞ የጥቅምና ጉዳት ትንተና መሰረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። መምህራኖችን ማወያየት ያስፈለገበት ምክንያትም ይኸው ነበር። የቀረቡትን የተቃዉሞ አማራጮችን በዚህ መልኩ ገምግመውታል።

1) ከስብሰባው ሙሉ በሙሉ መቅረት (Boycott)። ይሄኛዉ እጅግ ተመራጭ ቢሀንም ሁሉም መምህራን ካልተሳተፉበት መምህራኑን ለደመወዝ ቅጣትና ከስራ ለመባረር አደጋ ያጋልጣል።

2) በስብሰባዉ ላይ መሳተፍና መድረኩን ሙሉ በሙሉ ወደ ተቃዉሞ መግለጫ መቀየር። ይህ የሰዎችን ቀልብ የሚገዛ ቢሆንም ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። ችግሮችን ለመፍታት በኦሆዴድ በኩል አቅም ከማጣትና በህወሀት በኩል ፍላጎት ካለመኖሩ በስተቀር በእስካሁኑ ሂደት መንግስት ጋር ያልደረሰ ጥያቄም ሆነ የመፍትሄ ሀሳብም የለም።ይህኛው አካሄድ የሚቀርቡትን ጥያቄዎችና ሀሳቦችን ቆራራጦ በሚዲያ በማቅረብ ለፕሮፖጋንዳ እንዲጠቀሙበት እድል ይሰጣቸዋል። ከሁሉም በላይ በመድረኩ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ጠንካራ መምህራንን ለይቶ ለመጉዳትም ያስችላቸዋል። ይህ ደግሞ ከዚህ በፊትም በተግባር ያየነው ነገር ነዉ።

3) በስብሰባው ላይ መሳተፍና ምንም አይነት ሀሳብም ሆነ ጥያቄ አለማንሳት (Silent Protest)። ይህ ከሁሉም ተመራጭ የሆነ የተቃዉሞ ዘዴ ነዉ። መምህራንን ለምንም አይነት አደጋ አያጋልጥም (It has Zero Cost) ። በአብዛኛው ዝም በማለት የጠላትን ልቦና ለማዳከምና ለማሸበር (Psychological Terror) ይረዳል። በተጨማሪም በመምህራኑ ዉስጥ አስርገው የሚያስገቧቸው አስመሳዮችና የመንግስት ካድሬዎችን ለመለየትና ለወደፊቱም ለመጠንቀቅ ይረዳል።

በመሆኑም ከነገ ጧት ጀምሮ ሁሉም መምህራን በስብሰባው በመገኘት በአንድነትና በፅናት በዝምታ ተቃውሟቸውን እንዲገልፁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ከዚህ በፊት ስታነሷቸው የነበሩት ጥያቄዎችና እናንተ ያፈራችኋቸው ተማሪዎቻችሁ ይህንን ስርዓት እንዳናጋው ሁላ በዚህ ስብሰባም ድምፃቹን በጋራ መንፈጋችሁ ይበልጡኑ ስርዓቱን ግራ ያጋባዋል።

በአንድነት ዝምታን በመምረጥ
ጠላትን ግራ አጋቡት!

#Oromoprotests

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule