• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሆላንዱ ወርክሾፕ – ኢትዮጵያ እና መጭው የርስበርስ ጦርነት

September 25, 2016 01:52 am by Editor 2 Comments

ሃገራችን በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ ነው ያለችው። ይህ ቀውስ ወደ እርስበርስ ጦርነት እያመራ ይገኛል። ጉዳዩ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ላይ ጥቅም ያላቸው የውጭ ዜጎችንም ማሳሰቡ አልቀረም። በሆላንድ፣ ዘ ሄግ ከተማ፣ ዲያማንት ኮሌጅ 24 ሴፕቴምበር 2016 በተደረው በዚህ ወርክሾፕ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና የሆላንድ ዜጎች ተገኝተው ነበር። በወርክሾፑ እንዲወያዩ የተጋበዙት ታዋቂው ፕሮፌሰር ጆን አቢንክ፣ መስፍን አማን እና ገረሱ ቱፋ ናቸው። አወያዮቹ ሚ/ር ፍራንስ እና አብይ አሸናፊ ነበሩ።

ethi-holland2ተናጋሪዎቹ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ከፍተኛ ቀውስ በማስረጃ እያጣቀሱ ካብራሩ በኋላ የገዥው ፓርቲ አጠያያቂ ህጋዊነት እና የማክተሙ አዝማምያን ያመላከተ ድምዳሜ ሰጥተዋል።

መጪውን ሁኔታ የሚጠቁሙ ሶስት ቢሆኖች (Scenarios) ላይም የውይይቱ ተሳታፊዎች አስተያየቶቻቸውን ሰጥተዋል።

አንደኛው ቢሆን (Scenario) የፕ/ር መስፍን ወልደማርያም፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና የዶ/ር ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በመገናኛ ብዙሃን የተሰራጩ አስተያየቶች ሲሆኑ፤ በጥቅሉ ኢትዮጵያ ወደ እርስበርስ ጦርነት እንደምታመራ የሚጠቁመው እይታ ነው።

ሁለተኛው ቢሆን በገዥው ፓርቲ እየተነገረ ያለው የተሃድሶ ለውጥ የሚለው እንቅስቃሴ ሲሆን፤

ሶስተኛው ቢሆን ደግሞ የሽግግር መንግስት ይቋቋማል፣ ከዚያም ፍትሃዊ ምርጫ ይደረጋል የሚለው ግምት ነው።

ሶስቱም ተናጋሪዎችም ሆኑ በአዳራሹ ያሉ ተሳታፊዎች ሁለተኛው እና ሶስተኛው ቢሆኖች የማይታሰቡ እንደሆኑ አስምረውበታል። በተለይ ሁሉንም አካላት ያካተተ የሽግግር መንግስት ተቋቁሞ ፍትሃዊ ምርጫ ቢደረግ ችግሩ እንደሚፈታ ፕ/ር ጆን አቢንክ ተናግረዋል። ነገር ግን ከገዥው ፓርቲ የረጅም ግዜ ተመክሮ እና  ባህርይ አንጻር ይህ ሊሆን አይችልም። ገዥው ፓርቲ ለትይታ ብቻ የሚሆን ቅርጻዊ ለውጥ (cosmetic changes) በማድረግ መቆየት መርጣል ይላሉ።

መስፍን አማን እና ገረሱ ቱፋም አንደኛው ቢሆን ላይ ነው የሚያመለክቱት፣ “ከሁሉም ቢሆኖች እርስበርስ ጦርነቱ መጥፎው አማራጭ ቢሆንም፣ ይህ ሊሆን ግድ ሆኗል። ጠቅላይ ሚንስትሩ የህዝቡን ጥያቄ ለማፈን ሰራዊቱን ሲያዙ ነው ጦርነት ያታወጀው።  ሃገሪቱ አንደኛውን በርስበርስ ጦርነት ውስጥ ገብታለች” ባይ ናቸው።

የዲያስፖራው ሚናም በውይይቱ ተነስቷል። ዲያስፖራው ከዘር እና ከጎሳ ውይይት አልፎ በጋራ ችግሮች፣ በብሄራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲወያይ ፕሮፌሰር አቢንክ መክረዋል።

ገረሱ ቱፋ  እና ከመስፍን አማንም የኦሮሞ እና አማራ ተወላጆች በግል የማንስማማባቸው ብዙ ጉዳዮች ቢኖሩም በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠን በሃገሪቱ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር እና መፍትሄ ለመፈለግ ችግር የለብንም ብለዋል። ከስብሰባው በኋላ የኦሮሞ እና አማራ ኮሚኒቲ አባላት የጋራ መድረክ ለመመስረት ተስማምተዋል።ethi-holland3

እንደዚህ አይነት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ውይይት ሲካሄድ የሆላንድ ዜጎች በተለምዶ ተገኝተው አያውቁም ነበር። በዚህ ውይይት ላይ አሁን ለመገኘት የፈለጉበት ምክንያትም ግልጽ ነው። በሃገሪቱ እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ አመጽ የሆላንድን ብሄራዊ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የዳች ሜዲያ ተቋማት እየገለጹ ነው። በአስር ሚሊዮን ዩሮ ኢንቨስትመንት  ከአመት በፊት ኢትዮጵያ በመግባት አበባ ምርት የተሰማራው ኩባንያ በባሕርዳር ህዝባዊ አመጽ ሙሉ በሙሉ ወድሞ ስራውን በይፋ አቁሟል። ጊንጪ ላይም የሆላንድ የእርሻ ኩባንያ ከጥቅም ውጪ መሆኑ በዜና ተሰምቷል። ይህ ጉዳይ ሄነከን ቢራን ጨምሮ ለተቀሩት 130 የሚሆኑ የሆላንድ ኩባንያዎች ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።

ክንፉ አሰፋ

Filed Under: News, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    September 26, 2016 07:18 pm at 7:18 pm

    ጓዶች!! የሌለ ነገር እየፈጠራችሁ ሰው አታደናግሩ! ሁሉም ሰው በሰላም ለመኖር ይፈልጋል! የምትጠቅሷቸው ሰዎች ሁሉ ፋይዳ ሰጪዎች አይደሉም!! ወሳኙ ሃገር ውስጥ ያለው ህዝብ ነው!

    Reply
    • ማህሌት says

      September 29, 2016 07:47 am at 7:47 am

      የምትሰጠው አስተያየት ማንነትህን ስለሚያሳይ መልስ ባያስፈልግህም የበላህን እያከከው እንደሆነ ያስታውቃል ወያኔ ሞቱ ደርሶ ሲፈራገጥ እንዳንተ ያሉ ደጋፊዎቹ እውነቱ አልዋጥም ቢላችሁ አይገርምምናት!!

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule