• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሆላንዱ ወርክሾፕ – ኢትዮጵያ እና መጭው የርስበርስ ጦርነት

September 25, 2016 01:52 am by Editor 2 Comments

ሃገራችን በከፍተኛ ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ ነው ያለችው። ይህ ቀውስ ወደ እርስበርስ ጦርነት እያመራ ይገኛል። ጉዳዩ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ላይ ጥቅም ያላቸው የውጭ ዜጎችንም ማሳሰቡ አልቀረም። በሆላንድ፣ ዘ ሄግ ከተማ፣ ዲያማንት ኮሌጅ 24 ሴፕቴምበር 2016 በተደረው በዚህ ወርክሾፕ በርካታ ኢትዮጵያውያን እና የሆላንድ ዜጎች ተገኝተው ነበር። በወርክሾፑ እንዲወያዩ የተጋበዙት ታዋቂው ፕሮፌሰር ጆን አቢንክ፣ መስፍን አማን እና ገረሱ ቱፋ ናቸው። አወያዮቹ ሚ/ር ፍራንስ እና አብይ አሸናፊ ነበሩ።

ethi-holland2ተናጋሪዎቹ ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ከፍተኛ ቀውስ በማስረጃ እያጣቀሱ ካብራሩ በኋላ የገዥው ፓርቲ አጠያያቂ ህጋዊነት እና የማክተሙ አዝማምያን ያመላከተ ድምዳሜ ሰጥተዋል።

መጪውን ሁኔታ የሚጠቁሙ ሶስት ቢሆኖች (Scenarios) ላይም የውይይቱ ተሳታፊዎች አስተያየቶቻቸውን ሰጥተዋል።

አንደኛው ቢሆን (Scenario) የፕ/ር መስፍን ወልደማርያም፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እና የዶ/ር ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በመገናኛ ብዙሃን የተሰራጩ አስተያየቶች ሲሆኑ፤ በጥቅሉ ኢትዮጵያ ወደ እርስበርስ ጦርነት እንደምታመራ የሚጠቁመው እይታ ነው።

ሁለተኛው ቢሆን በገዥው ፓርቲ እየተነገረ ያለው የተሃድሶ ለውጥ የሚለው እንቅስቃሴ ሲሆን፤

ሶስተኛው ቢሆን ደግሞ የሽግግር መንግስት ይቋቋማል፣ ከዚያም ፍትሃዊ ምርጫ ይደረጋል የሚለው ግምት ነው።

ሶስቱም ተናጋሪዎችም ሆኑ በአዳራሹ ያሉ ተሳታፊዎች ሁለተኛው እና ሶስተኛው ቢሆኖች የማይታሰቡ እንደሆኑ አስምረውበታል። በተለይ ሁሉንም አካላት ያካተተ የሽግግር መንግስት ተቋቁሞ ፍትሃዊ ምርጫ ቢደረግ ችግሩ እንደሚፈታ ፕ/ር ጆን አቢንክ ተናግረዋል። ነገር ግን ከገዥው ፓርቲ የረጅም ግዜ ተመክሮ እና  ባህርይ አንጻር ይህ ሊሆን አይችልም። ገዥው ፓርቲ ለትይታ ብቻ የሚሆን ቅርጻዊ ለውጥ (cosmetic changes) በማድረግ መቆየት መርጣል ይላሉ።

መስፍን አማን እና ገረሱ ቱፋም አንደኛው ቢሆን ላይ ነው የሚያመለክቱት፣ “ከሁሉም ቢሆኖች እርስበርስ ጦርነቱ መጥፎው አማራጭ ቢሆንም፣ ይህ ሊሆን ግድ ሆኗል። ጠቅላይ ሚንስትሩ የህዝቡን ጥያቄ ለማፈን ሰራዊቱን ሲያዙ ነው ጦርነት ያታወጀው።  ሃገሪቱ አንደኛውን በርስበርስ ጦርነት ውስጥ ገብታለች” ባይ ናቸው።

የዲያስፖራው ሚናም በውይይቱ ተነስቷል። ዲያስፖራው ከዘር እና ከጎሳ ውይይት አልፎ በጋራ ችግሮች፣ በብሄራዊ ጉዳዮች ላይ እንዲወያይ ፕሮፌሰር አቢንክ መክረዋል።

ገረሱ ቱፋ  እና ከመስፍን አማንም የኦሮሞ እና አማራ ተወላጆች በግል የማንስማማባቸው ብዙ ጉዳዮች ቢኖሩም በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠን በሃገሪቱ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር እና መፍትሄ ለመፈለግ ችግር የለብንም ብለዋል። ከስብሰባው በኋላ የኦሮሞ እና አማራ ኮሚኒቲ አባላት የጋራ መድረክ ለመመስረት ተስማምተዋል።ethi-holland3

እንደዚህ አይነት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ውይይት ሲካሄድ የሆላንድ ዜጎች በተለምዶ ተገኝተው አያውቁም ነበር። በዚህ ውይይት ላይ አሁን ለመገኘት የፈለጉበት ምክንያትም ግልጽ ነው። በሃገሪቱ እየተካሄደ ያለው ህዝባዊ አመጽ የሆላንድን ብሄራዊ ጥቅም ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የዳች ሜዲያ ተቋማት እየገለጹ ነው። በአስር ሚሊዮን ዩሮ ኢንቨስትመንት  ከአመት በፊት ኢትዮጵያ በመግባት አበባ ምርት የተሰማራው ኩባንያ በባሕርዳር ህዝባዊ አመጽ ሙሉ በሙሉ ወድሞ ስራውን በይፋ አቁሟል። ጊንጪ ላይም የሆላንድ የእርሻ ኩባንያ ከጥቅም ውጪ መሆኑ በዜና ተሰምቷል። ይህ ጉዳይ ሄነከን ቢራን ጨምሮ ለተቀሩት 130 የሚሆኑ የሆላንድ ኩባንያዎች ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።

ክንፉ አሰፋ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    September 26, 2016 07:18 pm at 7:18 pm

    ጓዶች!! የሌለ ነገር እየፈጠራችሁ ሰው አታደናግሩ! ሁሉም ሰው በሰላም ለመኖር ይፈልጋል! የምትጠቅሷቸው ሰዎች ሁሉ ፋይዳ ሰጪዎች አይደሉም!! ወሳኙ ሃገር ውስጥ ያለው ህዝብ ነው!

    Reply
    • ማህሌት says

      September 29, 2016 07:47 am at 7:47 am

      የምትሰጠው አስተያየት ማንነትህን ስለሚያሳይ መልስ ባያስፈልግህም የበላህን እያከከው እንደሆነ ያስታውቃል ወያኔ ሞቱ ደርሶ ሲፈራገጥ እንዳንተ ያሉ ደጋፊዎቹ እውነቱ አልዋጥም ቢላችሁ አይገርምምናት!!

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule