• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ላም እሳት ወለደች!

October 18, 2016 03:33 am by Editor Leave a Comment

አጉል ዘመን ገጥሟት በረት ብትከሳ፤
ከብቶች በመዥገሮች አዩ ብዙ አበሳ፡፡
ጡቶቿን አቃጣይ የነበልባል ጥጃ ላም እሳት ወለደች፤
ብ’ተው በማይተዋ ዘልለው ባልጠገቡ ወይፈኖች ነደደች፡፡
የከበረው ባህል ባለጌ ረጋግጦት እንደጨው ቀለለ፤
ወፍ ዘራሾች ነግሠው ባጥለቀለቁት ደም ምድር ተበከለ፡፡

አዎ፣ ላም እሳት ወለደች!
እንደዮዲት ጉዲት እቶኑ የሚፋጅ፤
ዕረፍት በማያ’ቅ ሠይፍ እንደነደርቡሾች እንደግራኝ አህመድ፤
ጭንቅላትን ገምሶ አንገትን ቆራርጦ ዜጎችን የሚያነድ፡፡

“አጥንትና ደሜ ይሄው የናንተው ነው፤
እኔ ከሌለሁኝ እናተም እንዲያው ነው፤
እርቧችሁ ጠግቤ፣ ብድንም ሞታችሁ፤
ማንም ስለሌለ ከኔ ‘ሚለያችሁ፤
እስከመጨረሻው አጅቡኝ ባካችሁ፡፡ ”

እያለ እሳት ጥጃው ሕዝብን ይማጠናል፤
መስሎት የማናውቀው ቁርበት ዘርጉ ይላል፡፡
ክፋትና ተንኮል ተፈጥሮው የሆነ፤
ሕግና ሥርዓትን ባዋጅ ያወደመ፤
የሰው ገላ ችቦ አንድዶ የሞቀ፤
ቆላ ደጋ ሳይል ሰደድ የለቀቀ፤
በገጠር ከተማ ቋያ ያዘነመ፤
ሁሉንም በመዝረፍ ራቁት ያስቀረ፤
መላ ከብትን ሸጦ በረት ያራቆተ፤
በዝረፍ እንዝረፍ የደንቆሮ ስብከት ሞኝን ያጃጃለ፤
ያልበላውን ዕዳ ትውልድ እንዲከፍል ቢል ያስተላለፈ፤
የሶላቶ ውላጅ ምድረ የሹምባሽ ልጅ፤
የባንዳ ጥርቅም የናት አንጀት በጣሽ፤
ላም እሳት ወለደች ታቅፎ የማይሳም ሣጥናኤልን ወራሽ፡፡

አዎ፣ ባንዳ ነገሠና ብዙ ታምር ታዬ፤

ጥላቻ ተዘርቶ ትርምስ በረዬ፤
ፍትህ ዐይኗ ጠፍቶ ዜጋ ተሰቃዬ፡፡
የከርቸሌ በሮች ሌት ተቀን ተከፍተው፤
ፍርድ ተገልብጦ ከሌለው ወዳለው፤
ይሉኝታና ሀፍረት ካድማስ ማዶ ርቀው፤
የ’ውነቱ አንገት ጠፍቶ ማተብ ማስቀመጫው፤
ተኖሮ ተሙቶ  “አለን” እንላለን ላለፍ ላገደመው፡፡

እንጂ፤ ተቸግረን እንጂ እውነት ጠፍታብነ፤
ተሳስረን እንጂ ነው ፍትህ ወድማብነ፡-

ስርቆት ባህል ሆኖ እያስመሰገነ፤
ውሸት ጽድቅ ሆኖ ሃቅ እያስኮነነ፤
ክብር ውርደት ሆኖ ውርደት ሲሆን ክብር፤
መች እናይ ነበረ ፍርድ እየተዛባ ስትፈራርስ ሀገር?

ከደጓ ላም ማኅጸን የተወለደው’ሳት፤
ኦሮሞን ካማራ ትግሬን ከኤርትራ አኙዋኩን ከኑዌር፤
ሊያናቁር ሊያናክስ ሊያደርጋቸው ጠላት፤
ነሰነሰ መርዙን ለሩብ ም’ት ዓመታት፡፡

ስለዚህ ወገኔ ትግራዩ ተነሣ፤
“በቃኝ!” በለውና ባንዴራህን አንሳ፤
ለመብትህ እምቢ በል ትግሉን ተቀላቀል፤
ዮሐንስ ይኩራብህ አሉላም አይፈር፤
የወንድሞችህ ደም ያንተም ደም ነውና፤
በምታውቀው ትግል የአርዮስን አረም ከሥሩ በመንቀል፤
የተሻመንከው ሕዝብ በሃሤት ይፈንድቅ፣ አብሮህ እልል ይበል፡፡

የጋራ ጠላትን በሚጠራርገው የማይቀር ጎርፍ ላይ፤
ምራቅህን ጨምር ታሪክ ተለውጦ እውናዊ ነፃነት በተግባር እንዲታይ፡፡

ትግርኛ ግጥም –  አሰር ኣሉላ ዮሐንስ

ነፃ ትርጉም –  ይነጋል በላቸው (yinegal3@gmail.com)

የግጥሙ ርዕስ  –  ላሕሚ እንታይ ወሊዳ ?

ምንጭ –  ethiomedia.com

ማጠቃለያ

  • የኦሮሞው ደም፣ የአማራው ደም፣ የኮንሶው ደም፣ የጋምቤላው ደም የትግራይ ሕዝብ ደም ነው !
  • ህወሓት ለአሁኒቷ ኢትዮጵያ ችግሮች ተባብሶ መቀጠልና ለውድቀታችን ዋና ተጠያቂ ነው !
  • ህወሓት ሳይውል ሳያድር ከሥልጣን ይወገድ!
  • (ሁሉንም ወገን የሚያሣትፍ) ዴሞክራሲያዊ የሽግግር መንግሥት አሁኑኑ በሀገራችን ይመሥረት!
Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule