• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት/ኢህአዴግ ዕድሜዬ ከ6 ወር አይበልጥም አለ

October 10, 2016 12:30 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም የሚገዛው ህወሃት ላለፉት 25ዓመታት መብት በገፍ ሲሰጥ የቆየ ይመስል ህገመንግሥታዊ መብቶችን የሚገፍ ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። አዋጁ ለስድስት ወር ይቆያል ማለቱ የህወሃት ዕድሜ ከስድስት ወር እንደማይቆይ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል፡፡

ከህወሃት በተሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ኃይለማርያም ደሳለኝ ትላንት እሁድ በሃገሪቱ “ያንዣበበውን አደጋ ለመቀልበስ” በሚል ሚኒስትሮች ምክር ቤት ለስድስት ወራት የሚዘልቅ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ማወጁን አስታውቋል። እንደ ኃይለማርያም ንግግር ህገመንግሥታዊ መብቶች የማይጣሱ መሆናቸው ቢነገርም እዚያው የኃይለማርያም ካቢኔ አባል የሆነው የጠቅላይ አቃቤ ሹመኛው ጌታቸው አምባዬ ህወሃት በቀጣይ እንደፈለገ የሚያደርጋቸውንና የሚገድባቸውን መብቶች በዝርዝር ተናግሯል። እነዚህም:-

1) ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማንኛውንም ሰው ይታሰራል፤ (ለ25 ዓመታት ሲደረግ ነበር)soilders 1
2) ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ የማንኛውም ሰው ቤት፣ ንብረት፣ ይበረበራል፤ (ለ25 ዓመታት ሲደረግ ነበር)
3) ይፋይም ይሁን የህቡህ ቅስቀሳ ይከለከላል፤ (ለ25ዓመት ተከልክሎ ነበር፤ እስርቤት የታጎሩት ምስክር ናቸው)
4) ጽሁፍ ማዘጋጀት፣ ማተምና ማሰራጨት ይከለከላል፤ (ጋዜጠኞችን በማሰር፣ ከአገር በማባረር፣ … ህወሃት የሚገዛት ኢትዮጵያ ቀዳሚ ነች)
5) ትእይንት ማሳየት ይከለከላል፤ (ላለፉት 25ዓመታት ተከልክሏል)
6) በምልክት መግለጽ ይከለከላል፤ (የአማራ ተጋድሎና የኦሮሞ ተቃውሞን ምልክቶች ለመገደብ የታሰበ)
7) መልእክትን በማናቸውም መንገድ ለህዝብ ይፋ ማድረግ፤ (ማኅበራዊ ሚዲያ በተለይ ፌስቡክን ለመገደብ ትዊተርን ለማነቅ የታቀደ)

በዚህ ገለጻ ጌታቸው አምባዬ ከአለቃው ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር በግልጽ የሚጋጭ መልስ ሰጥቷል፡፡

ያስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ካልወጣበት ቀን (ከቅዳሜ) ጀምሮ ተግባራዊ ሆኗል ተብሏል፡፡ ሟቹ መለስ በ1997ቱ ምርጫ ለአንድ ወር የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሲለፍፍ ወሩ ሲሞላ አዋጁ ስለመነሳቱ የተነገረ አለመኖሩ አገሪቱ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ባሰቸኳይ ጊዜ አዋጅ ነበረች የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ ህወሃት አሁን በለፈፈው ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለተፈጠረው ችግር “በጥልቅ መታደስ” ስላቃተው በጥልቅ ለመግደል ማሰቡ የራሱን መቀበሪያ ጉድጓድ በጥልቅ የቆፈረበት አዋጅ ነው ተብሏል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule