• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በጌድዮ ዞን ፖሊስ አዛዥ በአጋዚ ተገደለ

October 10, 2016 09:20 am by Editor Leave a Comment

በጌድዮ ዞን የምትገኘው ዲላ ወረዳ ፖሊስ ዋና አዛዥ በአጋዚ ተገደለ ሲሉ በስልክ ያነጋገርናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸውልናል።

ከሶስት ቀናት ቃጠሎ፣ ዘረፋ እና ውድመት በኋላ አጋዚ በትላንትናው እለት ዲላ እንደገባ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል። አጋዚ የጦር ቀጠና ምትመስለው ዲላ ከተማ እንደገባ አቶ ከበደ የተባሉትን የዞኑን ፖሊስ አዛዥ በጥይት ደብድቦ ገድሏቸዋል።

ላለፉት ሶስት ቀናት በዲላ፣ ይርጋጨፌ፣ ወናጎ እና ፍሰሀ-ገነት የተነሳው አመጽ ያነጣጠረው በጉራጌ እና አማሮች ላይ ነበር። የጌዲዮ ተወላጆች ከአካባቢው ካድሬዎች እየታዘዙ አብያተ-ክርስትያናትን እና መስጊዶችን ጨምሮ 60 የሚሆኑ መኖርያ ቤቶችን አቃጥለዋል። ህወሃት ሕዝባዊ አመጹን  መቋቋም ስላልቻለ ከ10 አመታት በፊት የነበረውን ቁርሾ በመቀስቀስ የጌዲዮ ተወላጆች በአማራ እና በስልጤ ተወላጆች ላይ ዘመቻ እንዳስነሳ ነው የአካባቢው ሕዝብ የሚናገረው።

በስልክ ያነጋገርናቸው አንዲት የአማራ አዛውንት ንብረታቸው ሙሉ በሙሉ እንደወደመና የሚያርፉበት መጠለያ እንኳን እንደሌላቸው ተናግረዋል። ልጆቻቸው በሙሉ ጥቃቱን በመሸሽ ወደ ጫካ እንደገቡም ተናግረዋል። የአካባቢው የስልጤ ተወላጆች ለግዜው በመስጊድ ውስጥ ተጠልለዋል ብለዋል።

በይርጋጨፌ፣ ዲላ፣ ወናጎ፣ ፍሰሀ-ገነትና በአቅራቢያው የሚኖሩ ሰዎች የቧንቧ ውሃ እንዳይጠጡ ውስጥ ምስጢሩን የሚያውቁ ዜጎች ለሕዝቡ ተናግረዋል። በጌዴኦ ዞን የከተማው ነዋሪ ለመጨረስ የመጠጥ ውሃውን ዴፖ መርዘዋል እየተባለ ነው።

ዲላ ነዋሪ ሕዝብ ላለፉት ለሶስት ቀናት የከፋ መከራ ውስጥ ነው ያለው። የአካባቢው ፖሊስ ሕዝቡ ከቤት  እንዳይወጣ ሲያዝዝ አጋዚ ደግሞ ከቤት ወጡ የሚል ትእዛዝ እየሰጡ ነው።

ትናንት ከተማው ውስጥ የገባው አጋዚ አስታራቂ በመምሰል የሚፈልገውን እያሰረ እና እየገደለ እንደሚገኝ ነው የተነገረው።

በአካባቢው ያሉ የመንግስት ባለስልጣናት እና ካድሬዎች በሙሉ አዋሳ ገብተው እንዳበቁ ወደ አዋሳ የሚወስደው መንገድ ዝግ ሆኗል።

በትግራይ ነጻ አውጪው አገዛዝ ሆን ተብሎ እንዲህ ያለው የዘር ግጭት በጊዴዮ እንዲባባስ ሕጻናትን ጭምር ማስታጠቁን የግጭቱ ሰለባዎች ይናገራሉ። (ፎቶ: ለማሳያ የተወሰደ)

ክንፉ አሰፋ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule