የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መከላከያ ሠራዊት ኢታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርኃኑ ጁላ ከዑጋንዳ የመከላከያ ሚኒስትር ጋር በወቅታዊ የሁለቱ አገሮች ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይታቸው የሁለቱ አገሮች የመከላከያ ዘርፍ ስምምነት ያለበት ደረጃ የተዳሰሰ ሲሆን በቀጣይ ስምምነቱን ለማደስ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ ይህም ሥምምነቱን የማደስ ሥራ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዲፈፀም መመሪያ ተሰጥተዋል ተብሏል፡፡ ሁለቱ ኃላፊዎች በዋናነት ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲዘገብ ስለነበረውና አሸባሪው የሕወሓት ቡድን የሥልጠናና ሌሎች ድጋፎችን በአሜሪካ፣በግብጽና በደቡብ ሱዳን በመታገዝ በዑጋንዳ አማካኝነት እገዛ እያገኘ ነው የሚለውን ወሬ የዑጋንዳ መከላከያ ሚኒስትር ፈፅሞ ከዕውነት የራቀ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የመከላከያ ሚኒስትሩ ሀገራቸው ኢትዮጵያን የአፍሪካ እናት … [Read more...] about የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ
Middle Column
መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ከመካከለኛው ምስራቅ አካባቢ የሚሰሙ ዘገባዎች እንደሚጠቁሙት ኢትዮጵያ ከትህነግ ጋር ወደ ዳግም ጦርነት ልትገባ እንደምትችል ጠቁመዋል። ትህግም ለውጊያ እየተዘጋጀሁ ነኝ ሲል ተሰምቷል። ኤርትራ ደግሞ በሩሲያ ሠራሽ ድሮኖች ራሷን አጠናክራለች። ከተለያዩ የዜና ምንጮች ለመገንዘብ እንደሚቻለው የኢትዮጵያ መካላከያ ሠራዊት አዲስ የማጥቃት ዘመቻ ሊጀምር ይችላል እየተባለ ነው። ለዚህም ይረዳ ዘንድ ኢትዮጵያ አዳዲስ ድሮኖችን ጨምሮ ተጨማሪ ተዋጊ ጀቶችን ወደ አገር ቤት በዚህ ማስገባቷ ተሰምቷል። ቱርክ ሰራሹ ባይራክ 32 ድሮን እና ተጨማሪ ጀቶች ወደ አዲስ አበባ ሳይገቡ አልቀረም። ከዚህ በፊት በተለያየ ዙር ሲሰለጥኑ የኖሩና በመጀመሪያው የክተት አዋጅ፣ የተመዘገቡ ወታደሮች እስካሁን ማስልጠኛ ካምፕ ውስጥ ቆይተው ሰሞኑን ወደ ወደ ተለያየ ክልል በተለይም ወደ አማራ ክልል ገብተዋል። … [Read more...] about መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል
ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች
ሩስያ የክፉ ቀን ወዳጄ ላለቻት ኤርትራ ድሮኖችን በድጋፍ የሰጠችው ለቀጠናው ሰላም ኤርትራ ወሳኝ ሃገር በመሆኗ እና ሩስያ ቀጣይ በኤርትራ ከምጽዋ 40 ኪ/ሜ ርቅት ላይ በኣፍኣቤት ለምትገነባው የጦር ሰፈር እንደ መጀመርያ ግብአትነት በመቁጠር ነው። የድሮን ድጋፉ የተሰጣት ኤርትራ ለአለፉት 3 ወራት በሩስያ ስልጠና የተሰጣቸውን 26 የድሮን ባለሙያዎቿን ጭምር አቀባበል በማድረግ ዛሬ በባፃ የድሮን ጣብያ በድምቀት ተቀብላለች። በዚህ ርክክብ ወቅት የተገኙት የኤርትራው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአደረጉት ንግግር "ይህ ከሩስያ የተደረገልን ድጋፍ የኤርትራን የጦር ኃይል በጥራት፣ በልምድ፣ በእውቀትና በታጠቀው የጦር መሳርያ በምስራቅ አፍሪካ ተወዳዳሪ ያደርገዋል" ሲሉ ተደምጠዋል። ባለፈው ወር የኤርትራው ውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኦስማን ሳሌህ ሩሲያን በጎበኙት ወቅት የሩሲያው ውጭጉዳይ … [Read more...] about ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች
አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ
"የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ሥልጣን" የለውም ክርስቲያን ታደለ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የንቅናቄውን ህግ ጥሰዋል በሚል 10 አባላቱን ከአባልነት አገደ፡፡ አብን ባወጣው መግለጫ ከድርጅት ህገ-ደንብ እና አሰራር ውጭ በመሆን አፍራሽ ድርጊቶችንና የዲሲፕሊን ጥሰቶችን በፈፀሙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ላይ የእርምት እርምጃ መወሰኑን ገልጿል፡፡ የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሚያዝያ 29 ቀን 2014 ዓ.ም አደረኩት ባለው አስቸኳይ ስብሰባ በፓርቲው መዋቅር የተለያዩ የሃላፊነት እርከኖች ውስጥ እየተከሰቱ ያሉ የዲሲፕሊን እና ድርጅታዊ መርህ ጥሰቶችን በፈጸሙ አባላቱ ላይ የእርምት እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡ በዚህም መሰረት የፓርቲው ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ የንቅናቄው ስራ አስፈጻሚ ሆነው ሳለ አፍራሽ ተልዕኮን ሲያረራምዱ ተገኝተዋል በሚል … [Read more...] about አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ
በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ
የአርሲ ዞን ሙኔሣ ወረዳ የእስልምና እምነት ተከታዮች ለኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮች ቤተክርስቲያን ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብር እና 20 የቀንድ ከብቶች አሰባስበው አበርክተዋል። በወረዳው የእስልምና እና የክርስትና እምነት ተከታዮች ለዘመናት በመከባበር እና በመቻቻል በፍቅር አብረው እየኖሩ መሆኑን የሁለቱ ሃይማኖቶች ተከታዮች ገልጸዋል። የሁለቱም እምነት ተከታዮች አንዳቸው ለሌኛው በየተራ መስጂድ እና ቤተክርስቲያን ተባብረው እያሠሩ በክፉ እና በደጉ አብረው ቆመው እስከ አሁን ደርሰዋል። የሁለቱ እምነት ተከታዮች አንዱ ለአንዱ ቤተ እምነት መሥራት የቆየ ከአባቶቻችን የወረስነው እሴት ስለሆነ እኛም ይህንኑ እያስቀጠልን ነው ብለዋል። የሥርዓት ለውጥም ሆነ የፖለቲካ ችግር ሀገሪቷን በገጠማት ወቅት ምንም ዓይነት የሃይማኖት ግጭት በወረዳው ተከስቶ አያውቅም ያሉት ነዋሪዎቹ፣ … [Read more...] about በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ
በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ
በትግራይ እናቶች "ልጆቻችሁን አምጡ" እየተባሉ በትህነግ ሰዎች እየታሰሩና እየተገደሉ ነው። ዘምተው የሞቱ ልጆቻቸውንም ሳይቀር "ውሸት ነው አልሞተም ልጅሸን አምጭ" እየተባሉ ችጋር ከሚጠብሳቸው ሌላ በየቀኑ ግፍ ይፈጸምባቸዋል። የወንበዴው ቡድን ዋና ግፍ ፈጻሚ አግአዚን ሲመራ የነበረውና በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የኮምዩኒኬሽን ኤሌክትሮኒክስ ሳይበር ዋና መምርያ ኃላፊ በነበረበት ጊዜ ከሰሜን ዕዝ ጋር የነበረውን ወታደራዊ የሬዲዮ ግንኙነት እንዲቋረጥ ያደረገው ገብረመድህን ወይም እነሱ ወዲ ነጮ እያሉ የሚጠሩት ቀብር አዲስ አበባ በተፈጸመበት ወቅት ደጋፊ ትህነጎች ወጥተው ትግራይ ትስርር እያሉ ሲጮሁ ነበር። አሸባሪ የተባለን ቡድን በአደባባይ በመደገፍ ይህንን ያህል ሰው ድምጹን ካሰማ ፈርቶ ዝም ያለውና ቀን የሚጠብቀው ምን ያህል ይሆን። በቂ የቪዲዮና የመንገድ ላይ ካሜራ … [Read more...] about በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ
ተስፋቢሱ ቴድሮስ
በዕውቀት ማነስ የሚሰቃየውና ሐኪም ሳይሆን የዓለምን የጤና መሥሪያቤት እየመራ ያለው ቴድሮስ አድሃኖም ተስፋው የተበተነ ይመስላል። በነ ቢል ጌትስና ወዳጆቻቸው ድጋፍ ያለብቃት አናት ላይ ላይ የተቀመጠው ቴድሮሰ አድሃኖም አብዛኛውን ጊዜ የሚያሳልፈው የተቀጠረበትን መሥሪያቤት በማገልገል ሳይሆን እንደ ፍንዳታ ስልኩ ላይ ተጥዶ ማኅበራዊ ሚዲያውን በማሰስ ነው። ነጋጠባ ትግራይ ትሰርዕ እያለ የሚፖስተው ቴድሮስ ከዱሮ የተጠናወተው ሰካራምነት አሁን ብሶበታል። በድጋሚ እንዳይመረጥ ዘመቻ ተከፍቶበት የነበረ ቢሆንም ጌቶቹ በቀጣይ ዓመታት የሚጠርግላቸው ቆሻሻ ስላለ አርፈህ ቀጥል ብለውታል። እርሱም ተስፋ ቆርጦ በመጠጥ መደንዘዙን ቀጥሎበታል። በትግራይ ከተደረገው ውጊያ በፊት ጀምሮ ትግራይን ልክ እንደ አገር በማስመሰል በማኅበራዊ ሚዲያ ሲታትር የነበረው ቴድሮስ አንዳንዴ ቀጥተኛ ሌሎች … [Read more...] about ተስፋቢሱ ቴድሮስ
ከሽፏል!
የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሴኔት HR6600/S3199 ሕግ ሆኖ እንዲፀድቅ የቀረበው የውሳኔ ኃሳብ እንዲቋረጥ ወሰነ። HR6600 እና S3199 ረቂቅ ሕጎች ሕግ ሆነው ከመውጣት እንዲዘገዩ የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሴኔት ውሳኔ ላይ መደረሱን የኢትዮጵያ አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ረቂቅ ህጉ እንዲቋረጥ ለጊዜው ከስምምነት የተደረሰበት ውሳኔ በቀጣይም ህግ ሆነው እንዳይፀድቁ ኢትዮጵያውያን እያደረጉት ያለው የዲፕሎማሲ ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ካውንስሉ አሳስቧል። የኢትዮጵያ አሜሪካ ሲቪክ ካውንስል በኢትዮጵያ ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነትና ጫና በመቃወምና ዳያስፖራ ማህበረሰቡን ጭምር በማስተባበር ከፍተኛ የህዝብ ዲፕሎማሲ ስራ በመስራት ላይ ያለ መቀመጫውን በአሜሪካ ያደረገ ተቋም ነው። (AMN) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከሽፏል!
“ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች
እኤአ በፌብሩዋሪ 2014 በ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወደ ሥልጣን የመጣውንና ምርጫው “ደህንነትና ትብብር ድርጅት” (OSCE Organization for Security and Cooperation) በተሰኘው ዓለምአቀፋዊ ድርጅት የጸደቀው የዩክሬን መንግሥት በመፈንቅለ መንግሥት ተወገደ። ፕሬዚዳንቱ ቪክቶር ያኑኮቪች ሕይወታቸውን ለማዳን ከአገር ለቅቀው ወጡ። መፈንቅለ መንግሥቱ የተቀነባበረው በተለይ በአሜሪካ ባልሥልጣናት ነው። ትውልደ ዩክሬን የሆነችውና በወቅቱ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአውሮጳና ዩሬዢያ ረዳት ጸሐፊ የነበረችው ቪክቶሪያ ኑላንድ የሤራው ዋና አቀናባሪ ነበረች። አብሯት ሟቹ ሴናተር ጆን ማኬይን ሠርቷል። ፕሬዚዳንት ያኑኮቪችን ከሥልጣን ለማስወገድ ቪክቶሪያ ራሷ ከማስተባበር ባለፈ ሰላማዊ ሰልፍ የሚወጡትን ዩክሬናውያንን ከመደገፍ አልፋ ለሰልፈኞች ብስኩት ስታድል በወቅቱ … [Read more...] about “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች
166, 800 የአሜሪካን ዶላር፤ 19,850 ዩሮና ለሸኔ ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያ ተያዘ
መነሻውን አዲስ አበባ ከተማ ያደረገ አንድ ህገወጥ የገንዘብ አዘዋዋሪ ግለሰብ ዶላር እና ዩሮ በመኪና ጭኖ ወደ ጅቡቲ በጉዞ ላይ እያለ በቁጥጥር ስር ውሏል። ግለሰቡ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ3-68991 በሆነ ኮንቴነር ተሽከርካሪ ላይ 166 ሺህ 800 የአሜሪካን ዶላር እና 19 ሺህ 850 ዩሮ በመጫንና መዳረሻውን ጅቡቲ በማድረግ በመጓዝ ላይ እያለ በተደረገ ጥብቅ ክትትል መያዙን የኢፕድ ምንጮች ገልጸዋል። በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ላይ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በደረሰው ጥቆማ አዘዋዋሪውን ከነ ገንዘቡ በቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉንም ነው ምንጮቻችን ጨምረው የገለጹት፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ መነሻቸውን ሀረሪ ክልል ሀረር ከተማ ያደረጉ ሶስት ህገወጥ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪ ግለሰቦችም ከእነጦር መሳሪያቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እነዚሁ … [Read more...] about 166, 800 የአሜሪካን ዶላር፤ 19,850 ዩሮና ለሸኔ ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያ ተያዘ